2023-05-05 15:25:51
ቅዱስነታቸው በተገኙበት በምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም የድል በዓል ተከበረ ።
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት እና ብፁዕ አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም የድል በዓል ተከበረ ።
በዓለ ንግሡ ዛሬ ሚያዝያ 27 ቀን 2015 ዓ,ም በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ተከብሯል።
ታቦቱ ሕጉ በቅዱስነታቸው መሪነት ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ሥርዓተ ዑደት ከተደረገ በኋላ በገዳሙ የተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ወረብ ቀርቧል ፣ በዕለቱ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ሊቀ ጳጳስ እና በብፁዕ አቡነ ቶማስ ሊቀ ጳጳስ ዕለቱን በተመለከተ ትምህርተ ወንጌል እና ታሪካዊ መልእክት ከሰጡ በኋላ በመጨረሻ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማናት ሰፊ ትምህርት ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ተሰጥቶ የበዓሉ ፍፃሜ ሆኗል።
መልአከ ሰላም አባ ኪሮስ ወልደአብ
9.3K viewsEOTC TV, 12:25