Get Mystery Box with random crypto!

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

የሰርጥ አድራሻ: @eliasmeseret
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 100.56K
የሰርጥ መግለጫ

Journalist-at-large

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2024-03-16 15:28:57
ትናንት ለሊት ከንግድ ባንክ የሌላችሁን ገንዘብ ለወሰዳችሁ ተማሪዎች በሙሉ፣

በማወቅም ይሆን ባለማወቅ የወሰዳችሁትን ብር መልሱ አለበለዚያ ግን ተጠያቂ ትሆናላችሁ እየተባላችሁ ነው።

ግር የሚለው ግን ንግድ ባንክ እስካሁን ይህን በርካቶች የሌላቸውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ያወጡበትን ድርጊት በይፋ አለማሳወቁ ነው። "የሲስተም ችግር እንጂ የሳይበር ጥቃት አልደረሰብኝም" የሚል መግለጫ አሁን አውጥቷል።

የተፈፀመበት ዝርፊያስ?

ሌላው አለም ላይ ቢሆን መጀመርያ ድርጊቱ ይፋ ይደረጋል፣ ከዛም ምን ያህል ገንዘብ፣ በየትኛው አካባቢ ካሉ ተገልጋዮች፣ በምን መልኩ፣ የወሰዱ ሰዎች ላይ የሚወሰዱ አካሄዶች... ወዘተ የሚሉ መረጃዎች ቢያንስ ለደንበኞች ይነገራል።

ምስል: ማህበራዊ ሚድያ

@EliasMeseret
34.8K viewsElias M, 12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-16 12:07:04
ንግድ ባንክን ምን አጋጠመው?

ከትናንት ለሊት ጀምሮ ተመሳሳይ መልዕክቶች እየደረሱኝ ነበር፣ መልዕክቶቹም "በርካታ ሰዎች፣ በተለይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከንግድ ባንክ ከኤቲኤም እና ከኦንላይን ትራንስፈር በነፃ ገንዘብ ወስደዋል ወይም ትራንስፈር አርገዋል" የሚል ነው።

አንድ ተማሪ እንደጠቆመኝ "እኛ ጋር ጓደኞቻችን ከ100 ሺህ እስከ 50 ሺህ  የሰሩ አሉ። 435ሺ ብር የሰራ ተማሪ አለ በዛች ቅፅበት ምክንያቱም ለሊት ላይ ንግድ ባንክ የፃፍክለትን ብር ያወጣ ነበር። ይህ የሆነው ለሊት ከ6 ሰአት እስከ 9 ሰአት አከባቢ ነበር።"

ሌላ ተማሪ ሲያስረዳ "ለምሳሌ እኔ ጋር 500 ብር ቢኖረኝ  ዝም ብዬ ወደ አንተ 50,000 ብር ፅፌ በሞባይል ባንክ ብልክ ዝም ብሎ ይልክ ነበር" ብሏል። ወደ ኢ-ብር የላኩት ልጆች ግን አካውንታቸው ወዲያው እንደታገደባቸው ታውቋል።

አንድ መምህር ደግሞ "እኔ በምሰራበት ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ ተማሪዎች ለሊቱን ሙሉ በዛ ያለ ገንዘብ በኤቲኤምና በትራንስፈር ገንዘብ ሲያስተላልፉ እንደነበር ሰምቻለሁ። ይህም ነገር በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎችም እንደነበር ስለሰማሁ ጥቆማ ልስጥህ በሚል ነው የጻፍኩልክ" ብለዋል።

ይህን ተከትሎ ባንኩ "በሲስተም ችግር ምክንያት" አገልግሎቶቹ ላይ ማለትም በቅርንጫፎች፥ በኢንተርኔት ባንኪንግ፥ በሞባይል ባንኪንግ፥ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ አጋጥሟል ብሏል።

የባንኩን የስራ ሀላፊዎች በስልክ ለማግኘት ያደረግኩት ሙከራ አልተሳካም፣ ባንኩ ግን ምን እንደተከሰተ ዝርዝር መረጃ ለህዝብ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

@EliasMeseret
37.7K viewsElias M, 09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-16 03:35:57 ትናንት ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል ለበርካቶች የተሰጠው የ African Leadership Magazine Award ምንድን ነው?

አዩሬ አታፎሪ የተባለ ጋናዊ ጋዜጠኛ ሰሞኑን ያዘጋጀው የ African Governance Award ለኢንደስትሪ ሚኒስትራችን መበርከቱንና ከጀርባው ያሉ አንዳንድ መረጃዎችን አካፍዬ ነበር።

እስቲ የትናንት ምሽቱን ሽልማት ትንሽ እንፈትሸው።

የ African Leadership Magazine Award የሚዘጋጀው ደግሞ በናይጄርያዊው ጋዜጠኛ ኬን ጊአሚ ነው። ኬን ከዚህ በፊት 11 ግዜ ሽልማቶችን አዘጋጅቶ ሸልሟል፣ የዚህ አመት ሽልማቱም እንደ ሁል ግዜው ግርታን የሚፈጥር ሆኗል።

እንዴት?

1. ድርጅቱ በፌስቡክ ገፁ ላይ የዘንድሮ የሽልማቱ አሸናፊዎች ብሎ የዘረዘራቸው የኬንያው ፕሬዝደንት ዊልያም ሩቶ፣ የቀድሞው የላይቤርያው መሪ ጆርጅ ዊሀ፣ የታንዛኒያዋ ፕሬዝደንት ሳሚያ ሱሁሉ... ወዘተ ነበሩ (ማስረጃ: ስክሪንሾት ይመልከቱ)። ተሸላሚዎቹ በዛሬው እለት በስካይ ላይት ሆቴል ተገኝተው ሽልማት እንደሚወስዱ በስፋት አስተዋውቆ የመግቢያ ትኬት የሸጠ ቢሆንም በስፍራው አልተገኙም።

2. የቀድሞው ጠ/ሚር አቶ ሐይለማርያም ደሳለኝ ተሸላሚ እንደሆኑ በሰበር ዜና ገልፆ ነበር (ማስረጃ: https://www.facebook.com/share/p/pwqFJvcY4eFx4TjM/?mibextid=Nif5oz) እርሳቸው ግን መገኘት እንደማይችሉ ሲገልፁ ከሽልማት ዝርዝር ውስጥ እንዳልተካተቱ የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል። መገኘት ያልተመቸው ባይሆን በተወካይ ይወስዳል እንጂ እንዴት ከዝርዝር ይወጣል የሚለው ሌላው ጥያቄ ነው።

3. ልክ እንደ አቶ ሐይለማርያም ሁሉ የቦትስዋናው 'ሉካራ' ድርጅት ዳይሬክተር የሆኑት ናሲም ላህሪ የዘንድሮው 'ምርጥ የሴት መሪ/አመራር' ተብለው ይፋ ከተደረጉ በኋላ ማምሻውን ሽልማቱ ለከንቲባ አዳነች አቤቤ ተበርክቷል (ማስረጃ: ስክሪንሾች ተያይዟል)።

4. የትናንት ምሽቱን ፕሮግራም ወጪ የሸፈነው የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ነበር። እንደገና ይሄው መፅሄት የኮሚሽኑን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቃበታ "በመንግስት አገልግሎት ላበረከቱት አስተዋፅዖ" በሚል ሽልማት ሰጥቷል። የፕሮግራም ስፖንሰርን መልሶ መሸለም የጥቅም ግጭት መፍጠሩ የማይቀር መሆኑ ብቻ ሳይሆን እርስ በርስ መሸላለም መሆኑ ግልፅ ነው። አቶ ደበሌ ከዚሁ ተቋም የዛሬ አመት ሌላ ሽልማት ወስደው ነበር (ማስረጃ: https://www.facebook.com/share/p/cvKWKss1tzg9g66u/?mibextid=Nif5oz)

ማሳረጊያ:

አሁን አሁን እየተለመደ የመጣ ነገር ቢኖር የመንግስትም ሆነ የግል ድርጅቶች "ሽልማት አገኘን" የሚል ዜና መስማት ነው። እርግጥ ነው ትክክለኛ አለም አቀፍ እውቅና የሚያገኙ እንደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይነት ተቋማት አሉ፣ ግን ሌላ ጨዋታም አለ።

ታድያ ለእንዲህ አይነት ዜና ያለውን ከፍተኛ ጥማት የተረዱት በተለይ ናይጄርያውያን እና ጋናውያን ጋዜጠኞች ተፍ ተፍ እያሉ ይገኛሉ፣ ሽልማቶችን በገፍ ያከፋፍላሉ። ከዛም ለሚድያቸው የሚሆን ለማስታወቂያ በሚል ዳጎስ ያለ ክፍያ ይቀበላሉ፣ የሽልማት ስነ-ስርዐት አዘጋጅተው አንደኛ-ሁለተኛ-ሶስተኛ ደረጃ ስፖንሰር ብለው ከፋፍለው ገቢያቸውን ያጦፋሉ።

@EliasMeseret
36.5K viewsElias M, 00:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-16 03:35:41
33.3K viewsElias M, 00:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-15 22:46:54
(ዮርዳኖስ ፍቅሩ) ፓስፖርትህ ወሎ ሰፈር አካባቢ ወድቆ ስለተገኘ ያገኘው ግለሰብ በዚህ ቁጥር ደውለህ እንድትወስድ መልዕክት እኔ ጋር ልኳል።

0921335279
36.5K viewsElias M, edited  19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-15 22:37:20 አዳዲስ የዚህ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰቦች፣ እንኳን በደህና መጣችሁ።

ለሚኖራችሁ አስተያየት እና ጥቆማ @ContactElias መጠቀም ትችላላችሁ።

መልካም ግዜ።
33.8K viewsElias M, edited  19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-15 20:30:20
እነዚህ ወገኖች ቋሚ የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ሰራተኞች ነበሩ

ለስራ እንደወጡ ስድስቱ ባለፈው ቅዳሜ እለት ወንጂ ላይ ታገቱ፣ ብርም ተጠየቀባቸው። አምስቱ ተገድለው ዛሬ ተገኝተዋል፣ አንዱ ያለበት አልታወቀም።

ነፍስ ይማር ከማለት ውጪ ምን ይባላል?

@EliasMeseret
35.2K viewsElias M, 17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-15 19:54:30
ኮመንት ላይ የሚሳደብ ካድሬ ሁሉ ወዶ እንዳልሆነ እገነዘባለሁ፣ ከሚደርሱኝ ማሳያዎች አንዱ...

@EliasMeseret
33.5K viewsElias M, 16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-15 19:37:05
እስራትን ፍትህ ለማስፈን ወይስ ለበቀል?

ህግ በትክክል በሚከበርበት ሀገር አንድ ሰው ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ የፍርድ ሂደቶችን አልፎ ነፃ ወይም ወንጀለኛ ይባላል፣ አልፎ አልፎም በምህረት ይፈታል።

እኛ ሀገር በተለይ አሁን አሁን ሁሉም በሚባል ደረጃ የፖለቲከኛ እስረኞች፣ ጋዜጠኞች ወይም የቅራኔ ድምፅ ያሰሙ ይያዛሉ፣ ካለ ፍርድ ሂደት ብዙ እንዲሰቃዩ ይደረጋል፣ ከዛም "ለህዝብ ጥቅም" ተብሎ ይፈታሉ።

የተፈቱት በደስታ ከእስር ቤት ይወጣሉ፣ እንኳን ደስ አላችሁ፣ እንኳን ደስ አለን ይባላል... እስሩን የፈፀመው አካል ግን ተሳስቶም ይሁን ለበቀል እስራቱን ቢፈፅም ህግ አይጠይቀውም።

ለማንኛውም... ከእስር የወጣችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ።

@EliasMeseret
35.8K viewsElias M, 16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-13 21:38:35
ማወያየቱ መልካም አካሄድ ነው!

ይህ እንዳለ ሆኖ ቤተ ክርስቲያናት እና ገዳማት ታጣቂዎችን አስጠልለዋል፣ የመሳርያ ማከማቻ ሆነዋል፣ ማሰልጠኛ ናቸው እየተባለ በከፍተኛ የወታደራዊ አመራሮች ጭምር ከሁለት እና ሶስት ቀናት በፊት በመንግስት ሚድያዎች በስፋት ሲነገር ነበር።

መረጃው ትክክለኛ ከሆነ እነዚህን ቤተ ክርስቲያናት እና ገዳማት ህግ ማስያዝ ያስፈልጋል፣ ይህም የመንግስት ስራ ነው፣ ህዝብም ሊደግፍ ይገባል።

ነገር ግን በደፈናው "ቤተ ክትስቲያናት እና ገዳማት" እየተባለ በሀገሪቱ ዙርያ ያሉ የእምነት ስፍራዎችን እና የሀይማኖት አባቶችን ለጥቃት እያጋለጠ ይገኛል። በቅርቡ እንኳን በርካታ አባቶች ተገድለው ተጥለው ተገኝተዋል።

Mark my word... በመንግስት ሀላፊዎች እና በአክቲቪስቶቻቸው ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚፈፀመው የስም ማጥፋት እና የደፈና የጥላቻ ንግግር ካልቆመ ጥቃቶች፣ ግድያዎች ይቀጥላሉ።

ድርጊቱን ፈፃሚዎችም "መንግስት ራሱ መስክሮ የለ" በሚል የልብ ልብ ተሰምቷቸው ማድረጋቸውን ይቀጥላሉ።

@EliasMeseret
21.6K viewsElias M, edited  18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ