Get Mystery Box with random crypto!

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

የሰርጥ አድራሻ: @eliasmeseret
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 100.56K
የሰርጥ መግለጫ

Journalist-at-large

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 40

2023-02-23 21:51:52
በህልሜ ነው በውኔ...?

ነፃነትን አግኝቶ የማያውቀው የኢትዮጵያ ሚድያ ከ2010 ዓ/ም ወዲህ ደግሞ የሄደበትን የይባስ የቁልቁለት ጉዞን ኢቢሲ ማምሻውን መዘገቡ ግርምታን አጭሮብኛል፣ እውነታውን እንዲህ ማውጣት ይልመድባችሁም ያስብላል።

ይሄ የምስልቅል ጉዞ አንዳንዱን የሚድያ ባለሙያ ለሞት፣ ሌላውን ለእስር፣ ለስደት፣ ድምፁን ለማጥፋት እና ሙያ ለመቀየር አስገድዷል። በተለይ የመንግስት ሚድያው ከአሸርጋጅነት ወጥቶ ነፃ የሚወጣበትን ቀን እንናፍቃለን።

@EliasMeseret
26.5K views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 20:05:40
የህዝቡ የማህበራዊ ሚድያ ላይ ጩኸት አላስተኛ ያላቸው ሚድያዎች አሁን ነቅተዋል፣ በአንድ ሰዐት ልዩነት ሁሉም ስለ ቦረና ድርቅ ፅፈዋል። ቢዘገይም መልካም አካሄድ ነው!

እንደ ሐረሪ ክልል ሁሉም ክልልሎች፣ የፌደራል መስሪያ ቤቶች፣ መላው ዜጋ እንዲሁም ዲያስፖራው ጭምር ሊረባረብ ይገባል። ከእልቂት በኋላ ከንፈር መምጠጥ ዋጋ የለውም።

ድርቁ እያስከተለ ያለው ጉዳት እጅግ ሰፊ እና አስከፊ ነው። በዚህ ዙርያ የበለጠ ማንቂያ እንዲሆን የአካባቢውን አርብቶ አደሮች፣ የመንግስት ሀላፊዎች እና የጤና ባለሙያዎች በማናገር ሰፋ ያለ መረጃ ይዤ ነገ እመለሳለሁ።

መልካም ምሽት።

@EliasMeseret
25.0K views17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 14:56:46
የቀድሞ የስራ ባልደረባዬ ኬንያዊው ቶም ኦዱላ በሀገሪቱ የሻይ ቅጠል አምራች ኢንደስትሪ ዙርያ ያለውን ቅሌት ለቢቢሲ በሰራው ዶክመንታሪ ከሶስት ቀን በፊት አጋልጦ ነበር (ዶክመንተሪውን ለመመልከት:

)

ይህን ተከትሎ የኬንያ መንግስት በዘገባው ላይ የተነሱት ጉዳዮች እጅግ እንዳሳሰቡት ገልፆ በአስቸኳይ ምርመራ እንደሚያደርግ፣ የችግሩን ፈጣሪዎች ለህግ እንደሚያቀርብ እና ፖሊስ በአስቸኳይ ምርመራ እንዲጀምር ትዕዛዝ እንደሰጠ አስታውቋል (ደብዳቤው ተያይዟል)።

እኛ ጋር ቢሆን ኖሮስ?

ከጠላት ጋር በመተባበር ሀገርን ለማፍረስ፣ ሆን ተብሎ ኢኮኖሚውን ለማዳከም፣ የሌሎች ሀገራትን ተልዕኮ ተቀብሎ በመስራት... ወዘተ ተብሎ እንዲወገዝ እንዲሁም ስራ እንዲያቆም ይደረጋል።

ለምሳሌ: የዛሬ አራት አመት ገደማ በኢትዮጵያ ኢንደስትሪ ፓርኮች ውስጥ በሚሰሩ ዜጎቻችን ላይ በተለይ የቻይና ኩባንያዎች የሚያደርሱትን የመብት ጥሰት፣ ማስገደድ እና የስነ ልቦና እና የአካል ጉዳት በዚህ እኔ በተሳተፍኩበት ዘገባ ከዳሰስን በሗላ "የሀገሪቱን የኢንደስትሪ ሰላም በማናጋት..." በሚል ክስ የውጭ ሚድያ መታወቂያዬ እንዲቀማ ሁለት የመንግስት መስሪያ ቤቶች ደብዳቤ አውጥተውብኝ ነበር: https://apnews.com/article/149dd4d7ba8642d6abeb8f765cda8a9a ቆይቶ አቶ አህመድ ሽዴ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ሲሆኑ ደብዳቤዎቹን ወደ ጎን በማለት ስራዬን እንድቀጥል አስደርገው ነበር።

ልዩነቱ ግልፅ ነው!

@EliasMeseret
27.0K viewsedited  11:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 09:55:30
#ትኩረት ተሰምቶ እንጂ ታይቶ የማይታወቅ ድርቅ፣ ረሀብ እና ቸነፈር በበርካታ ስፍራዎች ተከስቷል። ጉዳዩ በሚመለከታቸው ችላ ቢባልም (ለዜና ሽፋን እንኳን ባይበቃም) ክስተቱ የሚልዮኖች እንስሳቶችን እና በአንዳንድ ስፍራዎች ደግሞ የሰው ህይወት እስቀመቅጠፍ እየደረሰ እንደሆነ ታውቋል።

ይህ አሳዛኝ ክስተት እንደ ቦረና ባሉ ለአምስት ተከታታይ አመታት ዝናብ ባላገኙ አካባቢዎች የከፋ ሆኗል። የቦረና ዞን አስተዳደር 800,000 ገደማ ነዋሪዎች አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ገልፀዋል።

የእርዳታ ድርጅቶች 22.6 ሚልዮን ዜጎቻችን የምግብ እጥረት እንዳጋጠማቸው፣ 11.8 ሚልዮኑ ከፍ ያለ ስጋት ውስጥ እንደሚገኙ እንዲሁም በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ቢያንስ ለመጪዎቹ አስር ወራት በዚህ ሁኔታ እንደሚቀጥሉ እና ከፍ ያለ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል እያሳሰቡ ይገኛሉ።

"ከ110 ሚልዮን ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት ስለተገኘ ወደ ውጭ ኤክስፖርት ሊደረግ ነው" የሚለው ሀሳብ ይህን ሲሰማ ምን ይሰማው ይሆን?

ለማንኛውም፣ ሁላችንም የተቻለንን ርብርብ ለማድረግ እንዘጋጅ፣ በቅርቡ የድጋፍ ማሰባሰብ ዘመቻ እንጀምራለን።

File Elias Meseret

@EliasMeseret
24.2K viewsedited  06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 17:18:06
#የመጽሐፍምረቃ በሰብአዊ መብቶች ትግል ውስጥ ከሁለት አሥርት አመታት በላይ ያሳለፈው አቶ ያሬድ ሐይለማርያም የገጠሙትን ውጣ ውረዶች እና ሌሎች ከዚህ በፊት ያላካፈላቸውን ገጠመኞቹን እና በርካታ ትውስታዎቹን የከተበበትን ባለ 392 ገጽ መጽሐፍ የካቲት 24 ቀን 2015 ከቀኑ 10፡00 እስከ ምሽቱ 1:30 ድረስ በጊዮን ሆቴል ግሮቭ ጋርደን መናፈሻ ያስመርቃል።

በዕለቱ መጽሐፉን ቀድመው አንብበው የግምገማ ሃሳባቸውን የሚያቀርቡ ሦስት እንግዶችም ተጋብዘዋል። ዶ/ር ዳዲሞስ ኃይሌ፣ አንጋፋው ጋዜጠኛ መለስካቸው አመሃ እና የስጽነ-ሥሑፍ መምህርና አንጋፋ ገጣሚው ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ በመድረኩ ላይ ይሰየማሉ።

በተጠቀሰው ቀን፣ ሰዓትና ስፍራ ተገኝተው የመጽሐፍ ምረቃው ታዳሚ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል።
24.3K views14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 11:46:53
ከዛሬ ሶስት እና አራት አመት በፊት የመንግስት ሚድያዎች እንዲህ ምስሎችን ቀባ ቀባ አርገው ዜና ይሰሩ ነበር፣ የሆነ ሰሞንማ የሆነ ሳተላይትን ቀብተው አቅርበው ነበር።

እድሜ ለኢትዮጵያ ቼክ (https://www.facebook.com/EthiopiaCheck) ህዝቤ አሁን በ reverse image search ራሱ ምስሎችን ማጣራት ለምዶ እሳት ሲሆን እርግፍ አርገው ተዉት። ችግር በቅቤ ያስበላል አንደሚባለው...

@EliasMeseret
24.8K viewsedited  08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 20:36:51 "Being an Ethiopian የአንተ ፔጅ ነው አይደል?"

የኔ አይደለም፣ ማን እንደሚዘውረውም አላውቅም፣ ግን አሪፍ ፔጅ ነው።

https://www.facebook.com/actlikeethiopian?mibextid=ZbWKwL
25.4K viewsedited  17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 16:04:49 አንድ አመት ከግማሽ ለተዘጋ ፔንሲዮን "17 ሚልዮን ብር ታክስ ክፈሉ።"

ስሙን የማልጠቅሰው ይህ ትንሽ ፔንሲዮን የዛሬ አመት ተኩል ገደማ በፀጥታ ሀይሎች እንዲዘጋ ይደረጋል፣ ምክንያት በወቅቱ አልተሰጠም።

የትግራይ ተወላጅ ከሆኑት ባለቤቶቹ አንደኛዋ ወደ መቐለ ሄዳ መንገድ ሲዘጋ መመለስ ሳትችል ቀረች፣ በመሀል ቤቱ አንድ ንብረት ሳይተርፈው በለሊት ተዘረፈ። ታድያ ይህን ለፖሊስ ሪፖርት ሊያደርግ የሄደ ወንድም "ቤቱን ያስዘረፍከው አንተ ነህ" ተብሎ ለእስር ተዳረገ።

ያ ሁሉ አልፎ ሰሞኑን መንገድ ሲከፈት ከመቐለ የተመለሰችው አንደኛዋ ባለቤት ቤቱን ልታስከፍት ስትሄድ "ለታክስ 17 ሚልዮን ብር ክፈሉ፣ ከዛ ውጭ መክፈት አይቻልም" የሚል መልስ አግኝተዋል።

መቼም ብሄር እየተቆጠረ ባለፈው ሁለት አመት ሲደረግ የነበረ ግፍ (አንዳንዱን ሪፖርት የሰራሁበት፣ ሌላው አዝኜ ያለፍኩበት) እጅግ፣ እጅግ፣ እጅግ ብዙ ነው።

- ራይድ የሚሰራበትን መኪና በጠራራ ፀሀይ ተቀምቶ የጓደኛ እና ዘመድ መፅዋት ጠባቂ የሆነ

- ቤት ውስጥ ያለ ጌጣጌጥ እና ኤሌክትሮኒክስ በለሊት ተጭኖ የተወሰደበት

- በጥቆማ ነው የመጣነው እየተባለ ብር ስጡን አልያም ትታሰራላችሁ እየተባለ በየመንደሩ የነበረ ድርድር

- ከፍ ሲል ከእስር እንድንከላከላችሁ ከድርጅታችሁ የተወሰነ ሼር ወይም ድርሻ ስጡን የሚል

- ዝቅ ሲል ደግሞ ምግብ በልቶ "ለእናንተ አልከፍልም" ብሎ የሚወጣ

- ባንክ ውስጥ ያስቀመጠው ገንዘብ በሙሉ ተወስዶበት ባዶ አካውንት ያገኘ... ወዘተ

እውነታው የሚመረው ሊኖር ይችላል፣ ይህ ግን ባለፈው ሁለት አመት አልፈንበት የመጣነው ጭራቅ የሆነ ግዜ ነበር። "ጁንታ" የሚል አይጠፋም 'አ?

@EliasMeseret
25.6K views13:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 15:28:16
በስንዴ እጥረት ምክንያት የዱቄት ፋብሪካዎች ስራ እያቆሙ ነው ተባለ

(Via Ethio FM)

የፓስታና መኮሮኒ አምራች ፋብሪካዎች የስንዴ ምርት እጥረት ገጥሞናል፤ በዚህም ስራ ለማቆም ተገደናል እያሉ እንደሚገኙ ኢትዮ ኤፍኤም ዛሬ ዘግቧል።

የዱቄትና የዱቄት ውጤቶች አምራቾች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ሙሉነህ ለማ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት ስንዴ በአሁኑ ወቅት ኮንትሮባንድ ሆኗል፤ ማንም እንደፈለገ መግዛትም ሆነ መሸጥ አይችልም ብለዋል፡፡

መንግስት ለኤክስፖርት የሚሆን ስንዴን ለማግኘት ሲል ዩኒዮኖች ብቻ እንዲገዙ ፈቀደ፣ ለዱቄት አምራቾችም በዩኒዮኖች በኩል ታገኛላችሁ ተባሉ፣ በኋላም 12 ባለሃብቶች ተመርጠው ወደ ስራ ገቡ፣ ዱቄት አምራቾች ግን ስንዴ ሊያገኙ አልቻሉም ብለዋል፡፡

ይህ ችግር ከተፈጠረ 2 ወራትን አስቆጥሯል የሚሉት አቶ ሙሉነህ አምራቾች በእጃቸው ያለችውን ስንዴ እየቆጠቡ ሲጠቀሙ ቆይተው አሁን ላይ ስራ ማቆም ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህም በዳቦ ላይ የሚስተዋለው ጭማሬ እንዳለ ሆኖ የ1 ኪሎ መኮሮኒ ዋጋ ከ40 ብር ወደ 80 ብር ከፍ እንዲል አድርጎታል ነው የተባለው፡፡

እንደ አቶ ሙሉነህ ገለጻ በአሁኑ ወቅት ስንዴ እንደ ኮንትሮባንድ ተቆጥሮ በየኬላዎች በፍተሻ እየተያዘ ነው፡፡ በዚህም አምራቾች ገዝተው መተቀም አይችሉም፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች መጋዘን ላይ ስንዴ የተገኘባቸው ዱቄት ፋብሪካዎችም ሆነ ነጋዴዎች በህገ ወጥ መንገድ ግብይት ፈጽማችኋል በሚል ወከባ እየደረሰባቸው እንደሚገኝም አንስተዋል፡፡

በመሆኑም ከሁሉም በፊት የሃገር ውስጥ ፍላጎትን ማሟላት ይቀድማልና ችግሩን ለመፍታት መንግስት ትኩረት እንዲሰጥ አቶ ሙሉነህ ጠይቀዋል፡፡

@EliasMeseret
24.4K views12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 21:35:41
#UPDATE በ3.8 ቢሊየን ብር ወጪ ግዢ ስለተፈፀመባቸው 200 ባሶች እና አነጋጋሪ ዋጋቸው ከአራት ቀን በፊት አንድ መረጃ አጋርቼ ነበር፣ በዚህ ዙርያ ማብራርያ ሊሰጥ እንደሚገባም ሀሳብ ሰንዝሬ ነበር።

ለማስታወስ ያህል: ከላይ በተጠቀሰው ስሌት መሰረት አንዱ አውቶቡስ የተገዛው 19 ሚልዮን ብር (ወይም 354,000 ዶላር ገደማ) እንደሆነ፣ ነገር ግን እኔ በግሌ ሁለት የቻይና መኪና አቅራቢ ድርጅቶችን አናግሬ ዋጋቸው ከ111,000- 130,000 ዶላር ገደማ እንደሆነ እንዳሳወቁኝ ፅፌ ነበር።

በዚህ ዙርያ ዛሬ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ምትኩ አስማረ ጉዳዩን ያስረዳሉ ያሏቸውን ነጥቦች በስፋት አብራርተውልኛል። አቶ ምትኩ ያነሱልኝን ነጥቦች ሳልጨምር፣ ሳልቀንስ አቅርቤው አንባቢ የራሱን ግንዛቤ ይውሰድ:

- በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በኩል የ200 ባስ ግዥ ተፈፅሟል። የ200 ባስ ግዥ ጨረታ ሰነዱ የቀረበው የተለያዩ ወጭዎችን ሸፍኖ ማለትም የዉጭ መንዛሬም ሆነ ለሎች ነገሮችን አጠቃሎ በአድራሻችን ማቅረብ ነበር።

- ለዚህ ግዢ ያደታ ጁነይዲ (የ Higer Bus አቅራቢው) በአነስተኛ ዋጋ አሸንፏል፣ ዋጋውም ወደ 18.9 ሚልዮን ብር ገደማ ነበር። ሁለተኛ የሆነው ድርጅት ያቀረበው 22 ሚልዮን ብር ገደማ ነበር። ይህ ግዢ በአመት ለድጋፍ ሰጪ ባሶች ከከተማ አስተዳደሩ የሚከፈለውን 600 ሚልዮን ብር አስቀርቶ ወደፊት ሌሎች ባሶችን ለመግዛት ታሳቢ ያረገ ነበር።

ዋጋው ከአውቶብሱ የታች መሸጫ ዋጋ (base price) ለምን እጅግ ከፍ ያለ ሆነ የሚለውን ጥያቄዬን ሲያብራሩ:

1ኛ: የውጭ ምንዛሬ እጥረት ስላለ አውቶብሶቹ የተገዙት በውጭ ምንዛሬ ሳይሆን በብር ነበር (አቅራቢው ድርጅት ዶላር በራሱ አቅርቦ)። ያናገርናቸው አንዳንድ የቻይና ኩባንያዎች ጭራሽ በዶላር እንጂ በብር ግብይት አንፈፅም ብለዋል።

2ኛ: አውቶብሶቹ የተገዙት በቀጥታ ከፋብሪካው/አምራቹ ሳይሆን ከመኪና አቅራቢ ድርጅት፣ ይህም መሀል ላይ ያለ የድርጅት ትርፍን ታሳቢ ያደረገ ነበር።

3ኛ: አውቶብሶቹ በተለያየ ማዘመኛ ስፔክ (specifications) የተገጠመላቸው ናቸው። ከቻሲስ ስር ያሉ ዋና ዋና ክፍሎቹ ከጀርመን በመጡ ምርቶች እንዲደረጉ አስደርገናል፣ ይህም ዋጋው ላይ ጭማሬ አስከትሏል።

4ኛ: እንደ ሱር ታክስ፣ ዊዝሆልዲንግ እና ቫት ያሉ ቀረጦች ተጨምረውበታል፣ ይህም ወደ 30 ፐርሰን ይደርሳል። ግዢው በዚህ መልኩ ቢፈፀምም ወደፊት እኛ ከገንዘብ ሚኒስቴር ይህንን መልሰን እንጠይቃለን (ወደኋላ ተመላሽ ይሆናል)።

5ኛ: ከዛም የማስጫኛ፣ የወደብ ክፍያ፣ ኢንሹራንስ፣ ዲመሬጅ... ወዘተ ክፍያዎች ነበሩበት።
-------------------------------------------------------------

*እንደ ማንኛውም የሚድያ ስራ ሁሉንም ባላንስ ማረግ እና እኩል ቦታ መስጠት ተገቢነት እንዳለው አምናለሁ። በመግቢያው እንዳልኩት አንባቢዎች የራሳቸውን ንፅፅር አድርገው ግንዛቤ ይውሰዱ፣ በዚህ ገለፃ ለእኔ አንዳንድ መልሶችን ባገኝም አሁንም ያልተመለሱልኝ ጥያቄዎች እንዳሉ አሉ። ጉዳዩን ለኔ ለማስረዳት ርቀት ለሄዱት የአዲስ አበባ ኮሚኒኬሽን ቢሮ እና የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ግን ምስጋና

መልካም ምሽት!

@EliasMeseret
24.8K views18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ