Get Mystery Box with random crypto!

እለታዊ ዜና

የቴሌግራም ቻናል አርማ eletawizena — እለታዊ ዜና
የቴሌግራም ቻናል አርማ eletawizena — እለታዊ ዜና
የሰርጥ አድራሻ: @eletawizena
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.10K

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-04-27 07:59:26 ጥፍረ መጥምጥ፡ “ጥፍሬን ስለማፍርበት እደብቀዋለሁ”
https://www.bbc.com/amharic/articles/ckmz8kzzjvyo?at_medium=RSS&at_campaign=KARANGA

የጥፍር ፈንገስ ዓይነት አለው የሚሉት ዶ/ር ባሸና፣ ጥፍር ከተወጋ ወይንም ችግር ከገጠመው ለፈንገስ ጥቃት አመቺ ሁኔታን ስለሚፈጥር የፈንገስ ኢንፌክሽን ሊፈጥር እንደሚችል ይገልጻሉ።
6 views04:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 07:58:26 በሺዎች የሚቆጠሩ ከ20 በላይ አገራት ዜጎች ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸው ተነገረ
https://www.bbc.com/amharic/articles/c6pe767l6pdo?at_medium=RSS&at_campaign=KARANGA

ሁለት ሳምንት ሊሞላው የተቃረበውን በሱዳን ውስጥ የተከሰተውን ወታደራዊ ግጭትን በመሸሽ በሺዎች የሚቆጠሩ የተለያዩ አገር ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸው ተገለጸ። የተለያዩ ወታደራዊ ኃይሎችን በሚመሩት በሁለቱ የሱዳን ኃያላን ጄኔራሎች መካከል በተፈጠረው የሥልጣን ፉክክር ምክንያት በተቀሰቀሰ ግጭት ሳቢያ አገሪቱ ከባድ ግጭት ውስጥ ገብታለች። አስካሁን ከ20 አገራት በላይ ዜግነት ያላቸው ሰዎች በመተማ ዮሐንስ በኩል ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸው ተገልጿ።
6 views04:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 02:23:22 የእነረዳት ፕር. ሲሳይ አውግቼው የዋስትና ጉዳይ ለብይን ተቀጠረ
https://amharic.voanews.com/a/7067730.html

“ሀገራዊ ሁከት እና ብጥብጥ በመፍጠር፣ እንዲሁም ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትን በኃይል ለመናድ በመንቀሳቀስ ወንጀል ጠርጥሪያቸዋለኹ፤” በማለት፣ ፖሊስ፣ በረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቼው ሥር የክሥ መዝገብ የከፈተባቸው አምስት ግለሰቦች፣ ዛሬ ረቡዕ፣ ሚያዝያ 18 ቀን 2015 ዓ.ም. የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል፡፡

በክሥ መዝገቡ ጉዳያቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙቱ አምስቱ ግለሰቦች፥ በመምህርነት፣ በበጎ አድራጎት አገልግሎት እና በግል ሥራ ላይ ተሠማርተው የሚገኙት፥ ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቼው፣ ፕሮፌሰር ማዕርጉ ቢያበይን፣ ኄኖክ ዐዲሱ፣ ሰሎሞን ልመንህ፣ እንዲሁም የባልደራስ ምክትል ፕሬዚዳንት የኾኑት አቶ አምኃ ዳኘው ሲኾኑ፣ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ከተገለጸ ወዲህ ዛሬ ችሎት የቀረቡት ለሦስተኛ ጊዜ ነው፡፡

ፖሊስ በፍርድ ቤት በተፈቀደለት ያለፉት ስምንት ቀናት፣ አከናወንኹ ያላቸውን የምርመራ ሥራዎች ለችሎቱ አቅርቦ፣ ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀን እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው፣ ለፖሊስ ተጨማሪ ቀን ሊሰጥ አይገባም፤ ብለው መከራከራቸውን፣ ከጠበቆቻቸው አንዱ ሰሎሞን ገዛኽኝ ተናግረዋል፡፡

ፖሊስ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው፣ “የባንክ ቤት ማስረጃዎችንና የኤሌክትሮኒክስ ውጤት ማስመጣት” የሚሉ ጉዳዮች በምክንያትነት ካቀረባቸው ውስጥ እንደሚገኙበት ገልጸዋል፡፡ ጠበቆች በበኩላቸው፣ እነዚኽ መረጃዎች፣ ከመንግሥት ተቋማት የሚመጡ በመኾናቸው፣ ተጠርጣሪዎቹ በዋስ ቢፈቱ ሊያሳድሩ የሚችሉት ምንም ዐይነት ተጽዕኖ እንደማይኖር ጠቅሰው መከራከራቸውን ጠቁመዋል፡፡




በፖሊስ የቀረበው ሌላው መከራከሪያ፣ “ተጠርጣሪዎቹ በዐማራ ክልል አሥነስተዋል” ባለው ሁከት ምክንያት የደረሰውን ጉዳት ለመመርመር፣ “የምርመራ ቡድን ልከን ውጤቱ እስኪመጣ ድረስ” በእስር ላይ እንዲቆዩ የሚጠይቅ ነው፡፡ የተከሣሽ ጠበቆችም፣ “በዐማራ ክልል ሁከት የተነሣው ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ ነው፤ በመኾኑም፣ ይህ ጉዳይ ዋስትና ሊያስከለክላቸው አይገባም፤” ብለው ተከራክረዋል፡፡

የግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጠው ፍርድ ቤቱ፣ የፖሊስን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ፣ በዋስትናው ጉዳይ ብይን ለመስጠት፣ ለፊታችን ዓርብ ሚያዝያ 20 ቀን 2015 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡




ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በተመሳሳይ ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የዩቲዩብ እና ሌሎች ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ ባለሞያዎች ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው፣ ከ10 ቀን የጊዜ ቀጠሮ በኋላ ትላንት ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው፣ እያንዳንዳቸው በ20 ሺሕ ብር ዋስ እንዲፈቱ ተወስኗል፡፡ ይኹን እንጂ ጠበቃ ሰሎሞን እንዳሉት፣ የዋስትናው ክፍያ ተከፍሎ የመፍቻ ትዕዛዝ ለፖሊስ ጣቢያ ከቀረበ በኋላ፣ ፖሊስ በችሎቱ ውሳኔ መሠረት ሳይለቃቸው፣ ዛሬ ይግባኝ ጠይቋል፡፡

ፖሊስ፣ ለፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ላቀረበው ይግባኝ፣ ነገ ምላሽ እንደሚሰጡና ከሰዓት በኋላ ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን እንደሚያሳውቅም ጠበቃው ጠቁመዋል፡፡ “ኢትዮ ንቃት” በተሰኘ የዩቲዩብ ማኅበራዊ መገናኛ አዘጋጅ፣ ፖለቲካዊ ትንታኔዎችን በመስጠት የምትታወቀው መስከረም አበራ ደግሞ፣ ከትላንት በስቲያ፣ ሚያዝያ 16 ቀን ችሎት ቀርባ፣ ለፖሊስ ተጨማሪ 10 ቀን እንደተፈቀደለት ለማወቅ ተችሏል፡፡
28 views23:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 02:22:22 የእነረዳት ፕር. ሲሳይ አውግቼው የዋስትና ጉዳይ ለብይን ተቀጠረ
https://amharic.voanews.com/a/7067732.html

“ሀገራዊ ሁከት እና ብጥብጥ በመፍጠር፣ እንዲሁም ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትን በኃይል ለመናድ በመንቀሳቀስ ወንጀል ጠርጥሪያቸዋለኹ፤” በማለት፣ ፖሊስ፣ በረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቼው ሥር የክሥ መዝገብ የከፈተባቸው አምስት ግለሰቦች፣ ዛሬ ረቡዕ፣ ሚያዝያ 18 ቀን 2015 ዓ.ም. የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል፡፡
25 views23:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 02:21:22 የታንዛኒያው የሰላም ንግግር በቅድመ ድርድር ጉዳዮች ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ
https://amharic.voanews.com/a/7067628.html

በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል በታንዛኒያ ይደረጋል የተባለው የሰላም ድርድር፣ ትላንት ሚያዝያ 17 ቀን 2015 ዓ.ም. እንደሚጀመር፣ ሁለቱም አካላት ያረጋገጡ ቢኾንም፣ ድርድሩ በርግጥም ስለመጀመር አለመጀመሩ እስከ አሁን በይፋ የታወቀ ነገር የለም፡፡

በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የፖለቲካ፣ ሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮች ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዴኦዬ፣ ኅብረቱ በአፍሪካ ሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ የሚያከናውናቸውን ተግባራት በተመለከተ፣ ዛሬ በበይነ መረብ ለጋዜጠኞች መግለጫ በሰጡበት ወቅት፣ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል፣ በታንዛኒያ ይደረጋል የተባለው ድርድር ተጀምሮ እንደኾነና ሒደቱ በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ፣ ከአሜሪካ ድምፅ ጥያቄ ቢቀርብላቸውም፣ ቀጥተኛ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡


ኾኖም ኮሚሽነሩ፣ ለጥያቄው በሰጡት አስተያየት፣ ችግሩን በሰላም ድርድር ለመፍታት የተጀመረው ጥረት የሚደነቅ እንደኾነ ገልጸዋል፡፡ “ግባችን እ.አ.አ. በ2030 የመሣሪያ ድምፆችን ኹሉ ዝም ማሰኘትና ኹሉም ግጭቶች እንዲቆሙ ማድረግ ነው፤” ያሉት ኮሚሽነሩ፣ “ስለዚኽ በኢትዮጵያም ይኹን በሌላ ማንኛውም የኅብረቱ አባል ሀገር፣ ለሕዝቦቻችን ጥቅም ሲባል፣ እንዲሁም ዐቅማችንን ሁሉ የምንፈልጋትን አፍሪካ እውን በማድረግ ተግባር ላይ ማዋል ይቻል ዘንድ፣ ግጭቶችን ለመፍታት የሚወሰዱ ርምጃዎች የሚደነቁ ናቸው፤” ብለዋል፡፡

ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው አፍሪካ ተምሳሌት እንደኾነ የጠቀሱት የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት፣ በሀገሪቱ ለሚንቀሳቀሱ ሌሎች ታጣቂ ቡድኖች መነሣሣትን እንደሚፈጥር ኮሚሽነሩ ገልጸዋል፡፡ “የፕሪቶሪያው ስምምነት ተኣምራዊ ስምምነት እየተባለ ነው፡፡ ምክንያቱም፣ ላለፉት ስድስት ወራት ምንም ዐይነት ጥይት አልተተኮሰም፡፡ በመኾኑም ስምምነቱ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ሌሎች ታጣቂ ቡድኖች ትልቅ መነሣሣት ይኾናል ብዬ አምናለኹ፤” ሲሉም ተናግረዋል።




የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቃል አቀባይ ኑር መሐሙድ ሼኽ ደግሞ፣ በጽሑፍ በሰጡን አጭር ምላሽ፣ “እኛ የምናውቀው ንግግሩን የመጀመሩ ሒደት የላቀ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ንግግሮቹ በታንዛኒያ እንደሚደረጉ ነው፤” ብለዋል፡፡ “ሒደቱ በኢትዮጵያውያን ባለቤትነት የሚመራ ነው፤” ሲሉ በጽሑፋቸው ገልጸዋል።

የኢጋድ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ፣ ስለ ኹኔታው “ጥሩ ግንዛቤ” እንዳላቸውና “በፓርቲዎቹ ከተፈለጉ ድጋፍ ለማድረግ” እንደተዘጋጁ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት እና የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት፣ በታንዛኒያ እንደሚነጋገሩ ከመታወቁ ባለፈ፣ ተደራዳሪ ወገኖች በማን እንደሚወከሉ፣ ስለ አደራዳሪዎች ማንነት፣ እንዲሁም ስለ ድርድሩ ሒደት፣ መንግሥት እና ታጣቂው ቡድኑም ኾኑ የታንዛንያ ባለሥልጣናት፣ ዝርዝር ጉዳዮችን ከመግለጽ መቆጠባቸውን ሮይተርስ አመልክቷል።

የአሜሪካ ድምፅ፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል፣ አስተያየት ለማግኘት በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ አልተሳካም፡፡

በአሶሺየትድ ፕሬስ የተጠቀሱት የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ቃል አቀባይ ኦዳ ተርቢ ግን፣ “ለዋናው ድርድር መንገድ የሚጠርግ” ያሉት “የመጀመሪያ ውይይት መጀመሩን” ጠቅሰዋል፡፡ "የአሁኑ ንግግር ትኩረት፥ መተማመንን መፍጠር እና አቋሞችን ግልጽ ማድረግ ነው፤" ማለታቸውን፣ እንዲሁም ኖርዌይ እና ኬንያ፣ በዚኽ ሳምንት የሚደረገውን ንግግርም እንደሚያሸማግሉ መግለጻቸውን አሶሺየትድ ፕሬስ በዘገባው ጠቅሷል፡፡

በታንዛኒያዋ የዛንዚባር ደሴት በሚካሔደው ድርድር የኢትዮጵያን መንግሥት በመወከል ከሚሳተፉት መካከል፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሑሴንና የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዴዎን ጢሞቴዎስ እንደሚገኙበት፣ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ሁለት ምንጮች ለሮይተርስ ተናግረዋል፡፡ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ተወካዮችን ማንነት በተመለከተ ግን፣ እስከ አሁን በዘገባዎች አልተጠቀሰም፡፡




/ሙሉ ዘገባውን በድምፅ ለማድመጥ የተያያዘውን ፋይል ይጫኑ/ 
23 views23:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 02:20:22 ሐሙስ፡-ጋቢና VOA
https://av.voanews.com/clips/VAM/2023/04/26/20230426-213000-VAM131-program_original.mp3

Gabina VOA is designed to be an infotainment youth radio show broadcasting to Ethiopia and Eritrea in the Amharic language. The show brings varied perspectives on issues concerning young people in the Horn of Africa region. “Gabina” in the Amharic language is a front-row taxi ride.
21 views23:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 02:19:22 የታንዛኒያው የሰላም ንግግር በቅድመ ድርድር ጉዳዮች ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ
https://av.voanews.com/clips/VAM/2023/04/26/01000000-0aff-0242-3526-08db469c70ea_48k.mp3

በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል በታንዛኒያ ይደረጋል የተባለው የሰላም ድርድር፣ ትላንት ሚያዝያ 17 ቀን 2015 ዓ.ም. እንደሚጀመር፣ ሁለቱም አካላት ያረጋገጡ ቢኾንም፣ ድርድሩ በርግጥም ስለመጀመር አለመጀመሩ እስከ አሁን በይፋ የታወቀ ነገር የለም፡፡
21 views23:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 00:35:48 የመብት አቀንቃኙ ከያኒ ሀሪ ቤላፎንቴ ሲታወስ
https://amharic.voanews.com/a/harry-belafonte-obit-reax/7067557.html

ዝነኛው የሲቪል መብቶች ከበሬታ ተሟጋች፣ የፊልም ተዋናይ እና ድምጻዊ ሄሪ ቤላፎንቴ በተወለደ በ96 ዓመቱ አረፈ።


ፈር ቀዳጅ ተዋናይ እና ድምጻዊ በኋላም የመብት ከበሬታ እና የሰብዐዊነት ዕርዳታ ተሟጋቹ ሄሪ ቤላፎንቴ ትናንት ማክሰኞ ኒው ዮርክ በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በልብ ድካም ምክንያት ማረፉ ተሰምቷል።


ሄሪ ቤላፎንቴ ለሰብዐዊ መብት ከበሬታ ያለማሰለስ በቁርጠኝነት የታገለ ተሟጋች እና በኪነጥበብ ሥራዎቹም ለአያሌ ሽልማቶች የበቃ የፊልም ተዋናይ እና ድምጻዊ ነበር።


ዜና ዕረፍቱን ተከትሎ የሐዘን መግለጫ እየጎረፈ ነው፡፡ የፊልም ተዋናይቱ ኢቬት ኒኮል ብራውን “የድምጹን ነገር እንዲያው ዝም ነው፡፡ መልከ መልካም የሚያምር ሰውም ነበር፡፡ ልጆቹን በደምብ አሳድጓል፡፡ ዝናን ፈጽሞ ከቆመለት ዐላማ አያስቀድምም ነበር” ብላለች፡፡


በመዝናኛ ኢንዱስትሪው ውስጥ እጅግ ገናናው ጥቁር አሜሪካዊው ተዋናይ ታይለር ፔሪም ሄሪ ቤላፎንቴን በመብት ተከራካሪነቱ ባሳየው ጀግንነት አርአያዬ ነበር” ሲል አድንቆታል፡፡


ብዙ ሚሊዮን የሙዚቃ ቅጂዎች የተሸጡለት ዘፋኝ እና ተዋናይ የነበረው ሄሪ ቤላፎንቴ በኋላ የመዝናኛ ጥበብ ስራዎቹን ጋብ በማድረግ ያለማቋረጥ ጊዜውን ለሲቪል መብቶች እና ለሌሎችም የሰብዐዊነት ስራዎች ሰጥቷል።


የሲቪል መብቶች መሪው የማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር ጓደኛ የነበረው ቤላፎንቴ በፖለቲካ መድረኮች እና በጥበብ ባልደረቦቹ ዘንድ አዘውትሮ ይሟገትለት እንደነበር ይታወሳል።
26 views21:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 00:34:48 የሱዳን ግጭት በብሔራዊ የጤና ቤተ ሙከራ ደኅንነት ላይ ስጋት ደቅኗል
https://amharic.voanews.com/a/un-warns-of-lab-risk-amid-Sudan-conflict/7067574.html

በሱዳን ግጭት ውስጥ ከገቡት ወገኖች አንዱ፣ በዋና ከተማዋ ካርቱም የሚገኘውንና ለሥነ ሕይወት(ባዮሎጂካል) ምርምር የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን የያዘውን ብሔራዊ የጤና ቤተ ሙከራ መቆጣጠሩን፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባለሥልጣናት ያስታወቁ ሲኾን፣ ድርጊቱ “እጅግ አደገኛ” እንደኾነ በይነዋል፡፡ በግጭቱ ሳቢያ፣ ከሀገር የሚሰደዱ ሱዳናውያን ቁጥር እያሻቀበ መሔዱንም ተቋሙ አስታውቋል።


በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም የሚገኘው ብሔራዊ የጤና ቤተ ሙከራ፣ ትላንት ማክሰኞ፣ ከሱዳን ተዋጊዎች መካከል በአንዱ ቡድን ቁጥጥር ሥር መዋሉ ይፋ የተደረገው፥ በሁለቱ የሱዳን ተዋጊ ኃይሎች መካከል፣ አጣብቂኝ ውስጥ የሰነበቱ ሱዳናውያን፣ ከአካባቢው መሸሻቸውን እንደሚቀጥሉ ባለሥልጣናት እያስጠነቀቁ ባሉበት ወቅት ነው፡፡


ውጊያው ሱዳንን ወደ ትርምስ የከተታት ሲኾን፣ ቀድሞውንም በከፍተኛ ርዳታ የምትተዳደረውን አፍሪካዊት ሀገር ወደ ውድቀት አፋፍ አድርሷታል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መረጃ እንደሚያሳየው፣ ከግጭቱ በፊት፣ የሱዳን አንድ ሦስተኛ ሕዝብ ወይም 16 ሚሊየን የሚኾነው ወገን፣ ርዳታ ፈላጊ ነበር። አሁን ደግሞ ቁጥሩ ይጨምራል።


በሱዳን የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ዶክተር ኒማ ሰዒድ አቢድ፣ “ከተዋጊ ወገኖች አንዱ” ሲሉ የትኛው እንደኾነ በውል ያለዩት ቡድን፣ በካርቱም የሚገኘውን ማዕከላዊ የሕዝብ ጤና ቤተ ሙከራ መቆጣጠሩንና በውስጡ ይሠሩ የነበሩትን ባለሞያዎች(ቴክኒሺያኖች) ማስወጣታቸውን ገልጸዋል።


አቢድ፣ በጄኔቫ በተካሔደው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መግለጫ ላይ፣ ከፖርት ሱዳን በቪዲዮ ተገኝተው ስለ ኹኔታው ሲያብራሩ፣ “እጅግ፣ እጅግ አደገኛ ነው፤” ያሉ ሲኾን፣ በቤተ ሙከራው ውስጥ የፖሊዮ፣ የኩፍኝ እና የኮሌራ ቫይረስ እንደሚገኙ ገልጸዋል። አቢድ አክለውም፣ “ካርቱም የሚገኘው ማዕከላዊ የሕዝብ ጤና ቤተ ሙከራ፣ ከተፋላሚ ወገኖች በአንዱ መያዙ፣ አስከፊ የሥነ ሕይወት አደጋ ስጋት ደቅኗል፤” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።


ኹኔታውን አስመልክቶ፣ የዓለም ጤና ድርጅት በአወጣው መግለጫ፣ የቤተ ሙከራው ባለሞያዎች መባረራቸው እና በካርቱም የደረሰው የኃይል መቋረጥ፣ በቤተ ሙከራው ውስጥ ለሕክምና አገልግሎት ተብለው የተቀመጡትን የሥነ ሕይወት ቁሳቁሶች በአግባቡ መቆጣጠር እንደማይቻል የሚያሳይ መኾኑን አመልክቷል፡፡


ቤተ ሙከራው የሚገኝበት ማዕከላዊ ካርቱም፥ የሱዳን ብሔራዊ ጦር፣ ፈጥኖ ደራሽ ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች ከሚባሉትና በዳርፉር ግጭት በተፈጸመው አሠቃቂ ድርጊት መሳተፋቸው ከሚገለጸው የጃንጃዊድ ሚሊሺያዎች የተወጣጣው ቡድን ጋራ፣ ውጊያ ከሚያካሒድበት አቅራቢያ ነው።


ውጊያው ከተቀሰቀሰበት እ.አ.አ. ሚያዝያ 15 ቀን ጀምሮ፣ ቢያንስ 20 ሺሕ ሱዳናውያን ወደ ቻድ ተሰድደዋል። በሱዳን ይኖሩ የነበሩ አራት ሺሕ የሚኾኑ የደቡብ ሱዳን ስደተኞችም፣ ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር(ዩኤንኤችሲአር) ቃል አቀባይ ኦልጋ ሳራዶ ተናግረዋል።


የስደተኞች ቁጥር፣ ከዚኽም በላይ እንደሚያሻቅብ ያስጠነቀቁት ሳራዶ፣ ወደ ሌሎች አምስት የሱዳን አጎራባች ሀገሮች የተሰደዱ ሱዳናውያን አኀዝ እንደሌላቸው ገልጸዋል። ዩኤንኤችሲአር፣ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች፣ ከሱዳን ሸሽተው ግብጽ መግባታቸውን አመልክቷል።


የሱዳን እና የግብፅ ድንበር፣ ከሱዳን ለመውጣት የሚሞክሩ ሰዎችን በሚያመላልሱ አውቶቡሶች ተጨናንቋል፤ የሚሸሹ ሰዎችም ድንበሩን አቋርጠው ወደ ሱዳን ለመግባት ተሰልፈው ሲጠብቁ ይታያሉ። አሕመድ ኤልባድዌይ፥ ተሰልፈው ከሚጠብቁት ሰዎች መሀል ሲኾን፣ “ወደ ሱዳን ድንበር ከደረስኹ ከ14 ሰዓታት በላይ ኾኖኛል። ድንበሩ ከትላንት ምሽት ጀምሮ ተዘግቷል፡፡ ስለዚኽ መሻገር አልቻልንም። እዚኽ ምግብም ኾነ ውኃ የለም። እህል ከቀመስኹ ሁለት ቀን ኾኖኛል፤” ሲል ተናግሯል፡፡


ኤልባድዌይ አያይዞም፣ “ድንበሩ ማታ ማታ ይዘጋል። ጠዋት ብቻ ነው የሚከፈተው። አሁን ከጠዋቱ 2 ሰዓት ኾኗል፤ ነገር ግን እስከ አሁን አልተከፈተም። ድንበሩ እስኪከፈት እና ፓስፖርቴ ላይ ማኅተም ተደርጎበት እስክሻገር እየጠበቅኹ ነው፤” ሲል፣ ድንበሩ ተከፍቶ ወደ ግብጽ ለመሻገር ያለውን ጉጉት ገልጿል።


ግጭቱ፣ ተጨማሪ መፈናቀሎችን በሀገር ውስጥም በውጭም እንደሚያስከትል ያመለከቱት የዩኤንኤችሲአር ቃል አቀባይ፣ የውጭ መንግሥታት የኤምባሲ ሠራተኞቻቸውንና ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት እየተሯሯጡ ባሉበት ወቅት፣ ድርጅቱ ሥራውን ለማስፋፋት እና ለማጠናከር እየጣረ መኾኑን አመልክቷል።


ከ800 ሺሕ በላይ ደቡብ ሱዳናውያን ስደተኞች በሱዳን የሚኖሩ ሲኾኑ፣ ከእኒኽም ሩቡ በካርቱም ዋና ከተማ የሚገኙ በመኾናቸው፣ በግጭቱ ቀጥተኛ ተጎጂ ኾነዋል። በአጠቃላይ ሱዳን፣ 1ነጥብ1 ሚሊዮን ስደተኞችን የምታስተናግድ አገር ስትኾን፣ በብዛት ከዳርፉር የተፈናቀሉ 3ሚሊዮን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችም አሏት።


በተባበሩት መንግሥታት የሥነ ሕዝብ ፈንድ ድርጅት ምልከታ መሠረት፣ በሱዳን የሚካሔደው ግጭት፣ በመጪዎቹ ሳምንታት ውስጥ ይወልዳሉ ተብለው የሚጠበቁ 24 ሺሕ ሴቶችን ጨምሮ፣ በ10 ሺሕዎች የሚቆጠሩ ነፍሰ ጡር እናቶችን ያሰጋል።


በመላ አገሪቱ የሚገኙ 219ሺሕ ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ውጊያው፣ እየተካሔደ ባለበት ወቅት፣ ከቤታቸው ወጥተው ወደ ሆስፒታሎች እና ክሊኒኮች መሔድና አስቸኳይ ርዳታ ማግኘት አደገኛ እንደሚኾንባቸው ተቋሙ ጨምሮ ገልጿል።


በሱዳን፥ በርዳታ ሠራተኞች፣ በሰብአዊ ተቋማት እና በመጋዘኖቻቸው ላይ ጥቃት መድረሱን ተከትሎ፣ የዓለም ምግብ ፕሮግራምን ጨምሮ ሌሎች የረድኤት ተቋማትም በሱዳን ያደርጉት የነበረውን የርዳታ ሥራ ለማቆም ወይም ለመቀነስ ተገድደዋል፡፡


ከሚያዚያ 15 ቀን ወዲህ፣ ሦስት የዓለም ምግብ ድርጅት ሠራተኞችን ጨምሮ ቢያንስ አምስት የርዳታ ሠራተኞች ተገድለዋል።
25 views21:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 00:33:48 የኦሮሚያ ክልል የማኅበረሰብ ተወካዮች ለትግራይ የጦርነት ተጎጂዎች ድጋፍ አደረጉ
https://amharic.voanews.com/a/tigray-abbaa-gadaas/7067533.html

የኦሮሚያ ክልል የማኅበረሰብ ተወካዮች፣ በሰሜኑ ጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው የትግራይ ክልል ነዋሪዎች የሚውል 10ሺሕ ኩንታል የምግብ እህል ርዳታ፣ ለክልሉ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስረከቡ፡፡


ከኦሮሚያ ክልል የማኅበረሰብ አካላት የተውጣጡ አባገዳዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የሴቶች እና የወጣቶች ተወካዮች የተካተቱበት


ልኡክ፣ ከትላንት ሚያዝያ 17 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ቀናት፣ በመቐለ ከተማ ጉብኝት ያካሔዱ ሲኾን፣ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች እና ከመቐለ ከተማ ነዋሪዎች ተወካዮች ጋራ ተወያይተዋል፡፡


የማኅበረሰብ ተወካዮቹን ስለ ጉብኝታቸው ያመሰገኑት፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ፣ በመንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል የተጀመረው


ንግግር ውጤታማ ይኾን ዘንድ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡ ተመሳሳይ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት፣ ከሌሎች ጎረቤት ክልሎች ጋራም ለማካሔድ እንደሚሠሩ፣ ፕሬዝዳንቱ አክለው አመልክተዋል፡፡


ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡
26 views21:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ