Get Mystery Box with random crypto!

Tsegaye Demeke - Lawyer

የቴሌግራም ቻናል አርማ consultancy2012 — Tsegaye Demeke - Lawyer T
የቴሌግራም ቻናል አርማ consultancy2012 — Tsegaye Demeke - Lawyer
የሰርጥ አድራሻ: @consultancy2012
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.71K
የሰርጥ መግለጫ

Legal Service

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-23 21:56:54 #ሀ) በሸሪዓና በፍትሐብሔር ህጉ መሰረታዊ የፖሊሲ ሐሳብ ልዩነቶች የሸሪዓም ሆነ የፍትሐብሔር ህጉ የውርስ ደንቦች መሰረታዊ ግብ የሟችን ውርስ ለወራሾቹ ማስተላለፍ ቢሆኑም በይዘታቸው አንድ አንድ መሰረታዊ ልዩነቶች አሏቸው፡፡ ይህም ልዩነት ሁለቱ ህግጋት መካከል የተካተቱ የፖሊሲ ሀሳብ ልዩነት ነፀብራቅ ነው፡፡ ከልዩነቶቹ ጥቂቶቹን ስንመለከት፣
የፍትሐብሔር ሕጉ የሟች ወራሾች ከሟች በሀይማኖትና በእምነት መለየታቸው የወራሽነት መብታቸውን አያሳጣቸውም፡፡ በሌላ በኩል ሟች ሙስሊም ከሆነ የእስልምና ኃይማኖት ተከታይ ያልሆኑ ወራሻቹ በሟች ውርስ እንዳይሳተፉ የሸሪዓ የውርስ ደንቦች ይከለክላሉ፡፡
የፍትሐብሔር ህጉ የሟች ሴትና ወንድ ወራሾች በጾታቸው ምክንያት የተለያየ ድርሻ እንዲወስዱ አያስገድድም፡፡ በእኩል የዝምድና ደረጃ እስካላቸው ድረስ እኩል ድርሻ ያገኛሉ፡፡ በሸሪዓ የሟች ሴት ልጆች ከሟች ውርስ አንድ ሶስተኛ የሚሰጣቸው ሲሆን ወንዶች ሁለት ሶስተኛ ይወስዳሉ፡፡
በሸሪዓ ሚስት ባሏን የመውረስ መብት ያላትና ከባሏ ውርስ አንድ ስምንተኛ የማግኘት መብት ያላት ሲሆን በፍትሐብሔር ህግ መሰረት ሚስት ባሏን የመውረስ መብት የላትም፡፡
የኢትዮጵያ የፍትሐብሔር ህግ ሟች ከወራሾቹ አንዱን በኑዛዜ የመንቀል መብት ያለው መሆኑን የሚደነግግ ሲሆን በሸሪዓ ሟች ወራሾቹን በኑዛዜ የመንቀል መብት የለውም፡፡
በፍትሐብሔር ህጉ ሟች በኑዛዜ ንብረቱን ለሶስተኛ ወገን የማስተላለፍ መብት ያለው ሲሆን በሸሪዓ አንድ ሰው በኑዛዜ ሊያስተላልፍ የሚችለው የንብረቱን አንድ ሶስተኛ ብቻ ነው፡፡

#ለ) በአፈፃፀም የሚታዩ ችግሮች
በሁለቱ ህጐች መካከል ያሉት እነዚህ እና ሌሎች መሰረታዊ ልዩነቶች ሟች ሙስሊም በሆነ ጊዜና የሟች ወራሾች የሌላ ኃይማኖት ተከታይ ወይም ከጋብቻ ውጭ የተወለዱ በሆኑ ጊዜ ወይም ሟች በጠቅላላ የኑዛዜ ስጦታና ነጠላ የኑዛዜ ስጦታ ንብረቱን ባከፋፈለ ጊዜ በሸሪአ ተጠቃሚ የሚሆኑት ወራሾቹ በሸሪዓ መሠረት ውርሱ እንዲፈፀም ሌሎች ደግሞ በፍትሐብሔር ህጉ መሰረት ታይቶ እንዲወሰን በየበኩላቸው የወራሽነት ማረጋገጫ ለማግኘትና ውርሱን ለመካፈል ክስ የሚያቀርቡበትና የአንድ ሰው ውርስ ጎን በጎን በሁለት ፍርድ ቤቶች የሚታይበት ሁኔታ ያጋጥማል፡፡

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስት አንቀፅ 34 ንዑስ አንቀፅ 5 ይህንን ችግር ዘለቄታ መፍትሔ ለመስጠት ታስቦ የተደነገገ ሲሆን፣ ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ ይቻል ዘንድ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶችን ለማጠናከር አዋጅ ቁጥር 188/1992 ታውጇል፡፡ በተለያዩ ክልሎችም የክልል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማጠናከሪያ አዋጆች ታውጀዋል፡፡ እነዚህ የህግ ማዕቀፎች ከመውጣታቸው በፊት የነበሩ በርካታ ችግሮችን ለመፍታት እንዲረዱ የሚስተባበል ባይሆንም አሁንም ቢሆን፣
በህግ ማዕቀፎቹ ድንጋጌዎች ግልፅ አለመሆንና በአንድ አንድ ጉዳዮች ክፍተት ያለባቸው በመሆኑ የተነሳና
መደበኛው ፍርድ ቤት እና የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ህግን በመተርጎምና በማስፈፀም ሒደት የየራሳቸው ችግር ያለባቸው በመሆኑ
ሁለቱን የውርስ ህግጋት በማስፈፀም በኩል በርካታ ችግሮች እንደሚፈጠሩና ችግሮቹ ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አልፈው የህገመንግስት አጣሪ ጉባኤና የፌዴሬሽን ምክር ቤት የመነጋገሪያ አጀንዳ እየሆኑ መሆኑን አንድ አንድ ጉዳዮችን አንስቶ ማየት ይቻላል፡፡


በአጠቃላይ በአገራችን እየተሰራባቸው ያሉ በርካታ ባህላዊና ኃይማኖታዊ የአወራረስ ሥርዓቶች ከፍትሐብሔር ህጉ የአወራረስ ደንቦች ጋር ጎን በጎን ሥራ ላይ በሚውሉበት ጊዜ የሚከሰቱትን ችግሮች መሰረታዊ ባህሪ ችግሮቹ የሚፈቱበትን የህግ አግባብ በመረዳት ለተግባራዊ እንቅስቃሴ ዝግጁ ለመሆን ስልጠናዎች በአካባቢያችን ያሉትን ባህላዊ ኃይማኖታዊ የአወራረስ ሥርዓቶች መሰረታዊ ደንቦች እና የአፈፃፀም ሥርዓት ላይ ስልጣኖቹ በየአካባቢያቸው የዳሰሳ ጥናት በማድረግ በጥናቱ ግኝት ላይ የጋራ ውይይት እንዲያደርጉ ማድረግ የላቀ ጠቀሜታ ስላለው ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው ነጥብ ነው፡፡

በአሁኑ ግዜ በተጨባጭ ቢያንስ ሁለት ዓይነት የአወራረስ ስርአት (መደበኛና ሸሪዓ) በመኖሩ አንዳንድ ግዜ አንድ ጉዳይ በሁለቱም ስርአቶች የሚስተናገድበትና ግጭት የሚፈጠርበት ሁኔታ ይከሰታል። የሽሪዓ ፍርድ ቤቶችን ስልጣን የሚሰጠው አዋጅ ክፍተት ያለበት መሆኑን ከላይ ተመልክተናል። በመሆኑም ህጉ ዘርዘር ባለ ሁኔታ ተሻሽሎ ሊወጣ ይገባዋል። ህጉ እስኪሻሻል ግን የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ምንግዜም ግጭት ሊከሰት የሚችል መሆኑን በጠረጠሩ ጊዜ ጉዳዩን የማጣራትና በተከራካሪ ወገኖች መካከል ፈቃድ በሌለ ግዜ ጉዳዩን ወደ መደበኛው ፍርድ ቤት የመምራት ሃላፊነት ይኖርባቸዋል።
1.3K views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 21:56:54 ስለውርስ ህግ በጠቅላላውና የአወራረስ ስርዓት በኢትዮጵያ
========================

1. ስለ ውርስ ህግ በጠቅላላው
በዓለማችን እየተሠራባቸው ያሉ ዘመናዊ የውርስ ህግጋት በመሠረታዊነት ሶስት አይነት የአወራረስ ሥርዓቶችን የሚዘረዝሩ የውርስ ደንቦችን የያዙ ናቸው፡፡ እነርሡም፣
የሟች ውርስ ያለኑዛዜ ለሟች የሥጋና የጋብቻ ዘመዶች የሚፈፀሙበትን የአወራረስ ሥርዓት በዝርዝር የሚደነግጉ፣ ደንቦችን የያዙ (Rules of Intestate Succession)
የሟች ውርስ በሟች ኑዛዜ መሠረት የሚፈፀምበትን ሥርዓት የሚደነግጉ ደንቦች የያዙ (Rules of testate Succession)
የሟች ውርስ በሟች በክፊል ኑዛዜና በከፊል ያለኑዛዜ የሚፈፀምበትን ደንቦች የያዙ (Rules of partially intestate and partially Testate secession) ናቸው፡፡
በአጠቃላይ አሁን እየተሠራባቸው ያሉ የውርስ ህግጋት የሟች የሚንቀሣቀሥ እና የማይንቀሣቀሥ ንብረት ገንዘብና ከሌሎች ሰዎች የሚሰበሰብ ብድር ወይም ተከፋይ ገንዘብ የአክስዮን ድርሻና ሌሎች በሟች መሞት ምክንያት የማይቋረጡ የሟች መብትና ግዴታዎች ለሟች ወራሾች ቀልጣፋና ውጤታማ በሆነ መንገድ የሚተላለፍበትን የአወራረስ ሥርዓት የሚደነግጉ ናቸው፡፡


2. የአወራረስ ሥርዓት በኢትዮጵያ

ስለ ኢትዮጵያ የአወራረስ ስርዓትና ህግ ስናነሳ በአሁኑ ጊዜ የሚታየው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስት ፀድቆ ስራ ላይ ከዋለ በኋላ ያለውን የአወራረስ ስርዓት ነው፡፡
ህገ መንግስቱ የግል መብቶችን በተመለከተ የሚነሱ ክርክሮች በተከራካሪዎቹ ፈቃድ በባህላዊ ወይም ኃይማኖታዊ ፍርድ ቤት የመዳኘት መብትን በአንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 5 ደንግጓል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የክልል ምክር ቤት በህገ መንግስቱ አንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 5 መሠረት የሀይማኖት እና የባህል ፍርድ ቤቶችን ሊያቋቁሙ ወይም ዕውቅና ሊሰጡ እንደሚችሉ ከመደንገጉም በላይ ህገመንግስቱ ከመጽደቁ በፊት ዕውቅና አግኝተው ሲሰራባቸው የነበሩ የኃይማኖትና የባህል ፍርድ ቤቶች በህገመንግስቱ መሰረት በአንቀጽ 78 ንዑስ አንቀጽ 5 በግልጽ ደንግጓል፡፡ በዚህ መሰረት፣ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤት በአዋጅ ቁጥር 188/1992 መሠረት ተጠናክሮ ስራውን የቀጠለ ሲሆን ክልሎችን የክልል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶችን የማጠናከሪያ አዋጆችን በማወጅ ስራቸውን እንዲቀጥሉ አድርገዋል፡፡

ከዚህ አንፃር ስንመዝነው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስት ፀድቆ ሥራ ላይ ከዋለበት ነሐሴ 1 ቀን 1987 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ባህላዊና ልማዳዊ የአወራረስ ደንቦች፣ ሀይማኖታዊ የአወራረስ ደንቦች ህገ መንግስታዊ ዕውቅናና ጥበቃ አግኝተው ከፍታብሔር ህጉ የውርስ ህግ ድንጋጌዎች ጐን በጐን እየተተገበሩ ይገኛሉ፡፡ ስለዚህ አሁን ያለው የአወራረስ ስርዓቶች ስንመለከት ሁለት መሠረታዊ እና ልዩ ባህሪያት ያሉት ነው፡፡
የመጀመሪያው በእኩል ደረጃ ህገመንግስታዊ ዕውቅናና ጥበቃ በተሰጣቸው፣ 1)ባሕላዊና ልማዳዊ የውርስ አወራረስ ደንቦች 2)ሀይማኖታዊ የውርስ አወራረስ ደንቦች እና 3) በፍታብሔር ህጉ የተመለከቱት የተለያዩ አይነት ባህሪ እና ውጤት ያላቸው የአወራረስ ሥርአቶች በአገሪቱ ውስጥ ተግባራዊ እየሆኑ መሆናቸው ሲሆን፣
ሁለተኛው በሟች የውርስ አወራረስ ሒደት ሥርዓት ሲፈፀም የሚነሱ ክርክሮች ተፈፃሚነት ያላቸውን የአወራረስ ደንቦች የመምረጥ መብት ሙሉ በሙሉ የተከራካሪዎች መሆኑ ነው፡፡

እዚህ ላይ መታየት ያለበት ከተከራካሪዎቹ አንደኛው በልማዳዊ ወይም ሀይማኖታዊ የአወራረስ ደንቦች መሰረት ለመዳኘት ፈቃደኛ ካልሆነ ጉዳዩ በፍታብሔር ህጉ የውርስ ህግ ድንጋጌዎች መሰረት የሚፈፀም መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡- ስለሆነም ዜጐች የፍታብሔር ህጉን የውርስ ደንቦች ተፈፃሚነት የሚያስቀሩት ጉዳዩ በባህላዊ ወይም ኃይማኖታዊ የአወራረስ ደንብ እንዲፈፀም ሙሉ በሙሉ ሲስማሙና ፈቃደኛ ሲሆኑ ብቻ ነው፡፡

የተለያየ አይነትና ባሕሪያት ውጤት ያላቸው የውርስ አወራረስ ደንቦች መኖራቸው ያለው ጠንካራና ደካማ ጐን
ከላይ እንደተገለፀው በአገሪቱ አንድ ወጥ የሆነ የአወራረስ ሥርዓት ኖሮ የማያውቅ ሲሆን አንድና ወጥነት ያለው የአወራረስ ሥርዓት ለመዘርጋት የተደረገው ሙከራም ተግባራዊ ውጤት አላስገኘም፡፡ ይህም በመሆኑና ህገመንግስቱ ባህልን፣ ሃይማኖትን መሰረት ለሚያደርጉ የአወራረስ ደንቦች ዕውቅናና ጥበቃ ሰጥቷል፡፡ ይህም ዜጐች በፈቃዳቸውና በፍላጎታቸው የህብረተሰባቸው ባህላዊ የውርስ ደንቦች ወይም ኃይማኖታዊ የውርስ ድንጋጌዎች መሰረት የሟች ውርስ የሚያስፈፅሙበት እድል የሚሰጥ በመሆኑ፣ ዜጐች የግል ጉዳያቸው በመረጡት መንገድ የመጠየቅና የመዳኘት መብታቸውን ያረጋግጣል፡፡ ይህም ሊመሰገን የሚገባው ጠንካራ ጎን እንደሆነ ለመረዳት ይቻላል፡፡
በሌላ በኩል ከአንድ በላይ የሆኑ የውርስ አወራረስ ስርዓቶች በአንዲት አገር ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ ሲሞከር የአንዱ የአወራረስ ሥርዓት ደንቦች ከሌላው የሚለያዩበት ሰፊ ሁኔታ ስለሚኖርና ከሚች ወራሾች መካከል የተወሰኑትን በአንደኛው የአወራረስ ስርዓት ሌሎቹ ደግሞ በሌላ የአወራረስ ሥርዓት መሰረት የሟች ውርስ እንዲፈፀም ለማድረግ የየበኩላቸውን ጥያቄ ስለሚያቀርቡና በሌሎች ምክንያቶች የሚፈጠረው የተለያዩ የውርስ ደንቦችና የአፈፃፀም ግጭት ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮች አሉ፡፡ በኢትዮጵያ ተፈፃሚነት ያላቸው ባህላዊ የአወራረስ ሥርዓቶች ብዛታቸውን፣ ይዘታቸውን የሚያሳይ ወጥ ጥናት ባለመደረጉ በእርግጠኘነት ብዛታቸውን፣ ይዘታቸውንና የአፈፃፀም ሒደታቸውን ከሌሎች ኃይማኖታዊና የፍታብሔር ህግ የውርስ ድንጋጌዎች ጋር በማነፃፀር ለመግለጽ አይቻልም፡፡ ሆኖም የተለያዩ የብሔር ብሔረሰቦች ጎሳዎችና ማህበረሰቦች የየራሳቸው ባህላዊ የውርስ አወራረስ ደንቦች እንዳላቸውና እነዚህም በይዘትም ሆነ በአፈፃፀም የተለያየ ይዘትና ባህሪ እንዳላቸው በተለያየ ጊዜ ከተደረጉ አጫጭር የዳሰሳ ጥናቶች ለመረዳት ይቻላል፡፡

ስለሆነም በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየሆኑ ባሉ የባህል አወራረስ ደንቦች መካከል ያለው ልዩነትና አንድነት እንደዚሁም እያንዳንዱ ባህላዊ የውርስ አወራረስ ሥርዓት እየተሰራባቸው ካሉት የፍትሐብሔር ህጉ እና የሸሪዓ የውርስ ድንጋጌዎች ያላቸውን አንድነት እና ልዩነት በንጽጽር ለማቅረብ አይቻልም፡፡ በአንጻሩ ጐን በጎን የሚተረጉሟቸው እና የሚያስፈጽሟቸው ፍርድ ቤቶች ተቋቁመው እየተሰራባቸው ባሉት የፍትሐብሔር ሕግ የውርስ ደንቦችና በሸሪዓ የውርስ ደንቦች መካከል ያለውን መሰረታዊ የይዘት ልዩነትም በአፈፃፀም ሒደት እየተከሰቱ ያሉ መሠረታዊ ችግሮች ማየት በአገራችን የተለያዩ ባህላዊ ኃይማኖታዊና የፍትሐብሔር ህግ የተደነገገውን የአወራረስ ሥርዓት ተግባራዊ በማድረግ ሒደት ጥንቃቄ ሊደረግባቸው የሚገቡ መሰረታዊ ጉዳዮች ለመረዳት ጠቀሜታ ስለሚኖረው በአጭሩ ማየት ይጠይቃል፡፡

የሸሪዓና የፍትሐብሔር የውርስ ደንቦች መካከል የሚታየው መሠረታዊ ልዩነትና በአፈፃፀም የሚታዩ ችግሮች
954 views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 21:56:24 ባንኮችም የዋስትና ሰነድን ለደንበኞች በመስጠት የሚያገኙት ገቢ በወለድ መልክ ገንዘብን መቀበልንና የዋስትና ጊዜው ሲያልቅ የሚመለስ ገንዘብም በዋስትና ተጠቃሚው በኩል እንዲከፈል አይጠበቅም። በመሆኑም የዋስትና ሰነድ መጻፍ በተለምዶ የሚታወቀውን የአበዳሪና ተበዳሪ የብድር ግንኙነትን አይፈጥርም። ይልቁንም ባንኮቹ ለሚሰጡት የዋስትና ሰነድ የሚቀበሉት ተመጣጣኝ የሆነ ኮሚሽን ብቻ ነው። ይህ ሁኔታ ታዲያ በተለይ የዋስትና ሰነድ እንደ ብድር አገልግሎት የሚታይ አይደለም ለሚሉት ወገኖች እንደ አንድ መከራከሪያ ሀሳብ ይነሳል። ምክንያቱም የባንክ የብድር ግንኙነት የአበዳሪና የተበዳሪ ግንኙነትን ለመፍጠር አበዳሪው ለተበዳሪው በገንዘብ የሆነ ብድር የመስጠትንና ተበዳሪውም ይህንኑ የብድር ገንዘብ በዓይነትም ሆነ በጥሬው የመመለስ ግዴታን የሚጥል መሆኑ ግልጽ ነው።ይሁንና ግን የዋስትና ደብዳቤ ለዋስትና ተጠቃሚው ሲጻፍ ባንኮቹ የዋስትና ደብዳቤ እንዲጻፍለት የጠየቀውን ደንበኛቸው የገባውን ግዴታ እንዲፈጽም መተማመኛ ከመስጠት ባለፈ ለደንበኛቸው የሚሰጡት የብድር ገንዘብ የለም።

ሌላው መነሳት ያለበት ጉዳይ ባንኮች በሚያዘጋጂዋቸው የዋስትና ደብዳቤዎች ላይ የሚጠቀሱ የሰነዱን ይዘቶች የተመለከቱት ነጥቦቸ ናቸው። በተግባር በባንኮች የሚዘጋጁት የዋስትና ሰነዶች የተለያዩ ቢሆኑም የሰነዶቹ ይዘት ግን አንዳንድ የሕግ ክርክሮችን ሲያስነሱ ይታያሉ።የአንዳንድ የዋስትና ደብዳቤዎች ይዘቶች በተለይም ዋስትና ሰጪውን ተቋም ሳይቀር ባለገንዘቡ የዋስትና ሰጪው እና ወራሾቹ በጋራም ሆነ በተናጠል በደብዳቤው በተቀመጡት ግዴታዎች መሠረት ራሳቸውን ህጋዊ ግዴታዎች ውስጥ ገብተዋል፤ የዋስትና ቦንዱም ለተጠቀሰው የገንዘብ መጠን በቦንዱ ውስጥ በሰፈሩት ህጋዊ ስምምነቶች እና ድንጋጌዎች መሠረት ሆኖ ይህንን ቦንድ ምንም ዓይነት ቅድመ ሁኔታ ሊቀርብበት የማይችል የሚያደርጉ ናቸው፤ ማንኛውም ድርጊት ወይም ሳይፈጸም የቀረ ነገር በመኖሩ ሳቢያ ኪሳራ የሚደርስ መሆኑን ዋስትና የተሰጠው ባለገንዘብ ከደረሰበት ይህንኑ በዋስትና ጊዜው ውስጥ ለዋሱ ማሳወቅ አለበት የሚሉና የመሳሰሉት ይገኙበታል። በመሠረቱ አንዳንዶቹ ግዴታዎች በልማድ የተጻፉ ከመሆናቸው ውጪ በተለይ የዋሱን ወራሾች ሁሉ ተጠያቂ የሚያደርጉት የዋስትና ግዴታዎች ባንኮችን በተመለከተ ሊፈጸሙ የሚችሉም ስላልሆኑ በአብዛኛው በሰነዶቹ ይዘት ላይም ጥንቃቄን ማድረግ ያስፈልጋል። የዋስትና ደብዳቤም በጊዜ ገደብ የተወሰነ ግዴታ ሲሆን ደብዳቤውም በግልጽ ዋስትና የተገባለትን የገንዘብ መጠን ማመልከት ይገባዋል።

እንደማጠቃለያም የዋስትና ውል ማለት ሁለት ሰዎች ባደረጉት የባለገንዘብነትና የባለእዳነት ግዴታ ግንኙነት ውስጥ ከእነዚህ ተዋዋዮች ውጪ የሆነ ሌላ ሦስተኛው ባለእዳው እዳውን በሙሉ ወይም በከፊል ያልተከፈለ መሆኑ ከተረጋገጠ ወይም ግዴታውን በውሉ በተመለከተው አኳኋን በአግባቡ ያልተወጣ ከሆነ እኔ በባለእዳው ስፍራና አቋም ሆኘ እዳውን እከፍላለሁ ወይም ግዴታውን እወጣለሁ ሲል ለባለገንዘቡ ማረጋገጫ የሚሰጥበት በሕግ አግባብ ከተረጋገጠ ከበስተጀርባው ለአፈጻጸሙ የሕግ ጥበቃ የሚያገኝ ውል ነው በማለት የፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት ማብራሪያ ሰጥቷል። ይሁንና ግን የዋስትና ሰነዶች ከአገልግሎታቸው አንጻር በህጋችን ላይ ግልጽና ሰፊ ሽፋን የተሰጣቸው አይደሉም። በተለይም በንግድ ሕጉን ውስጥ እነዚህ ሰነዶች እንደ ብድር አገልግሎት የሚቆጠሩ መሆንና አለመሆናቸውን በሚገልጽ መልኩ እንዲሁም የተለያዩ ዓይነት የዋስትና ደብዳቤዎችን አገልግሎት እና በምን ሁኔታ ሊጻፉ እንደሚችሉ በሚገልጽ መንገድ የተቀመጠ ግልጽ ድንጋጌ ያስፈልገናል። በመሆኑም የንግድ ሕጉ የዋስትና ደብዳቤዎችን የተመለከተ ሰፊ የሕግ ሽፋን መስጠትና ማካተት ይጠበቅበታል። ከዚህም ጋር ተያይዞ የዋስትና ሰነዶችን ልዩ ባህሪያትና በተግባር ያሉትን የባንኮችን አሰራሮች በመፈተሽ ዝርዝር የሕግ ድንጋጌ ማስቀመጡ አስፈላጊ ነው።
By Abyssinia Law
839 views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 21:56:23 መሠረት የዋስትና ደብዳቤን ለማዘጋጀት በአብዛኛው የሚቀርበው የመያዣ ንብረት በመሆኑና የሰው ዋስትና በፍትሐብሔር ሕጉ በተቀመጠው መሠረት የዋስትና ደብዳቤ ለመጻፍ እንደመያዣ የማይቀርብ በመሆኑ በሰው ዋስትናና በሰነዶች ዋስትና መካከል መሠረታዊና ሰፊ ልዩነት እንዳለ መገንዘብ ያስፈልጋል ማለት ነው። በመሆኑም ይህ የዋስትና አገልግሎት በዋናነት ሰውን እንደዋስትና ወይም እንደ መያዣ ማቅረብን የሚመለከት አይደለም። ለዚህም ይመስላል የፍትሐብሔር ሕጉ ራሱ የሰው ዋስትናን እንደ አንድ የዋስትና ዓይነት በዘረዘረበት የሕጉ ድንጋጌዎች አሁን ባንኮች የሚጠቀሙባቸውን የመልካም ሥራ አፈጻጸም ዋስትና፣ የውል ማስከበሪያ ዋስትና፣ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ደብዳቤዎችንና ሌሎችንም የተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎችን መሠረት አድርገው እና ለተለያዩ ዓላማ የሚውሉትን የዋስትና ዓይነቶችም ቢሆን ለመዘርዘር ያልቻለው።

በሀገራችን በተለይም እነዚህ የዋስትና ዓይነቶች በአለም አቀፍ ደረጃም በተገባር ላይ መዋል የጀመሩትና ይህ ልማድም ወደ ሀገራችን ገብቶ በባንኮች መተግበር የጀመረውም የንግድ ሕጉና የፍትሐብሔር ሕጉ ከወጡ በኋላ በመሆኑ የዋስትና ሰነዶን በተመለከተ የፍትሐብሔር ሕጉን መሠረት በማድረግ የሚሰጡ የፍርድ ቤት ውሳኔዎችም ሆነ የሕግ ትርጉሞች በመሠረታዊነት እነዚህ በባንኮች በአገልግሎት ላይ የሚውሉ የዋስትና ሰነድ ዓይነቶችን የማይወክሉ የሚሆኑት። በአለም አቀፍ ደረጃም ቢሆን የዋስትና ሰነዶችን በተለይም (Independent Letter of Guarantees) በተመለከተ በኮድ መልክ የወጣውና በአብዛኛው ሀገሮችና ተቋማት አገልግሎት ላይ የሚውለው URDG 458 የሚባለው ሰነድ ሲሆን ሰነዱም ከጥቂት አመታት በኋላ URDG 758 በሚል ተሻሻሎ ቀርቧል። ስለዚህም የዋስትና ሰነዶች ታሪካዊ አመጣጥና በተግባር አገልግሎት ላይ መዋል የጀመሩትም የኢትዮጵያ የፍትሐብሔርና የንግድ ሕግ ከወጡ በኋላ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል።

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ 47004 በተሰጠ አስገዳጅ የሕግ ውሳኔ መሠረት የመልካም ሥራ አፈጻጸም ዋስትና ውል በፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች መሠረት የሚገዛ መሆኑን ገልጿል። ሰበር ችሎቱ በርካታ ትንታኔዎችን በጉዳዩ ላይ ለመስጠት የተጓዘበት ርቀት ጥሩ የሚባል ቢሆንም በመሠረታዊነት ግን ውሳኔው ሁሉንም የሕግ ባለሙያ ሊያስማማ የሚችል አይመስልም። ለዚህም ዋነኛ ምክንያቱ በውሳኔው ላይ የዋስትና ሰነድን የዋስትና ውል ሲል የገለጸው ሲሆን ከላይ በተመለከትነው መሠረት ግን ሰነዱ በባንኮች ተዘጋጅቶ የዋስትና ተጠቃሚውም ሆነ አበዳሪው በዚህ ሰነድ ላይ ምንም ዓይነት የስምምነት ፊርማ ሳያስቀምጡ፤ እንደሌሎች ውሎችም ምስክሮች መኖርም ሆነ መፈረም ሳያስፈልጋቸው በባንኮቹ ብቻ ተፈርመው ለዋስትና ተጠቃሚው የሚሰጡ ሰነዶች ናቸው።

በመሆኑም በዚህ ሰነድ ላይ እንደውል ለመቆጠር ቢያንስ ሁለት ወገኖች በውሉ ስለመስማማታቸው በጽሑፍ በሆነ ሰነድ ላይ መፈረምና ምስክሮችም ስማቸውንና ፊርማቸውን ማስቀመጥ እንደሚገባቸው የውል ሕግ እያስገደደ እነዚህ ነጥቦች ባልተሟሉበት ሁኔታ ሰነዱን ውል ማለት መሠረታዊ የውል መርህን የሚጥስ ነው። ሌላው የሰበር ትንታኔው የዋስትና ውል ብሎ የጠራውን ሰነድ በፍትሐብሔር ሕጋችን አንቀጽ 1920 እስከ 1951 የተቀመጠ መሆኑን በመጥቀስ የዋስትና ውል በችሮታ ላይ የተመሠረተ ግዴታ መሆኑን በመግለጽ ዋሱ ዋስ በመሆኑ የሚያገኘው ጥቅም የሌለ በመሆኑ አንድ ሰው ባለእዳው ሳይጠይቅ ወይም ሳያውቅ ዋስ መሆን እንደሚችል መመልከቱ ግንኙነቱ የግድ ጥቅም ላይ ያልተመሠረተ መሆኑን የሚያሳይ ነው በሚል ያስቀመጠው ነው። (የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 921ን ይመልከቱ) ይህ ትንታኔም በአንድ በኩል የሰው ዋስትናን ከሰነድ ዋስትና ጋር ለማመሳሰል የተደረገ ይመስላል። ይሁንና ስለሰው ዋስትና የተቀመጠው ይህ ትንታኔ በምንም መልኩ የሰነድ ዋስትናን የሚወክል አይደለም። ምክንያቱ ደግሞ በባንኮችም ሆነ በኢንሹራንስ ድርጅቶች የሚሰጡ የሰነድ ዋስትናዎች እስካሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ በችሮታ የሚሰጡ ሳይሆን በተለይ ባንኮች የሰነድ ዋስትናዎችን ለመጻፍ ከተጠቃሚው ጋር የንብረት ወይም የገንዘብ መያዣ ውል የሚገቡ ሲሆን የዋስትና ሰነዶቹንም ለተጠቃሚው የሚጽፉት የዋሰትና መጠኑን መሠረት አድርገው በሚቀበሉት የገንዘብ ኮሚሽን እንጂ በችሮታ አለመሆኑ ነው።

ችሮታም የሰው ዋስትና መሠረታዊ መለያ ባህሪ እንጂ ለሰነዶች ዋስትና የሚሰራ ጉዳይ አይደለም። የሰነድ ዋስትና ለመጻፍም ባለእዳው ሳያውቅ መጻፍ የማይቻል ሲሆን የሰነድ ዋስትናን ለመጻፍ የግዴታ ባለእዳው በአካል ቀርቦ ለባንኩ ማመልቻ ማስገባትና ለሰነዱ መጻፍ መሠረት የሆነውን የመያዣ ውል መዋዋል ግድ የሚል ነው። በመሆኑም የሰነድ ዋስትና ለመስጠት የባለእዳው መቅረብና ስለዋስትናው ማወቅ የግድ ነው። በሌላ በኩል ከላይ ለመግለጽ እንደተሞከረው የዋስትና ሰነድ የፍትሐብሔር ሕጉ ከወጣ በኋላ የመጣ ጽንሰ ሀሳብ በመሆኑ ይህንን ግዴታ ወደፍትሐብሔር ሕጉ ወስደን ትርጉም ለመስጠት መሞከሩ አግባብ ያልሆነ መሆኑ ነው። በመሆኑም የሰበር ችሎቱ የሰነድ ዋስትናን ከሰው ዋስትና ጋር ለማዛመድ የሞከረበት ትንታኔው ከዚህ በላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች ተቀባይነት ያለው አይመስልም።ይህ የሚያመለክተንም በመሠረቱ እነዚህ የዋስትና ዓይነቶች በልማድ ባንኮች በተግባር በሰፊው ይጠቀሙባቸው እንጂ አገልግሎታቸው ተለይቶ እንዴት እንደሚዘጋጁ እና በምን ሕግ እንደሚገዙም የሚገልጽ ግልጽ የሕግ ደንጋጌ አሁን ባሉት የንግድ ሕግም ሆነ በፍትሐብሔር ሕግ ውስጥ የሌለ መሆኑን ነው።

የዋስትና ሰነዶች በሁኔታ ላይ የተመሠረቱና በሁኔታ ላይ ያልተመሠረቱ ሊሆኑ ይችላሉ። በሁኔታ ላይ የተመሠረተ ዋስትና የሚባለው ዋሱ ባለዕዳው ግዴታውን በማንኛውም ሁኔታ ሳይወጣ ቢቀር ግዴታውን ያልተወጣው በምንም ምክንያት ይሁን ምክንያቱን መጠየቅ ሳይጠበቅበት የተባለው ግዴታ እንዳልተፈጸመ በአበዳሪው ሲገለጽለት በዋስትና ደብዳቤው የጊዜ ገደብ ውስጥ መሆኑን በማረጋገጥ የሚከፈሉ የዋስትና ደብዳቤዎች ናቸው። በሁኔታ ላይ የተመሠረቱ የዋስትና ደብዳቤዎች ደግሞ ዋሱ ለአበዳሪው የዋስትና ግዴታውን ለመወጣት እንዲያስችለው ባለአዳው (ዋስትና የተገባለት ሰው) ግዴታውን ያልተወጣው በማን ጥፋት ነው የሚለውን ካረጋገጠ በኋላ እና ጥፋቱ የባለእዳው መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ የሚወጣው ግዴታ ነው።

ባንኮች በአሁኑ ወቅት እየሰጡዋቸው ካሉ የዋስትና ሰነድ ዓይነቶች ውስጥ የመልካም ሥራ አፈጻጸም ዋስትና፣ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና፣ የውል ማስከበሪያ ዋስትና፣ የቅድመ ክፍያ ዋስትና፣ የአቅራቢነት ዋስትና ሰነዶች (ደብዳቤዎች) ናቸው። እነዚህ የዋስትና ሰነዶች በአብዛኛው ባንኮች ለደንበኞች የሚያዘጋጁላቸው ደንበኞች ለባንኮች በሚያቀርቡት የመያዣ ንብረቶች መሠረት የመያዣ ውል ከተዋዋሉ በኋላ ነው። አንዳንድ ጊዜ ግን የዋስትና ደብዳቤ እንዲጻፍለት የጠየቀ የባንክ ደንበኛን ባንኮቹ ተመጣጣኝ የሆነ ገንዘብ በዝግ ሂሳብ እንዲያስቀምጡ በማድረግ በምትኩ ግዴታቸውን ለመወጣት መተማመኛ የሚሆኑ ሰነዶችን ይሰጣሉ። ይህ ዓይነቱ ዋስትና የገንዘብ ዋስትና ይባላል። በብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር sib/24/2004 መሠረት የገንዘብ ዋስትና ሰነድ አንድ ሰው አንድን የተለየና የተወሰነ ሥራ ለሌላ ሰው ለመሥራት ግዴታ ከገባ ይኸው ሰው በውሉ መሠረት የገባውን ግዴታ መፈጸም የሚችል መሆኑን ለማረጋገጥ ሌላው ሰው የሚያቀርበው ውል ነው።
864 views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 21:56:23 የባንክ ዋስትና ሰነዶች (Letter of Guarantees) በኢትዮጵያ ሕግ ያላቸው ሽፋን
=====================
የዋስትና ሰነዶች ባንኮች በተለይም ለደንበኞቻቸው ከሚሰጧቸው የብድር አገልግሎቶች መካከል ዋነኞቹ ናቸው። የዋስትና ሰነዶች በተለያዩ ስያሜዎች የሚጠሩ ሲሆን በዚህም መሠረት በእንግሊዝኛ ‘independent undertakings’, ‘performance bonds/guarantees’, ‘tender bonds/guarantees’, ‘independent (bank) guarantees’, ‘demand guarantees’, ‘first demand guarantees’, ‘bank guarantees’, and ‘default undertakings’ በሚሉ ስሞች ሊጠሩ ይችላሉ። ከዚህ በተጨማሪም እነዚሁ ሰነዶች ‘standby Letters of Credit’ ተብለው ሊጠሩ እንደሚችሉ የተለያዩ ጽሑፎች ያሳያሉ። በዚህ መጽሐፍ ውስጥም የዋስትና ሰነዶች የሚለው ጥቅል ስያሜን ለመጠቀም የተሞከረ ሲሆን አንዳንዶቹ ስያሜዎችም የዋስትና ዓይነቶችን የሚያመለክቱ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። የዋስትና ሰነዶች በባንኮች የሚሰጡት ደንበኞች የተለያዩ ስምምነቶችን ከሌሎች ሦስተኛ ወገኞች ጋር ፈጽመው ያለባቸውን ግዴታ በአግባቡ ለመወጣታቸው ከባንኮች ዋስትና እንዲሰጥላቸው በሚያቀርቡት ጥያቄ መሠረት ነው። የዋስትና ደብዳቤ የሚሰጠውም አንድን ሰው የብድር አገልግሎት ወይም እቃዎቸንና አገልግሎቶችን ለሌላ ሦስተኛ ወገን በብቃት እንዲያቀርብ መተማመኛ በመሆን ነው። ዋስትና ሰነድም አንድ ሰው አንድን የተለየና የተወሰነ ሥራ ለሌላ ሰው ለመሥራት ግዴታ ከገባ ይኸው ሰው በውሉ መሠረት የገባውን ግዴታ መፈጸም የሚችል መሆኑን ለማረጋገጥ ሌላው ሰው የሚያቀርበው ውል ነው። (የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰበር መዝገብ ቁጥር 47004 ተመልከቱ) የዋስትና ሰነዶች የባንክ የብድር ዓይነቶች ወይም የብድር አገልግሎት መሆናቸውን ከማየታችን በፊት ግን የዋስትና ሰነዶች ምን ማለት እንደሆኑ ማየቱ ተገቢነት ይኖረዋል።
የዋስትና ደብዳቤ አንድ ደንበኛ የፈለገውን የንግድ እንቅስቃሴዎችና ግንኙነቶችን እንዲፈጽም ለማስቻል ደንበኛው ለአቅራቢው ወይም የአገልግሎት ተግባር ለመፈጸም የተዋዋለውን ደንበኛ ሥራውን እንዲያከናውን ለማስቻል የሚሰጥ ደብዳቤ ሲሆን የዋስትና ደብዳቤውን የሚያዘጋጀው ባንክም ሰነዱ የተዘጋጀለት ደንበኛ ግዴታውን መወጣት ባይችል ለተጠቃሚው በቀጥታ ግዴታውን እንደሚወጣ በማረጋገጥ የሚዘጋጅ ነው። የዋስትና ሰነዶችን በተመለከተ የሕግ ሽፋን የሰጠው የተባበሩት መንግስታት ኮንቬንሽን (UN Convention on Independent Guarantees and Standby Letters of Credit) የዋስትና ደብዳቤ ምን ማለት እንደሆነ እና የዋስትና ደብዳቤ ዓይነቶችንም ለመዘርዘር ሞክሯል። በዚሁ አለም አቀፍ ሕግ መሠረትም የዋስትና ደብዳቤ በአዘጋጁ (በብዛት ባንኮች ሲሆኑ) ደብዳቤው ለተዘጋጀለት ተጠቃሚ ዋስትና የተገባለት ግዴታ በባለዕዳው የማይከፈል ቢሆን የዋስትና ደብዳቤውን የጻፉት ባንኮች ባለዕዳውን ተክተው ክፍያውን (ዕዳውን) ለመክፈል ዋስትና እንደሚሆኑ በመግለጽ የሚሰጥ ደብዳቤ ነው። ይሁንና ይህ ኮንቬንሽን የሚያገለግለው አለም አቀፍ የሆኑ ግብይቶችን በተመለከተ እንደሆነ ተገልጿል። ኮንቬንሽኑንም የፈረሙት ሀገሮች ጥቂት በመሆናቸው ሁሉም ሀገሮች በዚህ ስምምነት መሠረት ይዳኛሉ ባይባልም አብዛኛው ሀገራት ግን የዋስትና ሰነዶችን በተመለከተ በሚያወጧቸው ሕጎች የዚህን ስምምነት አንቀጾች ከግንዛቤ በመክተት ሊሆን ይችላል። ኮንቬንሽኑ በተለይም የተለያዩ ዓይነት የዋስትና ደብዳቤ ዓይነቶች እንዳሉ ደንግጓል።

በኢትዮጵያ ሕግ ከዋስትና ሰነዶች ጋር በተያያዘ መነሳትና መዳሰስ ካለበት ዋና ነጥቦች መካከል የዋስትና ደብዳቤ ምን ማለት እንደሆነ፤ የዋስትና ደብዳቤ ምን ምን ነገሮችን ማካተት እንዳለበት፤ የዋስትና ደብዳቤዎች ያላቸው ሕጋዊ አስገዳጅነት፤ የዋስትና ሰነዶች ከሌሎች የዋስትና ዓይነቶች (እንደ ሰው ዋስትና እና የንብረት ዋስትና) ጋር ያላቸው አንድነት እና ልዩነት፤ እንዲሁም የዋስትና ሰነዶች እየተሰራባቸው ካለው ልማዳዊ አሰራር መነሻ ያደረገ ሌላ ሕግ አስፈላጊነት እና የመሳሰሉት ነጥቦች መብራራት ያለባቸው ናቸው።


ዋስትና የገንዘብ፣ የሰው እንዲሁም የንብረት እና የሰነድ ዋስትና ሊሆን ይችላል። እነዚህ የዋስትና ዓይነቶች ግን በየራሳቸው ልዩነት ያላቸው ሲሆን ሁሉንም በተመሳሳይ መልኩ ትርጉም በመስጠት ወይም አንዱን በአንዱ እያቀያየርን መጠቀም በመደረታዊነት ያሉትን የተለያዩ የዋስትና ዓይነቶች እና ያላቸውን ጠቀሜታ የሚያጠፋ ይሆናል። በዋናነት በንብረት፤ በሰው እና በሰነድ ዋስትና መካከል ያለውን ልዩነት ለመገንዘብ የፍትሐብሔር ሕጉን ድንጋጌዎች መመልከት ያስፈልጋል።

የፍትሐብሔር ሕጉ የሰው ዋስትናን (Suretyships or Guaranteership) በተመለከተ ከአንቀጽ 1920 እስከ 1951 ድረስ ባሉት ድንጋጌዎች ሰፊ ሽፋን ሰጥቷል። እነዚህ የሕጉ ድንጋጌዎች ግን የሚገለጹት ስለ ሰው ዋስትና ሲሆን በዚህም መሠረት ግለሰቦች ራሳቸውን ለአንድ ብድር ዋስትና አከፋፈል ባለዕዳው በገባው ውል መሠረት ግዴታውን መፈጸም እንዲችል ለማረጋገጥ የሚሰጡት ዋስትና ነው። በፍትሐብሔር ሕጉ ላይ የተገለጹት ዋስትናን የተመለከቱት ድንጋጌዎች ከውል ሕግ ጋር የሚያያዙ በመሆናቸው የባንክ የብድር ግንኙነቶችን አስመልክቶ በባንክ የሚዘጋጁትን የዋስትና ደብዳቤዎችን የማይወክሉና የማይመለከቱ ናቸው። በባንክ የሚዘጋጁት የዋስትና ደብዳቤዎች በባንኮች ከመዘጋጀታቸው በፊት ዋስትና ደብዳቤው እንዲዘጋጅለት የጠየቀው ደንበኛ የዋስትና ደብዳቤውን ከማግኘቱ በፊት ለደብዳቤው መሠረት የሆኑ ሁለት ዓይነት የተለያዩ እና በራሳቸው የቆሙ ውሎችን ይዋዋላል። አንደኛው ውል የዋስትና ደብዳቤው እንዲዘጋጅለት የጠየቀው ሰው ሊፈጽመው የገባው የአገልግሎት ወይም የአቅርቦት ወይም ሌላ ግዴታን የተመለከተና ከሦስተኛ ወገን ጋር የሚገባው ውል ነው። ሁለተኛው ውል ደግሞ የዋስትና ደብዳቤውን ከባንክ እንዲፈቀድለት የሚጠይቀው ሰው ከባንኩ ጋር የሚገባው ውል ነው። ይህ ውል የዋስትና ደብዳቤ እንዲጻፍለት ጥያቄ ያቀረበው ሰው ደብዳቤው በባንኩ እንዲጻፍለት ባንኩ የሚጠይቀውን ዓይነት ዋስትና ማለትም የንብረት ወይም የጥሬ ገንዘብ ዋስትና በማቅረብ የሚዋዋለው የመያዣ ውል ነው። እነዚህ ሁለት ውሎችም እርስ በእርሳቸው የማይገናኙ እና በራሳቸው የቆሙ ናቸው ማለት ይቻላል። የዋስትና ደብዳቤው ደግሞ ከእነዚህ ውሎች በኋላ በባንኮች የሚሰጥ የዋስትና ሰነድ ሲሆን ይህንን በባንኮች ተዘጋጅቶ ለባለእዳው የሚሰጠውን ደብዳቤ ግን እንደ ውል ልንቆጥረው የምንችለው ሳይሆን በቅድሚያ ባንኮች እና የዋስትና ሰነዱን የጠየቀው ሰው በገቡት የመያዣ ውል አማካኝነት የሚዘጋጅ ደብዳቤ እንደሆነ የሚቆጠር ነው።

በመሆኑም የዋስትና ደብዳቤው የሚዘጋጀው በባንኮች በመሆኑና በደብዳቤው ላይ የሚፈርመውም የሚያዘጋጀው ባንክ ብቻ በመሆኑና የዋስትና ደብዳቤው ላይ ዋስትና የተገባለት ሰውም ፊርማውን የማያኖር ሲሆን በደብዳቤው ላይም የምስክሮች ፊርማም ሆነ ስም በአብዛኛው አይቀመጥም። በመሆኑም ይህ ሁኔታ የሚያሳየው ደብዳቤውን ውል ለማለት የውል መሠረታዊ ሁኔታዎችን ያላሟላ መሆኑን ሲሆን ውል ነው የምንል ቢሆን እንኳን ከራስ ጋር የተደረገ ውል እንደሆነ ከመቆጠር ውጪ ሌሎች ውሎች የሚያሟሉትን ነጥቦች የሚያሟላ አይደለም። በዚህም
1.1K views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 21:42:49 የወንጀል ህግ ምንነት፣ ዓላማውና ህገ መንግስቱ
====================
የሰው ልጅ ሠላማዊ ህይወትን ለመምራት ከወንጀል የፀዳ ህብረተሠብ መፍጠር አለበት፡፡ ለዚህ ደግሞ ያለው አማራጭ የወንጀል ፍትህ አስተዳደርን መዘርጋት ነው፡፡ ይህ የወንጀል ፍትህ አስተዳደር እንዲኖር ህግ አውጭ፣ ህግ ተርጓሚና አስፈፃሚ አካላት መኖር አለባቸው፡፡ በዚሁ መሠረት ህግ አውጪው እንደ ወንጀል አድርጐ የሚቆጥራቸው ድርጊቶች እና ተገቢ ብሎ ያመነባቸውን ቅጣቶች ዘርዝሮ በህግ ያወጣል፤ ህግ ተርጓሚው ወንጀል ፈፅመዋል ተብለው የተከሰሱ ሠዎችን ሲቀርቡለት ማስረጃውን አዳምጦ ተገቢውን ውሣኔ ይሰጣል፡፡ አስፈፃሚው አካል በፖሊስ አማካኝነት ወንጀል እንዳይፈፀም ይከላከላል ተፈፅሞም ከሆነ ተጠርጣሪዎች ይዞ ለፍርድ ያቀርባል፡፡ ዓቃቤ ህግ መንግስትን በመወከል ክስ ያቀርባል፡፡ ማረሚያ ቤቶች ቅጣት የተወሰነባቸውን ጥፋተኞች ተቀብለው ያሰራሉ ሌሎች ቅጣቶችም ተወስነው ከሆነ ያስፈፅማሉ፡፡
ስለሆነም የወንጀል ህግና የወንጀል የፍትህ አስተዳደር መሠረታዊ አላማዎች የወንጀል አይነቶችን አስቀድሞ በማሣወቅ የአንድ ህብረተሠብ አባላት ይህንን አውቀው ከጥፋት እንዲታቀቡ ማድረግና ይህን ማስጠንቀቂያ በማይከተሉ ላይ ቅጣት መፈፀም ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት የወንጀል ህግ የተለያዩ የህብረተሠብ አባላት ማለትም ሰዎች ከሠዎች ወይም ከቡድኖች ወይም ከመንግስት ጋር ያላው ግንኙነት ይወስናል፡፡ በህግ እውቅና በተሠጠው ግንኙነት መሠረት ድርጊታቸውን ማስተካከል የሚችሉ ህጉ ተፈፃሚ የማይሆንባቸው ሲሆን ይህን ማድረግ የማይቻላቻው በህጉ መሠረት ይዳኛሉ፡፡
ኢትዮጵያ ከላይ የተጠቀሰውን አላማ ለማሣካት በተለያዩ ጊዜያት የወንጀል ህጐች ድንግጋ በተግባር ላይ አውላለች፡፡ በ1923 ዓ.ም የተደነገገው ለመጀመሪያ ጊዜ በስራ ላይ የዋለው የወንጀል ህግ ነው፡፡ 1949 ዓ.ም የወጣው ደግሞ ሁለተኛውና ከ40 ዓመት በላይ በስራ ላይ የነበረ የወንጀል ህግ ነው፡፡ በየመሃሉም ተጨማሪና ያለውን ከፍተት ሊሞሉ የሚችሉ ህጐች በስራ ላይ ነበሩ፡፡
ኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የወንጀል ህግ ከ1949 ዓ.ም ጀሞሮ በስራ ላይ የነበረውን የወንጀለኛ መቅጫ ህግ በመተካት ከግንቦት 1 ቀን 1997 ዓ. ም ጀምሮ በተግባር ላይ ውሏል፡፡ በኢፌድሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 52(5) ላይ በተሰጠው ስልጣንና ሃላፊነት መሠረት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወጣ ነው፡፡ ይህ የወንጀል ህግ ህብረተሠቡን በጉዳት ለመጠበቅ የወጣና እንደ ወንጀል የሚቆጠሩ ድርጊቶችና ለነዚህ የተከለከሉ ድርጊቶች ተገቢ ተብለው የተዘረዘሩ ቅጣቶችን የሚዘረዝር ህግ ነው፡፡ ስለሆነም ቅጣት እና ወንጀል ሁለቱ የወንጀል ህግ መሠረታዊ ጉዳዮች ናቸው፡፡
ወንጀል ምን ማለት ነው?

ወንጀል ምን ምን አይነት ባህሪያትን ያካትታል ብሎ ቋሚና አለም አቀፋዊ ትርጉም ለመስጠት ያስቸግራል፡፡ ወንጀል የሚባሉት ባህሪያት ከማህበረሠብ ማህበረሰብ ይለያያሉ፡፡ ማህበረሠቡ ሲያድግ ይለወጣሉ፡፡ ስለሆነም በዛሬ ጊዜ ወንጀል ተብሎ የተደነገገ ድርጊት ወይም ያለማድረግ ከዚህ በፊት ወንጀል ላይሆን ይችላል፡፡ ወይም ከዚህ በፊት ወንጀል ተብሎ የተደነገገ ጉዳይ ዛሬ ወንጀል ላይሆን ይችላል፡፡
የወንጀል ህግ ህግ እና ቅጣቶቹ በአብዛኛው የአለማችን ሃገሮች በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ተመሣሣይነት ቢኖራቸውም በዝርዝር ጉዳዮች ላይ ሊለያዩ ይችላሉ፡፡ እንዲህ አይነት ልዩነት ሊፈጠር የሚችለው የተለያዩ ሃገሮች ህዝቦች በተወሰኑ ጉዳዮች ያላቸው የአመለካከት ልዩነት ነው፡፡ ይህ ልዩነት ሃይማኖት ከባህል በስልጣኔ እድገት በሰው ልጆች መብት አጠባበቅ ብለው አስተሣሠብ ሊመነጨ ይችላል፡፡ በዚሁም መሠረት የአልኮል መጠጦችን ማዘዋወር፣ ዝሙት አዳሪዎች፣ ግብረሰዶም፣ ፅንስ ማስወረድ የመሣሠሉት ድርጊቶች በአንዳንድ ሃገሮች የወንጀል ድርጌት ተብለው ክልከላ ተደርጐባቸው ግርፋት ወይም የሞት ቅጣት የመሣሠሉትን ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ በሌሎች ሃገሮች ግን ይሄንኑ ተመሣሣይ ድርጊቶች ያልተከተሉ ወይንም በወንጀል ህግ የማያስጠይቁ ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ ሆኖም ግን በሠፊው ተቀባይነት ያገኘው ትርጉም የሚከተለውን ይመስላል
ወንጀል ማለት ፡- በወንጀል ህግ የተከለከሉ ድትጊቶችን መፈፀም ወይም እንዲፈፀሙ ትዕዛዝ ወይም ግዴታ የተጣለበቸውን ድርጊቶች አለመፈፀም ነው፡፡
በዚህ መሠረት የወንጀል ህጉ ኃላፊነትን የማያስከትል ተግባር የፈፀሙ ሠዎች በወንጀል እንዳይጠቁ ማድረጊያና ወንጀል የፈፀሙ ቢሆንም እንኳን በህጉ ላይ ከተመለከተው ቅጣት ውጪ በዘፈቀደና ኢ-ሰብአዊ በሆነ መንግድ እንዳይቀጡ መከላከያ መሣራያ ነው፡፡
የወንጀል ህግ አላማና ግብ

የወንጀል ህጉ አንቀፅ 1 ሁለት ፓራግራፎች ያሉት ሲሆን በመጀመሪያው አላማውን ሲገልፅ ሁለተኛው ግቡን ያብራራል፡፡
አንቀፅ 1
የወንጀል ሕግ ዓላማ፣ ለጠቅላላው ጥቅም ሲባል የአገሪቱን መንግሥት፣ የሕዝቦቹን፣ የነዋሪዎቹን፣ ሰላም፣ ደህንነት፣ ሥርዓት፣ መብትና ጥቅም መጠበቅና ማረጋገጥ ነው፡፡
የወንጀል ሕግ ግብ ወንጀል እንዳይፈፀም መከላከል ሲሆን ይህንን የሚያደርገው ስለወንጀሎችና፣ ስለቅጣታቸው በቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት፣ ማስጠንቀቂያነቱ በቂ ባልሆነበት ጊዜ ወንጀል አድራጊዎቹ ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ከመፈፀም እንዲቆጠቡና ለሌሎች ማስተማሪያ እንዲሆኑ ወይም እንዲታረሙ በማድረግ ወይም ተጨማሪ ወንጀሎች እንዳይፈፅሙ እርምጃዎች እንዲወሰድባቸው በማድረግ ነው፡፡


የወንጀል ህግ አላማ

የወንጀል ህግ አላማ ከፍ ብሎ በተቀመጠው አንቀፅ 1 የመጀመሪያው ፓራግራፍ እንደተመለከተው የሃገሪቱ መንግስት፣ የህዝቦቹን፣ የነዋሪዎቹን፣ ሰላም ደህንነት ስርዓት መብትና ጥቅም መጠበቅና ማረጋገጥ ነው ይላል፡፡ ይህ ህጉ በመጨረሻ ሊደረስበት ያስበውን አላማ ያመለክታል ስለዚህም የወንጀል ህጉ አላማ አጠቃላይ ህብረተሠቡን ከወንጀል ድርጊቶች መጠበቅና ሰላምን ማረጋገጥ ነው፡፡
በአንቀፁ የተገለፀው “ህዝቦች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ህገ መንግስቱ ለብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ከፍተኛ ጥበቃ ያደረገላቸው በመሆኑ የወንጀል ህጉ ይህንን ሊያንፀባርቅና ህጉ ነዋሪዎቹ በግለሰብነታቸው ብቻ ሣይሆን በልዩ ልዩ ህብረት በተቋቋሙበት ሁኔታ ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ነው፡፡ በተጨማሪም ዜጐቹንም ሆነ በአገሪቱ ውስጥ የሚገኙትን የውጭ ሃገር ሰዎች ስለሚያጠቃልልና ወንጀል ህግ ጥብቃ የሚያደርገው ለሰዎች ሁሉ ስለሆነ “ዜጐች” ተብሎ በቅድሞው ህግ ተገልፆ የነበረው ነዋሪዎች በሚለው ተተክቷል፡፡
የወንጀል ህጉ አላማ የነዋሪዎቹን ሰላም ማረጋገጥ ነው፡፡ ይህ በግልፅ የሚያመለክተው ከግለሰቦች መብት ይልቅ የህዝቦች መብት ቅድሚያ እንደተሠጠው ነው፡፡ ስለሆነም አንድ የወንጀል ድርጊት ሲፈፀም በህብረተሠቡ አጠቃላይ ጥቅም ላይ ጉዳት ደርሷል ተብሎ ይገመታል፡፡ በዚህም መሠረት የህዝብ ስርዓት ፣ ሰላምና ፀጥታ ሊጠበቅ የሚችለው የግለሰቦች መብት ሲጠበቅ በመሆኑ በእነዚህ መብቶች ላይ የሚደርስ ጥቃት በህዝብ ጥቅም ወይም መብት ላይ እንደተፈፀመ ወንጀል ይቆጠራል፡፡
2.9K views18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 15:49:19 Channel photo updated
12:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 22:47:30 ካርታ ማምከን/የይዞታ ማረጋገጫ መሰረዝ/
====================
የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ማረጋገጫ ማስረጃ /ደብተር ወይም ካርታ/ በመሰረዝ ዋጋ ማሳጣት
አንድ የአስተዳደር አካል የቤት ባለቤትነት ማስረጃ በፈለገው ጊዜ ከሕግ ውጪ እንዲሰረዝ ማስቻል በኢ.ፌ.ዲ. ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 40/1/ እና /2/ ድንጋጌ ሥር የተከበረውን የንብረት ባለቤትነት መብት ዋጋ የሚያሣጣው ነው፡፡ የፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1195 እና 1196 ድንጋጌዎች አንድ ላይ ሲነበቡም የአስተዳደር አካል በባለቤት ማረጋገጫ ማስረጃ አሰጣጥ ላይ ፍጽም የሆነ አስተዳደራዊ ስልጣን ያለው ስለመሆኑ አያሣዩም፡፡ ይልቁንም ድንጋጌዎች እርስ በእርሣቸውም ሆነ ከፍ/ሕ/ቁጥር 1198 ድንጋጌ ጋር ተዛምደው ሲታዩ የባለቤት ማረጋገጫ ደብተር የሚሰረዘው በሕጉ በተመለከቱት ምክንያቶች ብቻ መሆኑን ከሕጉ ውጪ ተግባሩ ተከናውኖ ከተገኘም መብቱ የተነካው ሠው በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 37፣78 እና 79 ድንጋጌዎች መሠረት ጉዳዩን ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት አቅርቦ አቤቱታው እንዲታይለት የሚያርግበት ጉዳይ እንጂ አስተዳደር አካሉ የሰጠው ውሣኔ በፍርድ ቤት እንዳይታይ የሚገደብበት ስርዓት የሌለ መሆኑን የምንገነዘበው ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 42501 ቅጽ 15፣ ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 37፣ 38፣ 79፣ ፍ/ህ/ቁ. 1195፣ 1196፣ 1198
አስተዳደራዊ ተቋማት በሕግ ተለይቶ በተሰጣቸው ጉዳይ የመወሰን ሥልጣን እንዳላቸው የታወቀ ነው፡፡ ይሁንና ለአንድ ባለ ጉዳይ የተሰጠው ካርታ የተሰጠበት እና የተሻረበት አግባብ በሕግ አግባብ መሆን ያለመሆኑን አጣርቶ የመወሰን ሥልጣን የፍርድ ቤቶች ነው፡፡ በዚህ ረገድ አንድ ፍርድ ቤት የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታን የመሰረዝ ሥልጣን የአስተዳደር ክፍል ነው፣ ፍርድ ቤት ጉዳዩን አይቶ የመወሰን ሥልጣን የለውም በማለት የሚደርስበት ድምዳሜ የጉዳዩን የክርክር ባህሪ እና ይዘት ያላገናዘበ ነው፡፡ ፍርድ ቤቶች በአስተዳደር ክፍል የተሰጠው ካርታ የተሰጠበት ወይም የተሻረበት ሥርዓት እና አስተዳደራዊ ውሳኔው ሕግና መመሪያ ያገናዘበ መሆን ያለመሆኑን በማጣራት ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን እንዳላቸው ከፍ/ህ/ቁ. 1196 እና በህገ መንግስቱ ስለ ንብረት መብት ከአደረገው ድንጋጌና በፍርድ የሚያልቁ ጉዳዮችን በተመለከተ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 37 ከተመለከቱት ድንጋጌዎች ይዘት የምንረዳው ጉዳይ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ 99071 ቅጽ 18፣ ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 37፣ ፍ/ህ/ቁ. 1196
3.6K views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-22 19:26:05 https://youtube.com/channel/UCU9osTZjo6yLL8C6yqVbRhA
4.2K views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-01 11:56:36 ለመንግሥት ሠራተኞች የሚሰጥ የወሊድ ፈቃድ
==================
ለአንድ የመንግስት ሰራተኛ የተለያዩ ዕረፍት ዓይነቶች ያሉ ስሆን በፌደራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1064/2010” አንቀጽ 43 ላይ የተደነገገው የወሊድ ፈቃድ ነው።
ነፍሰጡር የሆነች የመንግሥት ሠራተኛ፣ ከእርግዝናዋ ጋር የተያያዘ ምርመራ ለማድረግ ሐኪም በሚያዘው መሠረት ደመወዝ የሚከፈልበት ፈቃድ ይሰጣታል፤
1. ከመውለዷ በፊት ዕረፍት እንድታደርግ ሐኪም ካዘዘ ደመወዝ የሚከፈልበት ዕረፍት ይሰጣታል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) የተመለከተው ፈቃድ እንደ ህመም ፈቃድ አይቆጠርም፡፡
3. ነፍሰጡር የሆነች የመንግሥት ሠራተኛ መውለጃዋ ሲደርስ እወልዳለሁ ብላ ከገመተችበት ቀን በፊት 30 ተከታታይ ቀናት የቅድመ ወሊድ ፈቃድ፣ እንዲሁም ስትወልድ ከወለደችበት ቀን ጀምሮ 90 ተከታታይ ቀናት፣ በአጠቃላይ 120 ተከታታይ ቀናት ደመወዝ የሚከፈልበት የወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) መሠረት ሠራተኛዋ የተሰጣት የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከማለቁ በፊት ከወለደች ያልተጠቀመችበትን ቀሪ የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከወለደች በኋላ እንድትጠቀምበት ይደረጋል፡፡
5. ሠራተኛዋ የወሰደችው የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ሲያልቅ ያልወለደች እንደሆነ እስከምትወልድበት ቀን ድረስ ባሉት የሥራ ቀናት የምትቆይበት ዕረፍት በበጀት ዓመቱ ካላት የዓመት ዕረፍት ፈቃድ ወይም በበጀት ዓመቱ የዓመት ፈቃድ የሌላት እንደሆነ ከሚቀጥለው የበጀት ዓመት የዕረፍት ፈቃዷ ይተካል፡፡
6. ሠራተኛዋ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) የተወሰነውን የወሊድ ፈቃድ ከጨረሰች በኋላ ብትታመምና ተጨማሪ ፈቃድ የሚያስፈልጋት መሆኑ በሀኪም ከተረጋገጠ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 43(1) በተደነገገው መሠረት የሕመም ፈቃድ መውሰድ ትችላለች፡፡
7. ማንኛዋም ስድስት ወር የሞላት ነፍሰጡር የሆነች የመንግስት ሠራተኛ የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከመውሰዷ በፊት ጽንሱ የተቋረጠባት ከሆነ ይህንኑ የሚያረጋግጥ የህክምና ማስረጃ ስታቀርብ የ60 ቀን የድህረ ወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
8. የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከወሰደች በኋላ የጽንስ መቋረጥ ካጋጠማት የወሰደችው የቅድመ ወሊድ ፈቃዷ ተቋርጦ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) የተመለከተው የ90 ቀን የድህረ ወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
9. ከሦስት እስከ ስድስት ወር ባለው የእርግዝና ጊዜ ውስጥ የፅንስ መቋረጥ ያጋጠማት የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ የሚከፈልበት 30 ተከታታይ ቀን ፈቃድ ይሰጣታል፡፡
10. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የትዳር ጓደኛው ስትወልድ ደመወዝ የሚከፈልበት 10 የሥራ ቀን ፈቃድ ይሰጠዋል፡፡
7.0K views08:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ