Get Mystery Box with random crypto!

Tsegaye Demeke - Lawyer

የቴሌግራም ቻናል አርማ consultancy2012 — Tsegaye Demeke - Lawyer T
የቴሌግራም ቻናል አርማ consultancy2012 — Tsegaye Demeke - Lawyer
የሰርጥ አድራሻ: @consultancy2012
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.71K
የሰርጥ መግለጫ

Legal Service

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2021-08-24 20:07:12 የኢትዮጵያ ዜግነትን ስለማጣትና ፤ የሌላ ሀገር ዜግነት በማግኘት የኢትዮጵያ ዜግነት ስለሚቀርበት ሁኔታ
===========================
1. #ኢትዮጵያን ዜግነት ስለመተው
የሌላ አገር ዜግነት ያገኘ ወይም ሊሰጠው ቃል የተገባለት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን የመተው መብት አለው፤
ዜግነቱን ለመተው የፈለገ ኢትዮጵያዊ ባለሥልጣኑ በሚወስነው ቅጽ መሠረት አስቀድሞ ለባለሥልጣኑ ማሳወቅ አለበት፤
ለአካለ መጠን ያላደረሰ ሰው ዜግነቱን ለመተው የሚችለው በወላጆቹ የጋራ ውሳኔ ወይም ከወላጆቹ አንዱ የውጭ አገር ሰው ከሆነ ኢትዮጵያዊ በሆነ ወላጁ ውሳኔ ይሆናል፤
ዜግነቱን ለመተው መፈለጉን ያሳወቀ ኢትዮጵያዊ፣
የሚፈለጉበት ብሔራዊ ግዴታዎች ካሉ እነዚህኑ ከመወጣቱ፣ ወይም በወንጀል ተከስሶ ወይም ተፈርዶበት ከሆነ ከክሱ ነፃ ከመደረጉ ወይም የተወሰነበትን ቅጣት ከመፈጸሙ፤ በፊት የዜግነት መልቀቂያ አይሰጠውም።
ባለሥልጣኑ የዚህ አንቀጽ ድንጋጌዎች መሟላታቸውን ካረጋገጠ በኋላ ዜግነቱ የሚቋረጥበትን ቀን የሚገልጽ የዜግነት መልቀቂያ የምስክር ወረቀት ለባለጉዳዩ ይሰጠዋል፡
የዜግነት መልቀቂያ የምስክር ወረቀት ያልተሰጠው ማንኛውም ባለጉዳይ ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት ይግባኝ የማቅረብ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
2. #የሌላ ሀገር ዜግነት በማግኘት የኢትዮጵያ ዜግነት ስለሚቀርበት ሁኔታ
ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በራሱ ፍላጎት የሌላ አገር ዜግነት ካገኘ ዜግነቱን በራሱ ፈቃድ እንደተወ ይቆጠራል፣
ከወላጆቹ አንዱ የውጭ አገር ዜጋ በመሆኑ ወይም በውጭ አገር በመወለዱ የሌላ አገር ዜግነት ያገኘ ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን አስቀድሞ እንዲተው ካልተደረገ በስተቀር ለአካለ መጠን ካደረሰ በኋላ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የሌላ አገር ዜግነቱን ትቶ በኢትዮጵያዊነቱ ብቻ ለመቀጠል መምረጡን ለባለሥልጣኑ ካላሳወቀ ዜግነቱን በፈቃዱ እንደተወ ይቆጠራል፣
ራሱ ጠይቆ ሳይሆን በማናቸውም ሌላ ምክንያት ላይ ተመሥርቶ በሕግ ድንጋጌዎች ተፈጻሚነት የተነሳ የሌላ አገር ዜግነት ያገኘ ኢትዮጵያዊ፤
ባገኘው የሌላ አገር ዜግነት መብቶች መጠቀም ከጀመረ፣ ወይም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ያገኘውን የሌላ አገር ዜግነት ትቶ በኢትዮጵያዊነቱ ብቻ ለመቀጠል መምረጡን ለባለሥልጣኑ ካላሳወቀ ዜግነቱን በፈቃዱ እንደተወ ይቆጠራል።
ከኢትዮጵያ ዜግነቱ በተጨማሪ የሌላ አገር ዜግነት ይዞ የተገኘ ሰው የኢትዮጵያ ዜግነቱ ቀሪ እስከሚሆን ድረስ የኢትዮጵያ ዜግነት ብቻ እንዳለው ሆኖ ይቆጠራል፡፡


#Join_our_telegram_channel
https://t.me/Consultancy2012
Call us for #Legal_Service
Tsegaye Demeke - Lawyer
4.1K views17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-01 20:38:17 እግድ እና የመያዣ ወይም የቅድሚያ መብት

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 173079 ከፍርድ በፊት የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረትን አስመልክቶ የሚሰጥ የእግድ ወይም ንብረት የማስከበር ትዕዛዝ የመያዣ መብትን የማያቋቁም በመሆኑ የቅድሚያ መብትን ሊፈጥር እንደማይችል አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡

ይህ የህግ ትርጉም የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሰበር ሰሚ ችሎት ከዚህ በፊት በሰ/መ/ቁጥር 97206 እና በሰ/መ/ቁጥር 29269 በዚሁ ጉዳይ ላይ ሰጥቶት የነበረውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም አሻሽሏል ወይም ለውጧል፡፡
5.1K views17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-31 20:04:44 ከሟች ለወራሾቹ ሊተላለፉ የሚችሉና ሊተላለፉ የማይችሉ መብትና ግዴታዎች
======================
በመጀመሪያው ምእራፍ እንደተመለከተው የውርስ ሕግ ዋናው አላማና ግብ የሟች መብትና ግዴታዎች ወደ ወራሾቹ የሚተላለፍበትን ስርዓት መልክ ማስያዝ ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን ሟች የነበረው መብት እና ግዴታ በሙሉ ወደ ወራሾቹ ይተላለፋል ማለት አይደለም፡፡
በፍትሐብሔር ሕጋችን ለሟች ወራሾች የሚተላለፉት የሟች መብቶችና ግዴታዎች በሟች መሞት ምክንያት ተቋርጠው የማይቀሩት ብቻ መሆናቸው በግልጽ ተደንግጓል፡፡ ይህንንም ፅንሰ ኃሣብ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 826 ንዑስ አንቀጽ 2 '' በሟች መሞት ምክንያት ተቋርጠው ካልሆነ በቀር በዚህ አንቀጽ ደንቦች መሠረት በውርስ ውስጥ የሚገኙት የሟች መብቶችና ግዴታዎች ለወራሾቹ እና የኑዛዜ ባለስጦታዎች ይተላለፋሉ'' በማለት በግልጽ አስቀምጦታል፡፡

ከዚህ የሕግ ድንጋጌ የምንረዳው በሟች መሞት ምክንያት ተቋርጠው የሚቀሩ መብቶችና ግዴታዎች ወደ ወራሾቹ ሊተላለፉ እንደማይችሉ ነው፡፡ እነዚህ በሟች መሞት ምክንያት ተቋርጠው የሚቀሩ መብትና ግዴታዎች ምንድን ናቸው የሚለውን ጥያቄ ስንጠይቅ ሟች በግሉ ብቻ ሊጠይቃቸው እና ሊጠቀምባቸው የሚችሉ መብቶች /Personal rights/ እና ሟች በግሉ ሊፈጽማቸው የሚገቡ ግዴታዎች /Personal obligations/ ናቸው፡፡ የሟች ግላዊ መብቶችና ግዴታዎች የተለያዩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ለምሣሌ ሟች በሙያው በመንግስት መስሪያ ቤት ወይም በአንድ የግል ድርጅት ተቀጥሮ የሚሰራ ሠራተኛ ቢሆን የሟቹ የመሥራት መብት ወራሾቹ ከእሱ ጋር ተመሣሣይ በሆነ ሙያ የሰለጠኑ ቢሆኑም እንኳን ለወራሾቹ በውርስ የሚተላለፍ አይደለM፡፡ አንደዚሁም ሟች ከልጆቹ ወይም ከዘመዶቹ የነበረው ቀለብ የመጠየቅ መብት ሟች ሲሞት የሚቋረጥና ለወራሾቹ ሊተላለፍ የማይችል መብት ነው፡፡ በሌላ በኩል ሟች በግል ችሎታው ለመፈፀም የገባቸው ግዴታዎች፣ ወራሾቹ በዚያ ሙያ ከእሱ የበለጠ ችሎታ እና ትምህርት ቢኖራቸውም እንኳን ሟች በግሉ ለመፈፀም የገባውን ግዴታ እነርሱ ተክተው እንዲፈጽሙ አያስገድዳቸውም፡፡ ይህም አንድ የህክምና ዶክተር ወይም ጠበቃ በሙያው ለመፈፀም የገባውን ግዴታ እሱ ሲሞት ወራሾቹ ዳክተሮች ወይም ጠበቃ ቢሆኑም እንኳን ሟች በገባው የውል ግዴታ እነርሱ ወርሰውና ተተክተው እንዲፈጽሙ መጠየቅና ማስገደድ አይችልም፡፡ ስለዚህ ከሟች ወደ ወራሾቹ የሚተላለፉ መብትና ግዴታዎችን ለመለየት መብትና ግዴታዎቹ በሟች መሞት ምክንያት የሚቋረጡ ናቸው ወይስ አይደሉም የሚለውን ጥያቄ በማንሣት መመርመር ያስፈልጋል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ሟች በውል ወይም በሕግ መሠረት ያገኘው የይዞታ መብት በውሉ ወይም በሕግ በተገለፀው የጊዜ ገደብ እስከሚደርስ ድረስ በአንድ ንብረት የመጠቀም መብት ሙሉ ወይም ሌጣ የንብረት ባለቤትነት፣የአክሲዮን፣ የንግድ መደብር እና የሌሎች የንግድ ማህበር ድርሻዎች ሟች ከሌሎች ሰዎች ሊጠይቀው የሚችል የገንዘብ እዳና በውል መሠረት የሚፈፀም ግዴታ እንደዚሁም ሌሎች አበዳሪዎች ከእሱ የሚጠይቁት የገንዘብ እዳና በሟች መሞት ምክንያት የማይቋረጥ የውል ግዴታ ለሟች ወራሾች የሚተላለፉ የሟች መብትና ግዴታዎች ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ የፍትሐብሔር ሕግ የሟች ወራሾች የውርስ ንብረት ክፍል ናቸው በማለት የሟች ወራሾች ጥያቄ ማንሣት የማይችሉባቸውን የካሣና የጡረታ ገንዘብ ክፍያዎች እንደዘ!ሁም በሞት ጊዜ ሊከፈል ስለተገባ የህይወት ኢንሹራንስ ክፍያ ገንዘብ በምን መልኩ ለሟች ወራሾች እና የሟች ወራሽ ላልሆነ ሰዎች ሊተላለፉ እንደሚችሉ ገዥነት ያላቸውን ደንቦች ደንግጓል፡፡

#Join_our_telegram_channel
https://t.me/Consultancy2012
Call us for #Legal_Service
4.9K views17:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-31 20:03:55 አሁን በስራ ላይ ያለው የውርስ ህግ አጣሪ ስለሚሆኑ ሰዎች ሲደነግግ ቀዳሚውና የመጀመሪያው የውርስ አጣሪ የሚሆነው ሟች በኑዛዜ የውርስ አጣሪ አድርጎ የሾመው ሰው እንደሆነ ከገለጸ በኀላ ሟች በኑዛዜ የውርስ አጣሪ አድርጎ የሾመው ሰው ከሌለና በኑዛዜው የውርስ አጣሪ እንደሚሆንና ጠቅላላ ኑዛዜ የተደረገለት ሰው መገኘት የሟችን ያለኑዛዜ ወራሾች የአጣሪነት ስራ እንደሚያስቀረው በፍትህብሄር ህግ ቁጥር 948 ንኡስ ቁጥር 2 እና 3 የሚደነግግ ሲሆን የሟች ውርስ መዘጋት ማለት ደግሞ የሟችን ንብረት ለወራሾች በአግባቡ የማከፋፈል ስራን አይጨምርም፡፡

የውርስ አጣሪው ሀላፊነት ከላይ ያነሳናቸውን ተግባር በመፈጸምና የሟችን ወራሾችና የሟች ከእዳ ተከፍሎ የሚቀረውን ንብረት በማጣራት፣ ዝርዝርና የመጨረሻ ሪፖርት ለወራሾቹ ማቅረብ ብቻ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ የውርሱን ንብረት ማስተዳደርም ሆነ የሟችን ንብረት መከፋፈል የወራሾች መብትና ሀላፊነት እንጂ የውርሱ አጣሪ አይደለም፡፡
በመሆኑም ውርስ አጣሪ በዋነኛነት ሊፈጽማቸው የሚችላቸው ተግባራት፣
ከሟች ውርስ መብት አለን የሚሉትን ሰዎች ሁኔታ መወሰን፣
የሟችን የውርስ ንብረት ማስተዳደር፣
የሟችን የውርስ እዳ መክፈል፣ ናቸው፡፡
4.1K views17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-07-31 20:03:55 ውርስ አጣሪው የተሾመበት ኑዛዜ ዋጋ ያለው ኑዛዜ መሆኑ አከራካሪ ሆኖ ሲገኝ ወይም፣
በሌላ ምክንያት ውርስ አጣሪውን በመለየት ላይ የሚያጠራጥር ነገር ሲኖር ወይም፣
ብዙ ውርስ አጣሪዎች ለምሣሌ ስልጣናቸው 947 የሚመነጭ ብዙ ያለ ኑዛዜ ወራሾች ኖረው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 958 በሚደነግገው መሠረት ውርሱን በመተባበር በመግባባት ለማስተዳደርና ለማጣራት ያልተስማሙ እንደሆነ ወይም፣ ከወራሾቹ መካከል አንዱ አካለ መጠን የላደረሰ ልጅ ወይም የተከለከለ ሰው ወይም በማናቸውም ሌላ ምክንያት ለምሣሌ በአገር ባለመኖሩ፣ እብደቱ በግልጽ ያልታወቀ ሰው በመሆኑና በሌሎች ምክንያቶች ጥቅሙን ለማስከበር የማይችል በሆነ ጊዜ ወይም፣
የውርሱ አስተዳዳር ወይም የማጣራቱ ስራ ልዩ ችግር ያስነሣና ልዩ ሙያ ያላቸውን ሰወች ወይም ሌላ ችግሩን ለመቅረፍ የሚችል የውርስ አጣሪ መሰየም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ወይም፣
በሕግ ሟች ኑዛዜ ወይም በዳኞች የተሰየመው አጣሪ ቸልተኛና ትጉህ ያልሆነ እንደሆነ ወይም የማጭበርበር ባህሪ የሚታይበትና ሀቀኝነት የጉደለው የሆነ አንደሆነ ወይም አጣሪው የማጣራት ስራውን በሚገባ ለመፈፀም ችሎታ የሌለው መሆኑ የታወቀ እንደሆነ፣
ዳኞች ከማናቸውም በጉዳዩ ያገባኛል ከሚል ባለጉዳይ ጥያቄ አቅራቢነት በሕግ፣ በኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት ውሣኔ ተሰይሞ የነበረውን የውርስ አጣሪ በመሻር በአካባቢው ውል ለማዋዋል ስልጣን የተሰጠውን ሰው ወይም ማናቸውንም ለስራው ብቁ ነው ብለው የሚመርጡትን ሌላ ሰው በውርስ አጣሪነት ለመሰየምና ለመተካት እንደሚችሉ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 951 ተመልክቶ እናገኘዋለን፡፡

በውርስ ህጋችን በግልጽ እንደተመለከተው በህግ፣ በሟች ኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት ውሳኔ የተመረጠ ወይም የተተካ የውርስ አጣሪ የሚከተሉት ግዴታዎችና ሀላፊነቶች ይኖሩበታል፡፡
ሟች በህይወት ዘመኑ ያደረገው ኑዛዜ ካለ ኑዛዜውን መፈለግና የሟችን የኑዛዜ ወይም ያለኑዛዜ ወራሾች እነማን እንደሆኑ ማረጋገጥ፣
የውርስ ንብረት ከብልሽትና ከብክነት ለመታደግ ተገቢውን የጥንቃቄ እርምጃ በመውሰድና ሌሎችንም አስፈላጊ ተግባራት በመፈጸም የውርሱን ሀብት ማስተዳደር፣
በግልጽ የታወቁ፣ ክርክርን የማያስነሱ መከፈል ያለባቸውን የውርስ እዳዎች በፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 1014 በተቀመጠው ቅደም ተከተል መሰረት መክፈል፣
ሟቹ በልዩ ኑዛዜ ያደረጋቸውን ስጦታዎች መክፈልና የሟችን የኑዛዜ ቃል ለመፈጸምና ውጤት ለመስጠት ማንኛውንም አስፈላጊ ጥንቃቄ ማድረግ፣
ጥያቄው ያገባኛል በሚል ማናቸውም ባለጉዳይ ሲቀርብና ዳኞችን የሚያሳምን ሆኖ ሲገኝ ስለስራው መልካም አፈጻጸም አንድ ዋስ ወይም ሌላ የመልካም ስራ አፈጻጸም ማረጋገጫ ሊሆን የሚችል መያዣ ማቅረብ፣
ስራውን ለመተው ሲፈልግ አዲስ አጣሪ እስከሚሰየምና ተተክቶ ስራውን እስከሚጀምር ድረስ የአጣሪነት ስራውን የማከናወን፣
ሟች በአደረገው ኑዛዜ ስለአጣሪነቱ የስልጣን ወሰንና ስለስራው አፈጻጸም የሰጠውን መመሪያና ትእዛዝ ተከትሎ የመስራትና ዳኞችም ስለስልጣኑ ወሰንና ስለስራው አፈጻጸም የሚሰጡትን ትእዛዞች በማክበር የአጣሪነት ስራውን ማከናወን፣
ውርሱን አጣርቶ ከጨረሰ በኋላ ለወራሾቹ ስለማጣራቱ የስራ ክንውን ሪፖርት ማቅረብ፣
ውርስ አጣሪው ማናቸውንም የህጉን ድንጋጌዎች በሟች ኑዛዜ የተሰጡትን መመሪያዎች ወይም በዳኞች የተሰጡትን ትእዛዞች በሚቃረን በጥፋቱ ወይም በቸልተኝነቱ መንገድ ለሚያደርጋቸው ጉዳዮችና በዚያ መሰረት ለሚደርስ ጉዳት በሀላፊነት የመጠየቅ ግዴታ እንዳለበት፣
ከፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 952፣ 954-957 እንደዚሁም የፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 960 እና 961 በማየት መረዳት ይቻላል፡፡

በሌላ በኩል ህጉ በህግ፣ በሟች ኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት ውሳኔ በውርስ አጣሪነት ለሚሰየሙ ሰዎች ያስቀመጠላቸው መብት አለ፡፡ ከመብቶቹ መካከል እጅግ በጣም አስፈላጊው የውርስ አጣሪነት ስራ ማንም ሰው በፈቃዱ ብቻ ሊያከናውነው የሚገባና ማንም ሰው ያለፈቃዱ የአጣሪነት ስራዎችን ለመቀበል የማይገደድ መሆኑ ነው፡፡ አንድን ተግባር አንድ ሰው ተገድዶ እንዲያከናውን ማድረግ የተከለከለና መሰረታዊ የሆነውን የሰው ልጅ ነጻነት መብት የሚነካ በመሆኑ የውርስ አጣሪነትን ተግባር አንድ ሰው ሳይፈልግ እንዲቀበልና እንዲሰራ ማድረግ እንደማይቻል የፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 953 በግልጽ ይደነግጋል፡፡ ሁለተኛው መብቱ ደግሞ ውርስ አጣሪው ስራውን እፍጻሜ ለማድረስ ወይም ለተወሰነ ጊዜ ለመስራት በግልጽ ግዴታ የገባ ካልሆነ በቀር በማናቸውም ጊዜ ስራውን መተው የሚችል መሆኑ ነው፡፡ እዚህ ላይ በጥንቃቄ መታየት ያለበት ጉዳይ ‹በግልጽ ግዴታ የገባ ካልሆነ በቀር› የሚለው ሀረግ ነው፡፡ በዝምታ በህግ፣ በሟች ኑዛዜ ወይም በዳኞች የውርስ አጣሪ ሆኖ እንዲሰራ መመረጡን ተቀብሎ ስራ መጀመሩ ብቻውን የማጣራት ስራውን በማናቸውም ጊዜ የመተው መብቱን አያስቀርበትም፡፡ ስራውን የመተው መብቱ ቀሪ የሚሆነው በግልጽ እራሱን ግዴታ ያስገባ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡

ሌላው እዚህ ላይ መታየት ያለበት ውርስ አጣሪው ይህንን የማጣራቱን ስራ የመተው መብቱን እንደፈለገው ሊጠቀምበት አይችልም፡፡ የሟች ውርስ ንብረት የግድ መጠበቅና በጥንቃቄ መያዝ ስለሚገባው ሌላ ተተኪ አጣሪ እስኪመረጥና ስራውን እስኪረከብ ድረስ ስራውን እየሰራ መቆየት ያለበት መሆኑ የፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 954 ድንጋጌዎችን በማየት ለመረዳት ይቻላል፡፡
በሶስተኛ ደረጃ ለውርስ አጣሪ የተቀመጠለት መብት አጣሪው ውርሱን ለማጣራት ለሰራው ስራ የአገልግሎት ዋጋ የማግኘት መብት ያለው መሆኑ ነው፡፡ የውርሱ አጣሪ የአገልግሎት ክፍያውን የሚያገኘው ሟች በኑዛዜው ውስጥ በሰጠው መመሪያ ወይም ወራሾቹ በሚያደርጉት ስምምነት ወይም ዳኞች በሚሰጡት ውሳኔ መሰረት ሊሆን እንደሚችል የፍትሀ ብሄር ህግ ቁጥር 959 ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም አጣሪው ውርሱን በማጣራት ለሰራው ስራና ግልጋሎት ከውርሱ ንብረት ላይ ከላይ ባስቀመጥናቸው ሁኔታዎች ሲወሰንለት የአገልግሎት ዋጋ የማግኘት መብት እንዳለው መታወቅ ይኖርበታል፡፡
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የውርስ ህግ መሰረት ‹ውርሱን ስለማጣራት› የሚለው ጽንሰ ሀሳብ ምንነትና ይዘት እንደዚሁም ጠቀሜታ በጥንቃቄ ሊታይ የሚገባው ነው፡፡ የመጀመሪያው በምእራፍ ሁለትም ለመጠቆም እንደተሞከረው ‹የሟች ውርስ መከፈት› እና ‹የሟችን ውርስ ማጣራት› የሚሉት ጽንሰሀሳቦች እጅግ በጣም የተለያዩ ናቸው፡፡ የሟች ውርስ መከፈት የምንለው ሟች ህይወቱ ካለፈበት ቅጽበት ጀምሮ ምንም አይነት የሲቪል መብት ግዴታ ሊኖረው ስለማይችል ህጉ የሟች ህይወት ካለፈችበት ሰኮንድ ጀምሮ የሟች መብትና ግዴታ ለሟች ወራሾች ለማስተላለፍ የሚያደርጋቸውን ጥንቃቄ የሚመለከት ነው፡፡

የሟች ውርስ የሚከፈተውም ሟች መኖሪያ ስፍራና ሟች በሞተበት ጊዜ እንደሆነ በፍትሀ ብሄር ህግ ቁጥር 826 ተመልክቷል፡፡ የሟችን ውርስ ማጣራት የምንለው ደግሞ የሟችን ያለኑዛዜና በኑዛዜ ወራሾች የሚለዩበት፣ የሟች እዳ የሚከፈልበት፣ የሟች አበዳሪዎች እና ተበዳሪዎች የሚለዩበት፣ ንብረቱ በሟች ወራሾች እስኪተላለፍና ውርሱ እስከሚዘጋበት ቀን ድረስ የንብረት ማስተዳደር ስራዎች የሚከናወንበት ውስብስብ ተግባር ነው፡፡
3.9K views17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ