Get Mystery Box with random crypto!

ATC UEE PREPARATION

የቴሌግራም ቻናል አርማ atc_uee — ATC UEE PREPARATION A
የቴሌግራም ቻናል አርማ atc_uee — ATC UEE PREPARATION
የሰርጥ አድራሻ: @atc_uee
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.25K

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

3

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-03-07 12:14:29
የምዝገባ ጥሪ ማስታወቂያ ለሬሚድያል ፕሮግራም ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ:

በ2015ዓ/ም ለሬሚዲያል ፕሮግራም ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደው ከመጋቢት 2-3/2015 ዓ/ም ስለሆነ በአካል ቀርባችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ በጥብቅ እናሳስባለን።

ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ይሁን ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እየገለፅን ማንኛዉም ተማሪ ሲመጣ የትራስ ጨርቅ እና አንሶላ ይዞ መምጣት እንዳለበት እናሳስባለን።

የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ዳይሬክቶሬት

ለበለጠ መረጃ ከዛሬ ጀምሮ ምሽት ሁለት ሰዐት ዜና በኋላ በኢቲቪ ዜና ቻናል ለተከታታይ ቀናት የሚተላለፈውን የጥሪ ማስታወቂያ እንድትከታተሉ እናሳውቃለን!!


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
1.2K views09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 11:00:40 በዚህ መረጃ ለአንድ ዓመት የሚለው ቃል ለዚህ ዓመት ተማሪዎች በሚለው ተረዱት ለሁሉም የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የማስተማሪያ ሰነድ የሚለው ከቀናት በፊት ያጋራናቹህ #CourseOutline ነው። የናቹራሎች Course Outline የሶሻሎች። Course Outline
1.7K viewsedited  08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 23:18:26 በዚህ መረጃ ለአንድ ዓመት የሚለው ቃል ለዚህ ዓመት ተማሪዎች በሚለው ተረዱት

ለሁሉም የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የማስተማሪያ ሰነድ የሚለው ከቀናት በፊት ያጋራናቹህ #CourseOutline ነው።

የናቹራሎች Course Outline
የሶሻሎች። Course Outline
2.5K viewsedited  20:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 23:04:27
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መግቢያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ከ95 በመቶ በላይ የሚሆኑት ተማሪዎች ከ50 በመቶ በታች ውጤት ማምጣታቸው ይታወቃል፡፡

ከሀምሳ በመቶ በታች ካመጡት ተማሪዎች መካከል በልዩ ሁኔታ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተው ለአንድ አመት የአቅም ማሻሻያ ትምህርት ሪሜዲያል እንዲወስዱ የተወሰነ ሲሆን ከመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተጨማሪ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትም የአቅም ማሻሻያ ትምህርት መውሰድ እንደሚችሉ የትምህርት ሚንስቴር የህዝብ ግንኙት ሃላፊ ወ/ሮ አመለወርቅ ህዝቅኤል ገልፀዋል፡፡

ትምህርት ሚንስቴር ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ያደረገ ሲሆን ይህን የአቅም ማሻሻያ ትምህርት መስጠት የሚፈልጉ የግል ከፍትኛ የትምህርት ተቋማትም በዚሁ መሰረት ተማሪዎች ተቀብለው ማስተማር የሚችሉ ሲሆን በቅድሚያ ግን የመዘገቧቸውን ተማሪዎች ለትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን ማሳወቅ እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም የልህቀት ማእከል ተብለው በተለዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በኩል የተዘጋጀ የአቅም ማሻሻያ ሪሜዲያል ትምህርት ማስተማሪያ ተዘጋጅቶ ለሁሉም የመንግስት እና የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መላኩን ጠቁመዋል፡፡

አያይዘውም የማስተማሪያ ሰነዱ ለተማሪዎቹ ከ 9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርት አጠቃሎ የያዘ ሲሆን ሁሉም የትምህርት ተቋማት ማስተማር የሚችሉት ይሄንን በመጠቀም መሆን እንዳለበት ለአሀዱ በሰጡት ቃል አመላክተዋል፡፡

Credit : #Ahadu

፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
2.4K views20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 21:49:17 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው የማካካሻ ትምህርት/Remedial Program/ ፕሮግራም ለመከታተል ያለፉትን ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በግል ከፍሎ ለመማር የሚፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

1. የመመዝገቢያ መስፈርቶች
በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው የማካካሻ ትምህርት/Remedial/ ፕሮግራም ለመከታተል ያለፉ (እንደተፈተኑት የትምህርት ዓይነት ብዛት 30% ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማለትም (210 ከ 700፣ 180 ከ 600 እና 150 ከ 500) የተቆረጠውን ነጥብ የሚያሟሉ፡፡

2. የሚያስፈልጉ የትምህርት መረጃዎች
1. E.S.L.C.E/EHEEQC የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመግቢያ ውጤት ካርድ ኦርጅናልና የማይመለስ ሁለት ፎቶ ኮፒ
2. ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኦርጅናልና የማይመለስ ሁለት ፎቶ ኮፒ
3. የማይመለስ ሁለት ዶሴ (ክላሰር) እና ሁለት ጉርድ ፎቶ ግራፍ
4. የማመልከቻ ክፍያ ብር 50.00 /ሀምሳ ብር/ ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000021480502 ገቢ የተደረገበትን ደረሰኝ ከማስረጃቸዉ ጋር
ማያያዝ::
5. የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ካርድ ኦርጅናልና የማይመለስ ሁለት ፎቶ ኮፒ

3. የማመልካቻ ቦታ
ሀ) አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ነጭ ሣር ካምፓስ የተከታታይና ርቀት ትም/ት ኮሌጅ ሬጅስትራር ጽ/ቤት
ለ)አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ የተከታታይ ትም/ት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት(የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ብቻ)
4. የምዝገባ ጊዜ - ከየካቲት 27/2015 - መጋቢት 07/2015 ዓ.ም ድረስ

ለተጨማሪ መረጃ - በ046-181-5468 እና 046-181-0228 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተከታታይና ርቀት ትምህርት ኮሌጅ


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
2.5K views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 19:24:11
በግልም ይሁን በመንግስት የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሪሚዲያል ለምትማሩ ተማሪዎች በተመጣጣኝ ክፍያ ለሁሉም ተማሪ Common Subject የሆነውን #Mathematics ሙሉ ቲቶርያል ሰርተንላቹሃል።

ስለ ቲቶርያሎቹ አሰጣጥ እና ስለ ክፍያው ሙሉ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ
1.6K views16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 19:04:09 ከ760 ሺህ በላይ ሠልጣኞች ቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ይገባሉ
**

በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 760 ሺህ 832ቱ ወደ ቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ገብተው እንደሚሰለጥኑ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ።

በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት የሚሰጠው ሥልጠና ወደ ደረጃ ስምንት ከፍ እንዲል ተደርጓል።

የሥራ እና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በትናንትናው ዕለት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ በ2015 ዓ.ም ወደ ቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ሊገቡ የሚችሉ ሠልጣኞች ቁጥር 760 ሺህ 832 ሲሆን፣ 20 በመቶ የሚሆኑት ከቴክኒክ እና ሙያ ውጪ ባሉ ማሠልጠኛ ተቋማት ይገባሉ።

በመሆኑም በአገር አቀፍ ደረጃ ቴክኒክ እና ሙያ የሚገቡት ሠልጣኞች ቀጥር 608 ሺህ 666 መሆናቸውን አስታውቀዋል።

በ2015 ዓ.ም የመቁረጫ ነጥብ የሠልጣኞች ድልድል የኢንዱስትሪውን የሰው ኃይል አሰላለፍ መሠረት በማድረግ የተሰላ በመሆኑ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የሥራ ገበያውን፣ የሰው ኃይል ፍላጎት እና የአከባቢውን የልማት ቀጠና መሠረት በማድረግ ቅበላ ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል።

መቁረጫ ነጥቡ የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናን የወሰዱ ተማሪዎችን ታሳቢ ተደርጎ የተሠራ በመሆኑ ለ2015 ዓ.ም ብቻ የሚያገለግል መሆኑን ያነሡት ሚኒስትሯ፣ መቁረጫ ነጥቡን እስካሟሉ ድረስ በመረጡት የሥልጠና መስክ በመንግሥት እና የግል ማሠልጠኛ ተቋማት ላይ መሠልጠን የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል።

በ2013 ዓ.ም እና በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና ሥርዓት ያልገቡ ተማሪዎች የሚስተናገዱት በ2014 ዓ.ም በነበረው የመቁረጫ ነጥብ መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም የ10ኛ ክፍል ትምህርታቸውን በመደበኛ የሥልጠና ፕሮግራም ወደ ቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ገብተው መሠልጠን ያልቻሉ ተማሪዎች 11ኛ ክፍል ገብተው መማር አለበለዚያም በአጫጭር ሥልጠና የቴክኒክ እና ሙያ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ አስረድተዋል።

በተፈጥሮ እና ማኅበራዊ ሳይንስ 12ኛ ክፍል አጠናቅቀው የመቁረጫ ነጥቡን የሚያሟሉ ተማሪዎች በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና ተቋማት ውስጥ በሚሰጡ ሁሉም ሙያዎች ላይ እኩል የመወዳደር እና የመሠልጠን መብት እንደሚኖራቸው አብራርተዋል።

እንደ ሀገር በሁሉም ዘርፍ ጥራት እና ብቃት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት ታቅዶ በትምህርት እና ሥልጠና ፖሊሲው ላይ በተደረገው ማሻሻያ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት የሚሰጠው ሥልጠና ወደ ደረጃ ስምንት ከፍ እንደሚል አስታውቀዋል።

እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ ደረጃ አምስት አድቫንስድ ዲፕሎማ፣ ደረጃ ስድስት የመጀመሪያ ዲግሪ፣ ደረጃ ሰባት ማስተርስ እና ደረጃ ስምንት ዶክትሬት (PHD) እኩሌታን የሚይዝ ሲሆን ዘርፉን ተወዳዳሪ እና ተፈላጊ በማድረግ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ አለው።

የቴክኒክ እና ሙያ ማሠልጠኛ ተቋማትን የማዘመን፣ ተደራሽ የማድረግ እና በትኩረት መስክ የማደራጀት ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ መግለጻቸውንም ኢፕድ ዘግቧል።

የትምህርት እና ሥልጠና ሥርዓቱን ለሥራ ገበያው በሁሉም ደረጃዎች የሠለጠነ የሠራተኛ ኃይል እና ተስማሚ ቴክኖሎጂ የማቅረብን ተልእኮ ለቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና የተሰጠ ነው ያሉት ወ/ሮ ሙፈሪያት፣ ተልዕኮውን ውጤታማ ለማድረግ በእውቀቱ፣ በክህሎቱ፣ በአመለካከቱ ብቁ የሆነ ዜጋ ለማፍራት ከሠልጣኝ ቅበላ እስከ ሥራ ማስተሳሰር ያሉ ሂደቶች ጥንቃቄን የሚሹ ጉዳዮች ናቸው ብለዋል።


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
2.5K views16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 17:37:05
#MaddaWalabuUniversity

በ2015 ዓ.ም በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ ሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ መጋቢት 7 እና 8/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሄዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➧ የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ፣
➧ ከ8-12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
➧ ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➧ የሌሊት አልባሳት፣
➧ የስፖርት ትጥቅ፣
➧ የኮቪድ-19 መከላከያ ማስክ፡፡

ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን የማያስተናግድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።

፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
2.3K views14:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 17:36:06
በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም በሪሜዲያል ፕሮግራም የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ መጋቢት 11 እና 12/2015 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ በዩኒቨርስቲው በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ ሲል ዩንቨርሲቲው ገልጿል።


፨ዝርዝር መረጃ ከምስሉ ይመልከቱ

፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
2.3K views14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 12:30:28
በ2014ዓ.ም የ12ኛ መልቀቂያ ፈተና ተፈትናችሁ የሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ መጋቢት 4 እና 5 /2015 ዓ.ም ለተከታታይ ሁለት ቀናት ብቻ መሆኑን ዩኒቨርሲቲዉ ያሳዉቃል ።
ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ስትመጡ ፦
 ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ያለዉን ትራንስክሪፕት ኦሪጂናል እና ፎቶ ኮፒ ፣
 የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃ ኦሪጂናል እና ፎቶ ኮፒ ፣
 አራት 3*4 ፓስፖርት ሳይዝ ጉርድ ፎቶግራፍ፣
 የሌሊት አልባሳት፣አንሶላ፣የትራስ ጨርቅ እና
 የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ እንድትመጡ ዩኒቨርሲቲዉ እያሳወቀ ከተባለዉ ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ ለሚመጣ ተማሪ ዩኒቨርሲቲዉ የማያስተናግድ መሆኑን ይገልጻል።
ለበለጠ መረጃ የዩኒቨርሲቲዉን ድረ-ግጽ
www.bhu.edu.et መጎብኘት ይቻላል

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራር እና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት

፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
2.7K views09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ