Get Mystery Box with random crypto!

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው የማካ | ATC UEE PREPARATION

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው የማካካሻ ትምህርት/Remedial Program/ ፕሮግራም ለመከታተል ያለፉትን ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በግል ከፍሎ ለመማር የሚፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

1. የመመዝገቢያ መስፈርቶች
በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው የማካካሻ ትምህርት/Remedial/ ፕሮግራም ለመከታተል ያለፉ (እንደተፈተኑት የትምህርት ዓይነት ብዛት 30% ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማለትም (210 ከ 700፣ 180 ከ 600 እና 150 ከ 500) የተቆረጠውን ነጥብ የሚያሟሉ፡፡

2. የሚያስፈልጉ የትምህርት መረጃዎች
1. E.S.L.C.E/EHEEQC የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመግቢያ ውጤት ካርድ ኦርጅናልና የማይመለስ ሁለት ፎቶ ኮፒ
2. ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኦርጅናልና የማይመለስ ሁለት ፎቶ ኮፒ
3. የማይመለስ ሁለት ዶሴ (ክላሰር) እና ሁለት ጉርድ ፎቶ ግራፍ
4. የማመልከቻ ክፍያ ብር 50.00 /ሀምሳ ብር/ ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000021480502 ገቢ የተደረገበትን ደረሰኝ ከማስረጃቸዉ ጋር
ማያያዝ::
5. የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ካርድ ኦርጅናልና የማይመለስ ሁለት ፎቶ ኮፒ

3. የማመልካቻ ቦታ
ሀ) አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ነጭ ሣር ካምፓስ የተከታታይና ርቀት ትም/ት ኮሌጅ ሬጅስትራር ጽ/ቤት
ለ)አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ የተከታታይ ትም/ት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት(የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ብቻ)
4. የምዝገባ ጊዜ - ከየካቲት 27/2015 - መጋቢት 07/2015 ዓ.ም ድረስ

ለተጨማሪ መረጃ - በ046-181-5468 እና 046-181-0228 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተከታታይና ርቀት ትምህርት ኮሌጅ


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news