Get Mystery Box with random crypto!

AMN-Addis Media Network

የቴሌግራም ቻናል አርማ addismedianetwork — AMN-Addis Media Network A
የቴሌግራም ቻናል አርማ addismedianetwork — AMN-Addis Media Network
የሰርጥ አድራሻ: @addismedianetwork
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 36.65K
የሰርጥ መግለጫ

This is an official Telegram channal for Addis Media Network (AMN) We trive to be the prime informer of issues. Hence, our motto says so, 'first to inform'
ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ !!
contact us via:- E-mail:- addisaammaa@gmail.com
twitter.com/AmnAddis

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-10-07 15:26:08 https://telegra.ph/AAmn-10-07
14.6K views12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-05 18:11:02

12.7K views15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-04 11:00:41
በትምህርት ዘርፍ ያለውን የጥራት ችግር ዘላቂ በሆነ ሀገራዊ መፍትሄ ለመፍታት የትምህርት ተቋማት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ(ኤ ኤም ኤን )መስከረም 23/2016 ዓ.ም
በትምህርት ዘርፍ ያለውን የጥራት ችግር ዘላቂ በሆነ ሀገራዊ መፍትሄ ለመፍታት የትምህርት ተቋማት ኃላፊነታቸውን በትጋት እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ።

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ይፋዊ የትምህርት ዘርፍ የከፍተኛ ትምህርት ተቋምነት ምስረታውን እያከበረ ይገኛል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ዶ/ር ብርሀነመስቀል ጠና ለ6 ዩኒቨርስቲው አስርት ዓመታት በትምህርት ዘርፍ ትውልድና ሀገርን ሲያገለግል ስለመቆየቱ አንስተዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያ የትምህርት ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ሆኖ የተቋቋመው የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ዘርፍ ያለውን ሀገራዊ ድርሻና ሚና ለማላቅ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩሉን ለመወጣት እየተሰራ ነውም ብለዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ተወካይ ሚኒስትር ዲዔታ ዶ/ር ሰለሞን አብርሀ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የትምህርት ተደራሽነት ለማሳደግ የተገኙ ውጤቶችን ያክል የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ሰፊ ጥረት ይፈልጋልም ብለዋል።

በዚህ ረገድ እንደ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ያሉ የትምህርት ዘርፉን አጋዥ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ራሳቸውን የማብቃትና ለተሻለ ሀገራዊ ኃላፊነት ዝግጁ የመሆን ተልዕኳቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በአዋጅ ወደ ትምህርት የከፍተኛ ትምህርት ተቋምነት ከተዛወረበት መስከረም 2014 ወዲህ ተቋማዊ ለውጥና ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል።

የዩኒቨርሲቲውን ምስረታና ቀጣይ ተልዕኮ በሚመለከት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብትና ቴክኖሎጂ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች፣ ከምሁራን እንዲሁም ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ጋር እየመከረ ይገኛል።

በአቡ ቻሌ


ትክክለኛውን የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዲጂታል ሚዲያ የትስስር አውታሮችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑን!
YouTube ➲ http://bit.ly/3itThRr
Telegram ➲ http://bit.ly/3W4puw9
Facebook ➲ https://bit.ly/3CJVgI8
Twitter ➲ http://bit.ly/3IKQ3TZ

13.1K views08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-30 16:15:55 https://telegra.ph/AAMN-09-30
12.8K views13:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-28 19:30:39
ነዋሪነታቸውን ብራይተን ያደረጉ የቀድሞ የእንግሊዝ አትሌቶች በአትሌት ሀይሌ ገ/ስላሴ ስም ቡና ማቅረብ ጀመሩ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ(ኤ ኤም ኤን )መስከረም 17/2016 ዓ.ም
በብራይተን ነዋሪነታቸውን ያደረጉ የቀድሞ እንግሊዝ አትሌቶች በኢትዮጵያዊው ጀግናው አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ ስም "ሀይሌ ኮፊ" የተሰኘ ቡና ለሯጮች መሸጥ መጀመራቸው ተገልጿል።

"ሀይሌ ኮፊ" የሚል ስያሜን ያገኘው ይህ ቡና በቀድሞ የእንግሊዝ የማራቶን ሯጭ ሪቻርድ ኔራርከር ፣ጆየል ኪድገር እና ስፔንሰር ቶማስ ሀሳብ አመንጪነት ለገበያ መቅረቡ ታውቋል።

ሪቻርድ ኔራርከር ዘጠኝ አመታትን በአዲስ አበባ በቆየበት ወቅት ከኦሎምፒክ ሻምፒዮኑ ሀይሌ ጋር በነበረው ቅርበት ይህ የቢዝነስ ሀሳብ ሊመጣ እንደቻለ ተገልጿል።

"ቡና በኢትዮጵያውያን ባህል ውስጥ ትልቅ ቦታ አለው" ያለው ኔራርኩር ሀይሌ በአለም አቀፍ አትሌቲክስ ያለውን ስም በመጠቀም ቡናን ለሚያዘወትሩ ለአትሌቶች "ሀይሌ ኮፊን" እንደሚያቀርብ መግለፁን አትሌቲክስ ዊክሊ ዘግቧል ።

የቀድሞ የኦሎምፒክ ማራቶን ሯጭ የነበረው ኔራርኩር የአትሌቲክስ ውድድሮችን የሚያዘጋጅ ሲሆን ኪድገር በ800 ሜ ለእንግሊዝ ተወዳድሯል።አሁን ላይ በአሰልጣኝነት እየሰራ እንደሚገኝ መረጃው ያሳያል።

ሌላኛው የቀድሞ አትሌት ቶማስ በ2019 በ800 ሜ አትሌቲክስ ውድድር ሻምፒዮን መሆን ችሏል።


ትክክለኛውን የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዲጂታል ሚዲያ የትስስር አውታሮችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑን!
YouTube ➲ http://bit.ly/3itThRr
Telegram ➲ http://bit.ly/3W4puw9
Facebook ➲ https://bit.ly/3CJVgI8
Twitter ➲ http://bit.ly/3IKQ3TZ
13.4K views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-26 12:53:55
13.7K views09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-06 16:50:23 https://telegra.ph/Health-staff-09-06
13.4K views13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-03 11:32:27 https://telegra.ph/%E1%8B%98%E1%88%98%E1%8A%95-%E1%8A%A0%E1%8D%88%E1%88%AB%E1%88%B9-%E1%8B%A8%E1%8A%A0%E1%88%AD%E1%89%B5%E1%88%AE%E1%88%B5%E1%8A%AE%E1%8D%92-%E1%88%85%E1%8A%AD%E1%88%9D%E1%8A%93-09-03
13.8K views08:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-28 12:23:11
15.4K views09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-27 23:31:43
19ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዛሬው ዕለት
ፍፃሜውን አግኝቷል።

በሃንጋሪ ቡዳፔስት ሲካሄድ የቆየው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ውድድር በዛሬው ዕለት ማምሻውን በተከናወኑ ውድድሮች ፍፃሜውን ሲያገኝ አሜሪካ በ12ወርቅ በ8 ብር እና በ9 የነሐስ በድምሩ በ29 ሜዳሊያዎች በቀዳሚነት አጠናቅቃለች።

ካናዳ በ 4 የወርቅ እና በሁለት የብር በድምሩ በስድስት ሜዳሊያዎች በሁለተኛነት ስታጠናቅቅ ስፔን በ4 የወርቅ እናት በ1 የብር በድምሩ በ5ሜዳሊያዎች 19ኛውን የቡዳፔስት የዓለም አትሌቲክስን ውድሩን በሶስተኛነት አጠናቅቃለች።

ኢትዮጵያ በ2 ወርቅ ፣ በ4 ብር እና በ3 የነሃስ በድምሩ በ9 ሜዳሊያዎች ከዓለም ስድስተኛ ከአፍሪካ ደግሞ ተቀናቃኟ ኬኒያን ተከትላ በሁለተኛነት ጨርሳለች።
14.1K views20:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ