Get Mystery Box with random crypto!

የጸጋ ወንጌል

የቴሌግራም ቻናል አርማ abutjesys — የጸጋ ወንጌል
የቴሌግራም ቻናል አርማ abutjesys — የጸጋ ወንጌል
የሰርጥ አድራሻ: @abutjesys
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 376

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-02-19 18:06:38
77 viewsD Tz, 15:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 14:58:07 *“ከዓለም አይደሉም!”*

#እነዚህ ከ2000 ዓመታት በፊት በዓለም የነበረው፣ ነገር ግን ከዓለም ያልሆነው ኢየሱስ፣ ይህችን ምድር ትቶ ከመሄዱ በፊት፣ በዚህ ትቷቸው ሊሄድ ስላሉት የአብ ስጦታዎቹ ያቀረበው ልመና ውስጥ ያሉ ውብ ቃላት ናቸው!  

> ኢየሱስ በምድር ሲመላለስ የነበረበት ማንነት ከእርሱ መሄድ በኃላ ክፍት ሆኖ አልቀረም፤ ያ ቦታ በብዙ የሞቱ ፍሬዎች ተይዟል፡፡ እርሱ የኖረበት ሕይወት የብዙ ቢሊየኖች ሕይወት ሆኗል፡፡

> አዎን፣ ኢየሱስን ከዓለም ጋር ምንም የሚያገናኘው ነገር አልነበረም፤ የለምም፡፡ የእርሱ ለሆኑትም ይህ እውነት ነው፡፡ “በዓለም” እንጂ “ከዓለም አይደሉም”፡፡ ከዓለም ያልሆኑት እነዚህ በዓለም የሆኑበትም ብቸኛው ምክንያት፣ ኢየሱስን በዓለም እንዲሆን ያደረገው ምክንያት ነው፡፡ ጌታ እንዲህ አለ

“ወደ ዓለም እንደ ላክኸኝ እንዲሁ እኔ ወደ ዓለም ላክኋቸው” (ዮሐ.17፡18)

> አዎን፣ ከዓለም ያልሆነው ክርስቲያን በዓለም የመሆን ምክንያቱ ስለተላከ ብቻ ነው!

> ታዲያ የዮሐ.17፡6-19 ኢየሱስ ወደ አባቱ ያቀረበው ልመና ማጠንጠኛው፣ ከዓለም ያልሆኑት እና የእኔ የሚላቸው የአብ ስጦታዎቹ፣ በዓለም ሳሉ በተለያዩ ተጽህኖ ስር ወድቀው በተግባራዊ ምልልሳቸው ከዓለም የሆኑ መስለው እንዳይታዩ አብ ይጠብቃቸው ዘንድ ነው፡፡ እንዲህ ብሏል

1ኛ. ቁ.11 ላይ ቅዱስ የሆነው አብ ደቀመዛሙርቱ አንድ እንዲሆኑ፣ ማለትም ከዓለም የሆነው ነገር ገብቶ ዥንጉርጉር የሆነ መልክ እንዳይኖራቸው በስሙ እንዲጠብቃቸው፡፡

2ኛ. ቁ.15 ላይ ቅዱስ አብ ከየትኛው ከዓለም መስለው እንዲታዩ ከሚሰራ ክፉ እንዲከልላቸው

3ኛ. ቁ.17 ላይ ቅዱስ አባት የኢየሱስ የሆኑት ከመስመር ወጥተው ከዓለም ጋር እንዳይደባለቁ፣ ቅዱስ በሆነው ቃሉ ሁሌም ድንበራቸውን እንዲያውቁ እንዲያደርጋቸው ለምኗል፡፡

> በዚህ ሁሉ ላይ ደግሞ ቁ.19 እንደሚያስነብበን እኛ ከዓለም ናቸው የሚያስብል ሕይወት እንዳንኖር፣ ራሱ ኢየሱስ ስለ እኛ ራሱን ቀድሷል፤ ማለትም በላይ በአብ ቀኝ ተቀምጦ፡- እውነተኛ ስፍራችሁ እዚህ ነው በማለት በየቀኑ ዓይናችን ወደ ሰማይ ይነሳ ዘንድ የስበት ማዕከላችን ሆኗል፡፡

ይሄ ሁሉ ለምን?

> እኛ ከዛሬ 2000 ዓመታት በፊት ኢየሱስ የኖረውን ሕይወት እንድንኖር ነው! የጌታ ልመና ሁሌም ሕያው ነውና፣ በዚህ ጸሎት ኃይል ዛሬ ላይ ያለን አማኞች በሙሉ ከዓለም እንዳይደለን የሚናገር ሕይወት መኖር እንችላለን፡፡ አዎን “የኢየሱስ ሕይወት በሥጋችን መገለጥ” ይችላል (1ቆሮ.4፡10)፡፡

ታዲያ ለዚህ ማለትም ኢየሱስ ለአባቱ ላቀረበው ልመና መልሳችን ምንድን ነው? አሜን ነውን?
80 viewsJesus-my-Saviour, 11:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-12 06:18:00 እይታ 2
ባለፈው አማኝ ከእግዚኣብሄር ቃል ውስት መንፈሳዊ እርስት እንዳሉት እና ፍለጋውን ካጠናከረ እነዚህን እርስቶች አንደሚወርስ ተመልክተን ነበር ያበካነው።
ታዲያ ዛረ ደግሞ ከዚያው ከጥለን እርስቶቹ ምን አንደሆኑ እንመለከታለን።
የመጀመሪያው እርስታችንም ሰላም ነው። በጌታ ስለተሰጠን ሰላም ሲበራልን ከፍርሃት ነፃ እንወጣለን፡፡
እንደዚሁም በመዝሙር ምዕራፍ 91፥1 የዳዊት የምስጋና መዝሙር። በልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ ያድራል። 2 እግዚአብሔርን። አንተ መታመኛዬ ነህ እለዋለሁ፤ አምላኬና መሸሸጊያዬ ነው፥ በእርሱም እታመናለሁ። 3 እርሱ ከአዳኝ ወጥመድ ከሚያስደነግጥም ነገር ያድንሃልና። 4 በላባዎቹ ይጋርድሃል፥ በክንፎቹም በታች ትተማመናለህ፤ እውነት እንደ ጋሻ ይከብብሃል። 5 ከሌሊት ግርማ፥ በቀን ከሚበርር ፍላጻ፥ 6 በጨለማ ከሚሄድ ክፉ ነገር፥ ከአደጋና ከቀትር ጋኔን አትፈራም። 7 በአጠገብህ ሺህ በቀኝህም አሥር ሺህ ይወድቃሉ፤ ወደ አንተ ግን አይቀርብም። 8 በዓይኖችህ ብቻ ትመለከታለህ፥ የኃጥኣንንም ብድራት ታያለህ። 9 አቤቱ፥ አንተ ተስፋዬ ነህና፤ ልዑልን መጠጊያህ አደረግህ። 10 ክፉ ነገር ወደ አንተ አይቀርብም፥ መቅሠፍትም ወደ ቤትህ አይገባም። 11 በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ 12 እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። 13 በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። 14 በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ። 15 ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ አከብረውማለሁ። 16 ረጅምን ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ።
ይህን የቃለ እውነቶች በእምነት ከውስጥ ሰውነታችን ጋር ስናዋህደው ስጋት ከህይወታችን ይገፈፋል፡፡ ምክኒያቱም እንዱህ ተብል ተጽፎአሌና፡፡
“እውነትን ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል” (ዮሐ 8፤32) ይህ እውነት ምንም እንኳን ለአይሁድ ቢነገርም ዛሬም ይህ እውነት ለያንዳንዳችን ያስፈልገናል። ጌታ በምድር በነበረበት ዘመን የነበሩት የፈሪሳዊያን ችግራቸው ጌታን በእምነት ዓይናቸው አለማየታቸው ነበር በስጋዊ ነገር እየተመኩ በመንፈሳዊ ነገር ግን ክርስቶስ ስጋት የሆነባቸው። ክርስቶስንም ሳያስወግዱ ማረፍ ያካታቸው። ክርስቶስ ግን ሰላማቸው ነበር።
(ዮሐ 9፤39-41) ኢየሱስም። የማያዩ እንዲያዩ የሚያዩም እንዲታወሩ እኔ ወደዚህ ዓለም ለፍርድ መጣሁ አለ። ከፈሪሳውያንም ከእርሱ ጋር የነበሩት ይህን ሰምተው። እኛ ደግሞ ዕውሮች ነንን? አሉት። ኢየሱስም አላቸው። ዕውሮችስ ብትሆኑ ኃጢአት ባልሆነባችሁም ነበር፤ አሁን ግን። እናያለን ትላላችሁ፤ ኃጢአታችሁ ይኖራል። የነዚህ ሰዎች ሰላም ማጣት በራሳቸው መመካት ነበር። እውርም ሆነው ሰላማቸውን ማየት አቃታቸው። እኛስ ወገኖች?
ዛሬም ጌታ የውስጥ ዓይናችንን በከፈተው ቁጥር ከቃል የምንወርሳቸው ብዙ ርስቶች አሉን፡፡ ልክ አብርሃም “በምድሪቱ በርዝመቷ ተመላለሰ” እንደተባለ በቃል ምድር ላይ ተነስተን በርዝመቱ በቁመቱ ስንመላለስ በሌላ አባባል በመረዳት ባለጠግነት ስንሞላ (ቆሊስያስ 2፤2-3 ልባቸው እንዲጸናና፥ በፍቅርም ተባብረው በማስተዋል ወደሚገኝበት ወደ መረዳት ባለ ጠግነት ሁሉ እንዲደርሱ የእግዚአብሔርንም ምሥጢር እርሱንም ክርስቶስን እንዲያውቁ እጋደላለሁ።
የተሰወረ የጥበብና የእውቀት መዝገብ ሁሉ በእርሱ ነውና። 2ኛ ጴጥ 3፤18 ነገር ግን በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ። ለእርሱ አሁንም እስከ ዘላለምም ቀን ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን።) ከጌታ ብዙ ርስቶችን እንወርሳለን፡፡ በቃል ውስጥ ብዙ መንፈዊ ርስቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ፡- የመለኮታዊ ሰላም ርስት ፣ የመለኮታዊ ጤንነት ርስት ፣ የመለኮታዊ ጥበቃ ርስት ፣ የመለኮታዊ መከናወን ርስት ፣ የመለኮታዊ ሞገስ ርስትና ሌሎች ርስቶችን ከቃሉ ዓይተን ስንወርሳቸው በሕይወታችን ላይ ይንፀባረቃሉ፡፡ ቃለን የጌታ መንፈስ ሲያበራሌን ያኔ በውስጣችን የበራው የቃለ ፍቺ ያለማወቅን ጨለማ ይገፋል፡፡ “የቃሉን ፍቺ የበራል” (መዝ 119፤130) የውስጥ ዓይናችን ጤናማ የሚሆኑት የቃሉን ዕውነት በሙላት ሲመለከቱ ነው፡፡
ያኔ የጨለማ ቁራጭ በኑሮአችን በሕይወታችን በቤታችን አይኖርም፡፡ ያ ያላየነው እንደዚሁም ያላወቅነው ነገር ያ ለእኛ የጨለማ ቁራጭ ነው። ስለዚህ በየእለቱ በቃሉ ሙላት ወደፊት እንዘርጋ።
ይከትላል፠፠፠፠፠


ጸጋና ሰላም ይብዛልን!!!!!!!!!
17 viewsErmi, 03:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 17:26:34 Sharing File...
66 viewskoreb, 14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 14:11:00 እውነተኛ ጸሎት የፊት ገፅታን ሁሉ ይለውጣል!!!

“ ፊትዋም ከእንግዲህ ወዲያ አዘንተኛ መስሎ አልታየም።” 1ኛሳሙ.1፥18
76 viewsJesus-my-Saviour, 11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 17:36:37 ይህ የዘጸአት ትረካ ምዕራፍ ሶስት ክፍል አንድ ነው
40 viewskoreb, 14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 17:35:12 Sharing File...
40 viewskoreb, 14:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 20:37:55 ይህ ምዕራፍ ሁለት በክላሲካል ነው! ነገ ምዕራፍ ሶስት በየ5 ደቂቃ እንደቀድሞ መቅረቡ ይቀጥላል።
73 viewskoreb, 17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 16:32:08 እይታ
ዘፍ 13፥14 “ ሎጥ ከተለየው በኋላም እግዚአብሔር አብራምን አለው። ዓይንህን አንሣና አንተ ካለህበት ስፍራ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ ወደ ምሥራቅና ወደ ምዕራብ እይ፤ 15 ፤ የምታያትን ምድር ሁሉ ለአንተና ለዘርህ ለዘላለም እሰጣለሁና። 16 ፤ ዘርህንም እንደ ምድር አሸዋ አደርጋለሁ፤ የምድርን አሸዋን ይቈጥር ዘንድ የሚችል ሰው ቢኖር ዘርህ ደግሞ ይቈጠራል። 17 ፤ ተነሣ በምድር በርዝመትዋም በስፋትዋም ሂድ እርስዋን ለአንተ እሰጣለሁና። 18 ፤ አብራምም ድንኳኑን ነቀለ መጥቶም በኬብሮን ባለው በመምሬ የአድባር ዛፍ ተቀመጠ፤ በዚያም ለእግዚአብሔር መሠውያን ሠራ።
ስንቶቻችን ነን መለየት አቅቶን ተደባልከን ያለን አብርሃም የእግዚኣብሄርን ምሪት ለማግኘት መለየት ነበረበት።
በእግዚአብሄር መለኮታዊ ጥሪ ከሀገሩና ከዘመዱ ተለይቶ የወጣው አብርሃም
የሚወርሰው የምድር ስፋት የሚለካው “ባየው” ልክ ነበር፡፡ አብርሃም ትወርሳለህ
የተባለው አንድ ጂኦግራፊካዊ ምድር ብቻ ነበር፡፡
በአዲስ ኪዳን የሰማያዊ ጥሪ ተካፋዮች ለሆነው ለእኛ ግን አሁን የሚሰጠን
ጂኦግራፊካዊ ምድር ወይም አንድ የመሬት ርስት ሳይሆን ነገር ግን የሚሰጠን ወይንም
ሌንወርሰው ያለ ርስት ጌታ በመስቀለ አማካኝነት ያስገኘልንን በዚህም ቁሳዊ አለም
ሊገለጡ የሚችሉት መንፈሳዊ ርስቶችን ነው፡፡
የእነዚን መንፈሳዊ ርስቶች የሚገኙበትና የሚወርሱበት ብቸኛ መንገድ የልቦናችን
ዓይኖች ሲበሩና በእምነት ዓይን ሲታዩ ነው፡፡
በክርስቶስ የመስቀለ ስራ (በሞቱና በትንሳኤው) የተገኙት እነዚህ መንፈሳዊ
በረከቶች በልቦናው ዓይኑ ያየ ይወርሳቸዋሌ፡፡
በመፅሐፍ ቅዱስ የመውረስ ህግ አለ፡፡ ያም “አምነህ ብታይ” የሚል ህግ ነው፡፡
ኤልሳ ሁለት እጥፍ በአንተ ላይ ያለውን መንፈስ በማለት ሲጠይቅ? ያገኝ ዘንድ በትጋት የኤሌያስን እንቅስቃሴ ማየት ነበረበት፡፡
ኤሌያስ አለው “ብታይ” ይሆንልሀል አለው፡፡ (2 ነገስት 2፤10)
ለአብርሃም የምታያትን ምድር ሁለ ለአንተ እሰጣለሁ ተባለ፡፡ በሌላ አባባል
አብርሃም ሊወርሰው የሚችለው ባየው ልክ ወይንም የአብርሃም የርስት ስፋት ያየውን
ያህል ነው፡፡
እኛ የዘላለም ሕይወት ያገኘነውና የዳነው ክርስቶስ በከፈለው ዋጋ ቢሆንም ስለ ደህንነት በቃል
አማካኝነት በውስጣችን ስለበራልንና ውስጣዊ ዓይናችን ይህንን እውነት ወይም ቃል
ስለተመለከተ ነው፡፡
ስለ ደህንነት በውስጥ ዓይናች ያን መረዳት ባናይ ዛሬ ባልዳንን ነበር፡፡
ልክ እንደዚሁ በቃል አማካኝነት የሕሊናችን ወይም የልቦናችን ዓይኖች ሲበሩ ብዙ እስከ ዛሬ ያላስተዋልናቸው
መንፈሳዊ ርስቶችን ከቃሉ እናገኛለን። ከእኛ የሚጠበከው በመጸሃፍ ቅዱስ ርዝመትና ስፋት እይታችንን አስተካክለን መራመድ ብቻ ነው።
ይቀጥላል . . .


ጸጋና ሰላም ይብዛልን!!!!
90 viewsErmi, 13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 12:42:04 Sharing File...
86 viewskoreb, 09:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ