Get Mystery Box with random crypto!

የጸጋ ወንጌል

የቴሌግራም ቻናል አርማ abutjesys — የጸጋ ወንጌል
የቴሌግራም ቻናል አርማ abutjesys — የጸጋ ወንጌል
የሰርጥ አድራሻ: @abutjesys
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 376

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-03-02 10:44:05
ሕይወት ያለ ኢየሱስ ከንቱ ነው!
የአባቴን ፈቃድ #የሚያደርጉ እንጄ ጌታ ሆይ ጌታሆይ የሚሉኝ ሁሉ .... ማቴ 7:21
59 viewsD Tz, 07:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 18:04:52 Sharing File...
105 viewskoreb, 15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 11:50:25 ሰላም እንዴት ናችሁ በተከታታይ ሲተላለፍ የነበረው የዘጸአት ትርጓሜ ትረካ የኔትወርክ አቅርቦት በመዘጋቱ ምክንያት ለሁለት ሳምንት ሳይተላለፍ ቆይቷል! ሆኖም ግን አሁን ላይ "Vpn" ብዙዎች እየተጠቀሙ በመሆኑ ከዛሬ ጀምሮ ትረካው የሚቀጥል መሆኑን ልገልፅላችሁ እወዳለሁ።
104 viewskoreb, edited  08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 10:48:26
የአባቴን ፈቃድ የሚያደርጉ እንጂ...
51 viewsD Tz, 07:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 08:46:52 እይታ 3
የሰውነትህ መብራት ዓይንህ ናት፡፡ ዓይንህ ጤናማ በሆነች ጊዜ ሰውነትህ ሁለ
ደግሞ ብሩህ ይሆናል ፡፡ ዓይንህ ታማሚ በሆነች ጊዜ ግን ሰውነትህ ደግሞ የጨለመ
ይሆናል፡፡ እንግዲህ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ እንዳይሆን ተመልከት፡፡ እንግዲህ
ሰውነትህ ሁለ የጨለማ ቁራጭ የሌለበት ብሩህ ቢሆን መብራት በደመቀ ብርሃን
እንደሚያበራልህ በጭራሽ ብሩህ ይሆናል (ለቃስ 11፤34-36) የጨለማ ቁራጭ በህይወታችን የማይኖረው ወይንም የጠላት ተጽኖ በህይወታችን
የማይኖረው ፍጹም ሙሉ በሙሉ የልቦናችን ዓይኖች ተከፍተው የጌታን የማዳኑን
ስራን በእምነት ስንቀበልና እደዚሁም ክርስቶስ ከሞት በመነሳቱ የተረጋገጠልንን ርስት
ስናይ ነው “ስለዚህም እርሱን ከሙታን በማስነሳቱ ሁሉን አረጋግጦአል” (ሐዋ 17፤ 30 እንግዲህ እግዚአብሔር ያለማወቅን ወራት አሳልፎ አሁን በየቦታቸው ንስሐ ይገቡ ዘንድ ሰውን ሁሉ ያዛል፤ 31 ቀን ቀጥሮአልና፥ በዚያም ቀን ባዘጋጀው ሰው እጅ በዓለሙ ላይ በጽድቅ ሊፈርድ አለው፤ ስለዚህም እርሱን ከሙታን በማስነሣቱ ሁሉን አረጋግጦአል። 32 የሙታንንም ትንሣኤ በሰሙ ጊዜ እኵሌቶቹ አፌዙበት፥ እኵሌቶቹ ግን። ስለዚህ ነገር ሁለተኛ እንሰማሃለን አሉት)።
ጌታ ከሞት በመነሳቱ ማናቸውም መንፈሳዊና ሰማያዊ በረከቶች እርግጠኝነትን
አግኝተዋል፡፡ እግዚአብሔር አብ ክርስቶስን ከሞት በማስነሳቱ ለእኛ ርስታችንን
አረጋግጦልናል፡፡
በጌታ መነሳት የተረጋገጠልን መንፈሳዊ ርስቶችን እንወርስ ዘንድ የልቦናችን
ዓይኖች ሊበሩ ይገባል (ኤፌሶን 1፡17-17 የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። 18 -19 ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤
ቃሉን በማንበብ እለት እለት እንትጋ ይቀጥላል.. .


ጸጋና ሰላም ይብዛልን!!!!!
57 viewsErmi, 05:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 08:17:46
የአባቴን ፈቃድ የሚያደርጉ እንጂ...
39 viewsD Tz, 05:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-25 09:38:46
ፈቃዱን ማድረግ ==> ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ
43 viewsD Tz, 06:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 04:47:57
በክርስቶስ አንድ አካል
57 viewsD Tz, 01:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 10:27:58
24 viewsD Tz, 07:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 12:54:56 #ዳዊት በፍልስጥኤማውያን ምድር!

(1 ሳሙ 27 )
------------
1 ዳዊትም በልቡ፦ አንድ ቀን በሳኦል እጅ እጠፋለሁ፤ ወደ ፍልስጥኤማውያንም ምድር ከመሸሽ በቀር የሚሻለኝ የለም፤ ሳኦልም በእስራኤል አውራጃ ሁሉ እኔን መሻት ይተዋል፥ እንዲሁም ከእጁ እድናለሁ አለ።
2  ዳዊትም ከእርሱም ጋር የነበሩት ስድስቱ መቶ ሰዎች ተነሥተው ወደ ጌት ንጉሥ ወደ አሜህ ልጅ ወደ አንኩስ አለፉ።

☞ አካሄዱን ሁሉ በማስተዋል ያደርግ የነበረውና እግዚአብሔር እንደልቤ ያለው ዳዊት ከሳኦል እጅ ለመዳን የእግዚአብሔርና የእግዚአብሔር ህዝብ ጠላት ወደ ሆነው ወደ ፍልስጤም መሸሹ ዳዊት ሙሉ በሙሉ ዓይንኑን ከአምላኩ ከእግዚአብሔር ማንሳቱና በራሱ መንገድ መሄዱን የሚገልጥ ነው።

☞ ታማኙ እግዚአብሔር ግን ዳዊት በምድረበዳ እንኳን ሳይቀር ለሳኦል እጅ አሳልፎ አልሰጠውም ነበር!

" ዳዊትም በምድረ በዳ በአምባ ውስጥ ይኖር ነበር፥ ከዚፍ ምድረ በዳም ባለው በተራራማው አገር ተቀመጠ፤ ሳኦልም ሁልጊዜ ይፈልገው ነበር፥ እግዚአብሔር ግን በእጁ አሳልፎ አልሰጠውም።"
(1 ሳሙ 23: 14)

☞ ዳዊት በራሱ መንገድ በሄደ ጊዜ ወደ ፍልስጤኤም ምድር መሸሽ ብቻ ሳይሆን ለፍልስጤኤም ንጉሥ ራሱን #ባሪያ እስክያደረግ ድረስና ከፍልስጤኤም ጋር በመተባበር ከእግዚአብሔር ህዝብ ጋር ለመዋጋት እስኪደፍር ድረስ #ውድቀቱ ተገለጠ(1 ሳሙ 28 ፥1–2)።

☞ እግዚአብሔር ግን ባሪያውን ዳዊት እንደገና በምሕረቱ ተገናኘው የዳዊት ልብ #በእግዚአበሔር #በረታ!(1ሳሙ 30፥ 6) እግዚአብሔርም በጠላቶቹ ላይ ድልን ሰጠው ከዚያም በኋላ እግዚአብሔር ለዳዊት በመንገዱ  ሁሉ ድልን ሰጠው ፣በእስራኤል ሁሉ ላይ ይነግሥ ዘንድና በእስራኤል ላይ ፍርድንና ጽድቅ ያደርግ ዘንድ እ/ር ምህረቱንና ጸጋውን አበዛለት!

(2 ሳሙ 8 )
------------
14 በኤዶምያስ ሁሉ ጭፍሮች አኖረ፥ ኤዶማውያንም ሁሉ ለዳዊት ገባሮች ሆኑ፤ እግዚአብሔርም ዳዊት በሚሄድበት ሁሉ ድልን ሰጠው።
15 ዳዊትም በእስራኤል ሁሉ ላይ ነገሠ፤ ዳዊትም ለሕዝቡ ሁሉ ፍርድንና ጽድቅን አደረገላቸው።

☞ #በክርስቶስ ኢየሱስ ያላችሁ ቅዱሳን ሁሉ ሁሌም ቢሆን የገዛ መንገዶቻችን በኃፍረትና በውድቀት የተሞሉ ናቸው ከዚያም ባሻገር ትናንትና ስንወዳቸው በነበሩ ወንድሞችና እህቶች ላይ ጠላት ሆነን እንነሳለን! እግዚአብሔር ግን የእንደገና አምላክ ነው ፥ በእውነት ከተመለሥን ከውድቀታችን ሊያነሣን #የታመነ ነው።

☞ ሁሉ ጊዜ የእግዚአብሔር ሙላት የሆነውን ጌታ ኢየሱስ እንድንመለከት እግዚአብሔር ጸጋውን ያብዛልን! አሜን።
63 viewsYemane H/mariam, 09:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ