2022-06-28 10:57:05
ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግስት.....
"ሰዎች ሰው የሞተው ሲወለድ ነው ይላሉ " ማለት ከናቱ ሆድ ወጥቶ ይህን አለም ሲቀላቀል ።ወደ እዚህ ምድር ሲመጣ ከዚያች ቀን ጀምሮ ጉዞ ወደ ሞቱ/ ወደ ፍፃሜው/ ያደርጋል ። ወደ እዚህ ምድር የመጣ የትኛውም ፍጥረት ፍፃሜው በሞት ነው ። ሞት ለሰው ልጆች ሁሉ አንድ ጊዜ የተመደበ የሀጥያት ዋጋ/ ደሞዝ/ ነውና ሰው ሁሉ መሞቱ አይቀሬ ነው ። እግዚአብሔር በሰው ልብ ውስጥ ዘላለማዊነትን ስላስቀመጠ ሰው እስከመጨረሻ ስስትንፋሱ ድረድ በጣር ውድጥ ሆኖ እንኳን ወደ ሞት የሚሄድ አይመስለውም ። ነገር ግን ሁሉ ይሞታሉ። እግዚአብሔር ግን እንደ ፈጣሪነቱና እንደ አምላክነቱ በሰዎች ላይ በሀጥያታቸው ምክንያት የሞት ፍርድን / ቅጣትን/ መስጠትን ብቻ አልወደደም እንደ ፍታዊነቱ ሀጥያትን ቀጥቶ ሀጥያተኛውን ማዳን መረጠ ። በዚህ ምክንያት የገዛ ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጅ ሁሉ ምትክ ሆኖ ፍርድን ተቀበለ ። የሰው ልጅ ከሚያስጨንቀውና ከሚያስፈራው ሞት በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ማምለጥ ሆነለት። ሞት መሻገሪያ እንጂ መኖርያ አልሆነለትም። ክብር ከጌታችን ይሁን።
111 views🇲 u🇱 🇪 🇷, 07:57