Get Mystery Box with random crypto!

የጸጋ ወንጌል

የቴሌግራም ቻናል አርማ abutjesys — የጸጋ ወንጌል
የቴሌግራም ቻናል አርማ abutjesys — የጸጋ ወንጌል
የሰርጥ አድራሻ: @abutjesys
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 376

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 26

2022-07-11 21:41:27 Watch "የቤተክርስቲያን ስያሜ፣ ምስረታ እና መገለጫ" on YouTube


23 viewsTsegaye Tezazu, 18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 07:08:00 " በዚያም ዘመን የእግዚአብሔር ቃል ብርቅ ነበረ፤ ራእይም አይገለጥም ነበር።"(1ሳሙ. 3:1፤)
"የእግዚአብሔርም ቃል ገና አልተገለጠለትም ነበር።"(1 ሳ.3:7፤)
"ዔሊም እግዚአብሔር ብላቴናውን እንደ ጠራው አስተዋለ።"(1ሳሙ. 3:8፤)
"ዔሊም ሳሙኤልን። ሄደህ ተኛ ቢጠራህም። አቤቱ፥ ባሪያህ ይሰማልና ተናገር በለው አለው።"(1ሳሙ.3:9፤)
ዘመኑ ዘመነ መሳፍንት ነበርና ሰው ሁሉ በፊቱ መልካም መስሎ የታየውን ያደርግ ነበር። እግዚአብሔር ሰውን ለገዛ መንገዱ የተወበት ወቅት ነበር። የእግዚአብሔር ቃል ብርቅ ነበር ሲባል እንዴት አሳዛኝ ጊዜ እንደሆነ ያሳያል። ምክንያቱም የእግዚአብሔር ሕዝብ ያለ ቃሉ ምን ብርሃን አላቸው ?፣ያለ ቃሉ ምንስ ዓይን አላቸው። ቃሉ ከተሰወረባቸው በሚያሳዝን ጥፋት ውስጥ እንዳሉ ያስረዳል። ሊቀ ካህኑም ማየት ተስኖታል። እግዚአብሔር ቃሉን የገለጠበት ዘንድ የታመነ ሰው ይፈልጋል። የተሰጠው ቃል ወይም የተሰጠው ፀጋ እግዚኣብሔር ይከበርበት፣ ነፍሳት ይባረኩበት ዘንድ የሚያውለው ጌታ ታማኝ ሠራተኛ ይፈልጋል። አሁን ያለንበት ጊዜ እንደ ዘመነ መሳፍንት ሁሉም መልካም ነው ያለውን የሚያደርግበት ጊዜ ነው። እግዚአብሔር ፈቃድ የተካዳበት የሰው ፍላጎት የገነነበት ሁኔታ እናያለን። ጌታ ለሚገልጥልን የቃሉ ብርሃን እንታዘዝ ፣ ከልምምድ ይልቅ ቃሉ ይምራን። "መጽሐፍስ ምን አለ? "(ሮሜ4:3፤)
የሚለው ቃል የሕይወታችን መርህ እናድርገው። እንዴት እናምልክ? እንዴት አናገልግል? እንዴት ህብረት እናድርግ?ወዘተ.. ለጥያቄዎቻችን ሁሉ መለስ "መጽሐፍስ ምን አለ?" ካልን በመለኮታዊ መለስ እንባረካለን፣ ከቃሉ ለውጡ የተመሰከረላቸው ልምምዶች ቢኖሩን የዘመነ መሳፍንት ሰዎች ከመሆን አናመልጥም። ያ ደግሞ ቃሉን እንዲሰወርበት የተተወ ትውልድ ነበር ።
56 viewsTsegaye Tezazu, 04:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 20:53:51 * በእግዚአብሔር ፊት አለመፍጠን! *

" እግዚአብሔር በሰማይ፥ አንተም በምድር ነህና በአፍህ አትፍጠን፥ በእግዚአብሔርም ፊት ቃልን ይናገር ዘንድ ልብህ አይቸኵል፤ ስለዚህም ቃልህ ጥቂት ትሁን። "
(መጽሐፈ መክብብ 5:2)

> መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚያምኑ ሰዎች ሆነው ነገር ግን ዘግናኝ ነገር ከፈፀሙት መካከል፣ ዕብ፡11÷32 የእምነት አባት ሲል የጠራው ዮፍታሔ አንዱ ነው። ይህ ሰው እግዚአብሔር በአሞን ላይ ድል እንዲሰጠው ልመና ባቀረበ ወቅት እንዲህ ሲል ተስሎ ነበር

" ከአሞን ልጆች ዘንድ በደኅና በተመለስሁ ጊዜ፥ ሊገናኘኝ ከቤቴ ደጅ የሚወጣው ማንኛውም ለእግዚአብሔር ይሆናል፤ ለሚቃጠልም መሥዋዕት አቀርበዋለሁ ብሎ ለእግዚአብሔር ስእለት ተሳለ።"
(መጽሐፈ መሳፍንት 11:31)

#ዮፍታሔ ምን እያለ ነው? በእግዚአብሔር ፊት እየተናገረ ስላለው ነገር ልብ ብሏልን? "ሊገናኘኝ የሚወጣውን ለመሥዋዕት አቀርባለሁ" ማለት ምን ማለት ነው?

> መቼስ በብሉይ ለመስዋዕት የሚቀርቡት እንስሳ ወይም እህል አልያም ፈሳሽ ቁሶች ናቸው። እነዚህ ደግሞ ዮፍታሔ አሸንፎ ሲመጣ "ሄደን እንገናኘው" ሊሉ አይችሉም።

#ታዲያ ዮፍታሔ እየተናገረ ያለውን አስተውሎታል? ውጤቱ ምን ሆነ

> ቁ፡34 እንደሚናገረው ዮፍታሔን ልትገናኝ መጀመሪያ የወጣችው ብቸኛዋ ልጁ ሆነች።

#እና የተሳለው ምን ሊሆን ነው?

> እግዚአብሔር በከነዓን የነበሩትን ያጠፋቸው አንደኛው ዋና ምክንያት የሰው መሥዋዕት ስለሚያቀርቡ ነበር፤ እስራኤላውያንንም እንዲህ ያለ ነገር እንዳያደርጉት አጥብቆ አስጠንቅቋቸዋል (ዘሌ፡18÷21፣ ዘዳ፡12÷31)።

#ዮፍታሔ ምን ወሰነ?

>"እመልሰው ዘንድ አልችልም" አለ። ልጅም ለአባቷ በመገዛት መንፈስ ተስማማች። ከሁለት ወር በኋላ ሠዋት(ቁ፡39)።

#እንዴት ያለ ነገር ነው!

> ዮፍታሔ በእግዚአብሔር ፊት ሳያገናዝብ (ምናልባት በችኰላ) ስለት መግባቱ ጥፋት ሆኖ ሳለ፣ የጥፋቱን ጎደና፣ መፅሐፉ ስለትህን ፈፅም ይላል በሚል ብቻ ማስቀጠሉ ያሳዝናል። ያው መፅሐፍ እኮ የሰው መሥዋዕትን ይፀየፍ የለምን? ዮፍታሔ ያስተዋለው ከፊሉን ብቻ ነውን? ልጅስ አባቷ ከመፅሐፉ ውጭ ሲሆን ዝም ብላ መታዘዝ ነበረባትን?

> ጎረቤት፣ የአገር ሰው፣ ምናልባት ካህናቱ ዮፍታሔን ለምን አላስቆሙም? ዘሌ፡5÷4 እኮ ሳያስብ ለሚምል ንሥዓ እንዲገባ መንገድን አስቀምጦለታል። ያሳዝናል፣ የእምነት ሰው ዮፍታሔም፣ ልጁም፣ ሕዝቡም "ሰው በፊቱ መልካም መስሎ የታየውን ያደርግ ነበር" የተባለው የዘመነ መሳፍንት ሕይወት ገብቶባቸዋል።

#በጌታ ፊት ብቻ ሳይሆን በሰውም ፊት ቢሆን ከመናገር ዘግየት ማለትን ተመክረናል(ያዕ፡1÷19)። በእግዚአብሔር ፊት ልመናችንን፣ የምንገባውን ቃል ማስተዋል እንዴት መልካም ነው። ሳናውቀው የሚያጠፋንን የምንለምን እና ሳናስብ የሚያጠፋ ነገር ቃል የምንገባ ደካሞች ነንና ረጋ ማለቱ የተወደደ ነው። እንደ ፈቃዱ ያልሆነ ሁሉ ከሥጋ ነው።
65 viewsJesus-my-Saviour, 17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 18:09:43 * እግዚአብሔር ከእኔ ጋር! *

" … በሄድሁበትም መንገድ ከእኔ ጋር ለነበረው ለእግዚአብሔር መሠውያን አደርጋለሁ።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 35:3)

> ይህንን ቃል የተናገረው ያዕቆብ መሆኑንን ሳስብ ጥቂት ቆም ብዬ ራሴን እንድጠይቅ ያስገድደኛል። የያዕቆብን መንገድ ማሰላሰል ጀመርኩኝ። "በሄድኩበት መንገድ" እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነበረ ሲል ምን ማለቱ ነው? ያዕቆብ እየተናገረ ያለው ስለየትኛው መንገዱ ነው?

> ያዕቆብ የሚለው ስም በራሱ የሚናገረው ጥሩ አይደለም፤ የሥጋ አካሄዱን የሚያመለክት ነው። ከዘፍ፡25 ጀምሮ ያዕቆብ የሚታወቀው ነገሮችን በራሱ ብልጠት፣ ብልሃት አልፎም ተንኮልና ውሸት ለማግኘት የሚጥር ሰው ሆኖ ነው። የወንድሙን ደካማ ጎን ለራስ ጥቅም ያደረገ፣ አባቱን ያታለለና የዋሸ ይህ ሰው ጭንቅላቱን ከመተማመኑ የተነሳ ድርድር የሚወድ ሰው ነበር።

> ብኵርና የወሰደው፣ ከላባ ጋር 20ዓመት የኖረው፣ ሚስት ሳይቀር ያገባው በድርድር ነው። ሌላው ቀርቶ ዘፍጥ፡28 ላይ እንደምናየው ከእግዚአብሔር ጋር እንኳ ለመደራደር ጥያቄ ሲያቀርብ እናየዋለን። የቤተሰብ ሕይወቱም ብዙ አስደሳች አልነበረም። ከሚስቶቹ ጋር የነበረው የፉክክር ግንኙት እንዲሁም ጣዖት አምልኮ ቤቱ መኖሩ (ዘፍ፡35) አሳዛኝ ታሪኮች ናቸው።

#ስለ ራሱ ሕይወት የሰጠው ምስክርነት ይህ ነበር

" … የሕይወቴ ዘመኖች ጥቂትም ክፉም ሆኑብኝ …"
(ኦሪት ዘፍጥረት 47:9)

#አዎን፣ ያዕቆብ "በሄድኩበት መንገድ" እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነበረ ሲል ምን እያለን ነው? እግዚአብሔር እንዲህ ያለህ ደስ ከማይል፣ የራስ ፈቃድ በነገሰበት፣ የሥጋ አካሄድ ይጓዝ ከነበረው ሰው ጋር ነበርን?

> ዘፍ፡28 ላይ እግዚአብሔር ለያዕቆብ እንዲህ ብሎት ነበር

" እነሆም እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፥ በምትሄድባትም መንገድ ሁሉ እጠብቅሃለሁ፥ ወደዚችም ምድር እመልስሃለሁ፤ የነገርሁህን ሁሉ እስካደርግልህ ድረስ አልተውህምና።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 28:15)

#ለካ እግዚአብሔር የጠበቀንና ያልተወን የእኛን ሁኔታ አይቶ ሳይሆን ስለተስፋ ቃሉ የታመነ ስለሆነ ነው። ያዕቆብን እግዚአብሔር የጠበቀው ያዕቆብ ታማኝ ሆኖ ሳይሆን እርሱ ባይታመን እንኳ የታመነ ሆኖ የሚኖር አምላክ ስላለው ነበር (2ጢሞ፡2÷11)። ያዕቆብን ሊያጠፋ የተነሳው ላባ ለዚህ ምስክር ነው

" ክፉ አደርግባችሁ ዘንድ ኃይል ነበረኝ፤ ነገር ግን የአባታችሁ አምላክ ትናንት። ያዕቆብን በክፉ ነገር እንዳትናገረው ተጠንቀቅ ብሎ ነገረኝ።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 31:29)

> በራሴ ፈቃድ በተጋዝኩባቸው መንገዶች እግዚአብሔርን ማሳዘኔ ያስከፋኛል። አለመታዘዝን በመታዘዝ ተበቅዬ የቤቴል ሕይወትን መኖር መሻቴ ነው። ነገር ግን እስከዛሬ በሄድኩባቸው ብዙ መውደቅና መነሳቶች ባሉበት መንገዶቼ እርሱ ታማኝ ስሆነ ብቻ ጠብቆ ዛሬ ላይ ያደረሰኝን አምላኬን በማሳብ እኔም እንደ ያዕቆብ እንዲህ እላለሁ

" … በሄድሁበትም መንገድ ከእኔ ጋር ለነበረው ለእግዚአብሔር መሠውያን አደርጋለሁ።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 35:3)
106 viewsJesus-my-Saviour, 15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 16:42:24 🇲 🇺 🇱 🇪 🇷:

#እውነተኛ የፍጥረት መጋቢ እግዚአብሔር

#እግዚአብሔር የሁሉ መጋቢ ነው ። ፍጥረት ሁሉ የሚያስፈልገውን በሰአቱና በጊዜው የሚሰጥ ፣ በምድር ላይ ላለ ፍጥረት ሁሉ የሚያስብ ግሩም መጋቢ ነው እግዚአብሔር በዘመናት ሁሉ ፣ ለደሀ አደጉ የሚሟገት ለመበለቲቱ የሚፈርድ ፣ ለተጠቃውና ለተገፋው መከታ የሚሆን አምላክ እንደሆነ ከቅዱስ ቃሉ እንረዳለን ።
" ለድሃ አደጉና ለመበለቲቱ ይፈርዳል፥ መብልና ልብስም ይሰጠው ዘንድ ስደተኛውን ይወድዳል።" (ኦሪት ዘዳግም 10:18፤)

#እንደ እግዚአብሔር ለችግረኛ የሚያስብ የሚራራ የለም ። እርሱ ለፃድቁም ለሀጥሁም ዝናብን ያዘንባል ፣ ፀሀይን ያወጣል ፣ ቡቃያና ሰብሉን በወቅቱ ያበቅላል ሁሉን በጊዜው ይሰጣል ፣ ለፍጥረት ሁሉ ያለ አድልኦ መግቦትን ይመግባል ።

"15፤ የሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል፤ አንተም ምግባቸውን በየጊዜው ትሰጣቸዋለህ።" (መዝሙረ ዳዊት 145:15፤)

#ማንም በተጨነቀው ልክ አይኖርም እግዚአብሔር ስለ ፈቀደ ግን ይኖራል ። እርሱ ደግሞ የኛ የደካሞችን ሸክም መሸከም የሚወድ ቸር አምላክ ነው።

"7፤ እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።" (1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 5:7፤)

#ልባችንን በዚህ በተወደደ ጌታ ላይ እናፍስስ የሚያስጨንቀንን የትኛውም የኑሮ ውጣ ውረድ ለጌታ እናሳየው ። እርሱ መለወጥ ህይወትን ማበጀት፣ ደግሞም ችግርን መረዳት ፣ ለችግራችን መፍትሄ መስጠት ያውቅበታል ።

"53፤ የተራቡትን በበጎ ነገር አጥግቦአል፤ ባለ ጠጎችንም ባዶአቸውን ሰዶአቸዋል።" (የሉቃስ ወንጌል 1:53፤)
138 views🇲 u🇱 🇪 🇷, 13:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 13:39:54 * ክርስቲያን የት ይሰብሰብ? *

> በብሉይ ዘመን የእግዚአብሔር ሕዝብ የሚሰበሰበው ኢየሩሳሌም በሚገኘው መቅደስ ዙሪያ ነበር (ዘዳ፡12÷6፣ 1ነገ፡8÷15-22)። በዓመት ቢያንስ ወንድ የሆነ ሁሉ ኢየሩሳሌም ከመሄድ የማይቀርባቸው ሶስት በዓላት ነበሩ (ዘፀ፡23÷17)።

> ያ የሳባ ንግስት በውበቱ የተማረከችለት (1ነገ፡10÷4-5)፣ የጌታ ደቀመዛሙርት ውብና ጌጠኛ ብለው የጠሩት (ሉቃ፡21÷5) ከቁስ የተሰራው መቅደስ ብቸኛው እስራኤላውያኑ በእግዚአብሔር ፊት የሚገናኙበት የአምልኮ ስፍራ ነበር።

#አንድ ወንድም እንዳለው ለእስራኤላውያኑ የመሰባሰቢያው ማዕከል ቦታና ሕንፃ ከሆነ ለክርስቲያንስ?

> ጌታ ቦታና ሕንፃ ልቧን ለያዘው ሳምራዊቷ ሴት እንዲህ አላት

" ኢየሱስም እንዲህ አላት። አንቺ ሴት፥ እመኚኝ፥ በዚህ ተራራ ወይም በኢየሩሳሌም ለአብ የማትሰግዱበት ጊዜ ይመጣል።"
(የዮሐንስ ወንጌል 4:21)

#ጌታ እንደተናገረው የቦታና የሕንፃ ጉዳይ ብሉይ ላይ ካከተመ፣ ክርስቲያን የት፣ ምን ብሎ ሊሰበሰብ ነው?

> ያው ወንድም እንዳለው ክርስቲያን የመሰባሰቢያ ማዕከሉ ቦታ ሳይሆን ማንነት ነው። እርሱም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው

" ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና።"
(የማቴዎስ ወንጌል 18:20)

ተጨማሪ ምንባቦች፦1ቆሮ፡5÷3-4፣ ዕብ፡13÷13፣ 1ጴጥ፡2÷4 -5…

> በአዲስ ኪዳን የመሰብሰቢያ ማዕከላችን ጌታ ኢየሱስ ነው። ዛሬ ከቦታና ሕንፃ ጋር ጉዳይ የለንም። በክርስቶስ ዙሪያ በቤት፣ በተዘጋጁ አዳራሾች፣ በሜዳ፣ በዛፍ ሥር ወዘተ መሰብሰብ ይቻላል። ጉዳያችን "ወደ እርሱ እየቀረባችሁ" 1ጴጥ፡2÷4 ከተባለው ሕያው ማንነት ጋር እንጂ ከግዑዝ አካላት ጋር አይደለም።
113 viewsJesus-my-Saviour, 10:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 20:23:33 *የእምነት ጊዜ*

"10፤ ኢያሱም ሕዝቡን። እኔ። ጩኹ እስከምልበት ቀን ድረስ አትጩኹ፥ ድምፃችሁንም አታንሡ፥ ከአፋችሁም አንድ ቃል አይውጣ፤ በዚያን ጊዜ ትጮኻላችሁ ብሎ አዘዛቸው።"
(ኢያሱ 6:10፤)

እግዚአብሔር ለኢያሱ ያስተላለፈውን ይህን ትዕዛዝ ሳስብ ለምን እግዚአብሔር የዝምታውን ጊዜ አረዘመው? ብዬ አሰብኩኝ። ምክንያቱም የሚጮሁት አንድ ጊዜ ሲሆን በዝምታ እየዞሩ የሚያሳልፋት ደግሞ ስድስት ቀን ነውና!

ዕብራውያን 11፥30 ይህን ክፍል ሲገልጠው እንዲህ ይላል……

"30፤ የኢያሪኮ ቅጥር ሰባት ቀን ከዞሩበት በኋላ በእምነት ወደቀ።"
(ዕብራ 11:30፤)

ምንአልባት ይህ ክፍል ሳይገባን "የዝምታው ጊዜ ትንሽ አረዘመም?!፤ለእግዚአብሔር ደግሞ የሚሳነው ነገር የለም……ታዲያ ለምን በአንድ ጊዜ ቅጥሩ አልፈረሰም?!" ብለን ይሆናል። ነገር ግን የስድስት የዝምታ ቀናቶች ቅሉ እምነት ሥራዋን እየሠራች ስለነበር ነው። ስለዚህ የሥራዋ ውጤት የኢያሪኮ ቅጥር ዳግም ላይሰራ እስከ ወዲያኛው አሰናበተው!

"20፤ ሕዝቡም ጮኹ፥ ካህናቱም ቀንደ መለከቱን ነፉ፤ ሕዝቡም የቀንደ መለከቱን ድምፅ በሰሙ ጊዜ ታላቅ ጩኸት ጮኹ፥ ቅጥሩም ወደቀ………"
( ኢያሱ 6:20፤)

አንድ ዘማሪ እንዲህ ሲል የተቀኘውን ቅኔ አስታውሳለሁ

*አንተን መጠበቅ ብዙ ትርፍ አለው
ለታገሰ ሰው ጸጋህ ላስቻለው
አንተን ጠብቆ ያፈረ የለም
በዚህ ምድር ቢሆን በወዲያኛው ዓለም
ከቶ አልተገኘም*

ወዳጆቼ ብዙዎቻችን እግዚአብሔርን አምኖ በትዕግስት ከመጠበቅ ይልቅ በችኮላና በጥድፊያ ድምፃችንን ማሰማት ይቀናናል። ነገር ግን እግዚአብሔርን አምነን በዝምታ ልንጠብቀው ይገባል። አንደበታችን ሳይሆን እምነት ብቻ ሥራዋን እድትሠራ ጊዜ ልንሠጥ ይገባናል። ያን ጊዜ ግዙፉ ተራራ ደልዳላ ሜዳ ይሆናል፤ባሕሩም የብስ ይሆናል፤ቅጥሩም ዳግም ላይሰራ ይወድቃል !

"26፤ በዚያን ጊዜም ኢያሱ። ይህችን ከተማ ኢያሪኮን ለመሥራት የሚነሣ ሰው በእግዚአብሔር ፊት ርጉም ይሁን፤ መሠረትዋን ሲጀምር በኵር ልጁ ይጥፋ፥ በርዋንም ሲያቆም ታናሹ ልጁ ይጥፋ ብሎ ማለ።"
(ኢያሱ 6:26፤)
124 viewskoreb, edited  17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 15:57:46 * "ፈቃድህ በምድር ትሁን!" *

#መቼ ይሆን የእግዚአብሔር ፈቃድ በምድር የሚሆነው?

> አሁን ያለው ዓለም ክፉ ነው። ምንም እንኳ እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ ነገሮች ገደባቸውን እንዳያልፉ ከጀርባ ቢቆጣጠርም፣ በፊት ለፊታችን እየሰራ የሚገኘው ግን የዚህ ዓለም ገዥ ሰይጣን ፈቃድ ነው። መላ ምድሪቱ በሰይጣናዊ ክፋት ከእለት ወደ እለት እየተጥለቀለቀች ነው።

#ታዲያ የሚሆነውን ጥፋት ስናይና ስንሰማ ጌታ እንደምሳሌ በተናገረው ፀሎት ውስጥ ያለው ቃል መቼ ይፈፀም ይሆን ያስብለናል

" … ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤"
(የማቴዎስ ወንጌል 6:10)

> በሰማይ ያለው የእግዚአብሔር ፈቃድ፣ ያ የእግዚአብሔር መሻት በአንድ ግለሰብ ላይ ወይም በአንድ ቤተሰብ ወይም በቤተክርስቲያን ውስጥ ብቻ ሳይሆን በምድር ላይ ሲሆን የምድር ገፅታ ምን ይመስል ይሆን!

#ለምድር በሰማይ ያለው የእግዚአብሔር ፈቃድ ምንድን ነው?

> ፈቃዱ ምድር በእግዚአብሔር ክብር (ዕን፡2÷14)፣ ፅድቅ (ኢሳ፡11÷4)፣ ሰላም (ኢሳ፡2÷1-5)፣ ጤና (ኢሳ፡65÷20-22)፣ የፍጥረት ስምምነት (ኢሳ፡11÷6-9)፣ ብልጥግና (ኢሳ፡35÷1-2) ወዘተ ተሞልታ ማየት ነው። ፍጥረት ከጥፋት ባርነት ነፃ ወጥቶ (ሮሜ፡8÷21)፣ ሰይጣን የሌለባት (ራዕ፡20÷1-3)፣ ፍትህ ከዳር ዳር የሰፈነባት (ዘካ፡5÷1-4) ምድር የእግዚአብሔር ፈቃድ የሰፈነባት ናት!

#ታዳያ ይህ መች ይሆናል? በእኛ ዘመን እንጠብቅን?

> መልሱ እዚያው ፀሎቱ ላይ አለ

" ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤"
(የማቴዎስ ወንጌል 6:10)

> አዎን በሰው መንግስት፣ ምናልባት፣ አዎን ምናልባት በጣም እጅግ ጥቂቱ የእግዚአብሔር ፈቃድ ይፈፀም ይሆናል። የእግዚአብሔር ፈቃድ በሙላት በምድርም የሚሆነው ግን የሰው ሳይሆን የራሱ የእግዚአብሔር መንግስት ስትመጣ ነው። ማቴ፡6÷10 የሚፈፀመው የእግዚአብሔር ንጉስ (መዝ፡2÷6) ሲነግስ ብቻ ነው። መቼም ቢሆን ኢየሱስ ሳይነግስ ምድር እፎይ ልትል አትችልም።
111 viewsJesus-my-Saviour, 12:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ