Get Mystery Box with random crypto!

የጸጋ ወንጌል

የቴሌግራም ቻናል አርማ abutjesys — የጸጋ ወንጌል
የቴሌግራም ቻናል አርማ abutjesys — የጸጋ ወንጌል
የሰርጥ አድራሻ: @abutjesys
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 376

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-03-12 21:30:25 Sharing File...
57 viewskoreb, 18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 11:22:24
የክርስቲያን
15 viewsD Tz, 08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 16:13:30 ፍቅርም እንደዚህ ነው!

1ኛ ዮሐንስ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁹ በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና።
¹⁰ ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም።

☞ ሰው ለቅዱሱ ለእግዚአብሔር ያለው የጠላትነትና ያለመታዘዝ ጫፍ የገለጠው አንዳች በደል የሌለበት ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ #ኢየሱስ_ክርስቶስ በመስቀል ይሞት ዘንድ በመፍረድ ነው(ማቴ 27፥ 20–26) እግዚአብሔር ደግሞ ፍቅሩ የገለጠው በዚህ ልክ ጠላትና ዓመጸኛ ለሆነው ለሰው ዘር በሙሉ አንድያ ልጁን #መድሀኒት እንዲሆን መስጠቱ ነው(ዮሓ3፥ 16–17)።

☞  በኃጢአት ምክንያት በቅዱሱ በእግዚአብሔር ፊት መቆም የማይቻለው ሰው የእግዚአብሔር ጽድቅ ሞት ያውጅበታል ነገር ግን ሰው በህይወት ይኖር ዘንድ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ለሰው ሁሉ መድሀኒት ይሆን ዘንድ ወደ ዓለም ላከው! #ኢየሱስም የሰው ሁሉ ኃጢአት ያስተሰርይ ዘንድ በዚያ መስቀል በመሞት ደሙን አፈሰሰ! —— #ፍቅርም_እንደዚህ ነው።

☞ አዎ የኃጢአት ደመወዝ የሆነውን ሞት በኢየሱስ በመስቀል ሞት ተከፍለዋል! #የሞት ኃይልም #በኢየሱስ ትንሣኤ ለዘላለም ተሽንፈዋል! በእርግጥም ኃጢአቱን ሁሉ በመናዘዝ ኢየሱስ ለእርሱ እንደሞተና እንደተነሳ #የሚያምን ሰው በሙሉ ከሞት ወደ #ህይወት ይሻገራል እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም #ያላመነ ግን #የዘላለም_እሳት ይጠብቀዋል። ጌታ ኢየሱስ ራሱ እንደተናገረው፦

“እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።”
  — ዮሐንስ 5፥24

— ዛሬም በኃጡአትና በሞት ጎዳና ያላችሁ ወገኖች ነፍሱን ስለ እናንተ እስከመስጠት ወደ ወደዳችሁ ወደ #ኢየሱስ ተመለሱ እርሱ ኃጢአታችሁ በሙሉ በደሙ አስወግዶታል! #በእርሱ እመኑ ለዘላለም #ከሞት ፍርድ ትድናላችሁ።

“እርሱም(#ኢየሱስ) የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት እንጂ።”
  — 1ኛ ዮሐንስ 2፥2
46 viewsYemane H/mariam, 13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 21:45:16 Sharing File...
24 viewskoreb, 18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 12:02:41
#የክርስቲያን #ማንነት
(ክፍል1/2)
32 viewsD Tz, 09:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 11:37:43 *የተረሳው የእግዚአብሔር ቃል አገልጋይ!*

" እስራኤልም ሁሉ ከዳን እስከ ቤርሳቤህ ድረስ ሳሙኤል ለእግዚአብሔር ነቢይ ይሆን ዘንድ የታመነ እንደ ሆነ አወቀ። "
(መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 3:20)

> ሳሙኤል የእግዚአብሔር ቃል ብርቅ በነበረበት ዘመን በእግዚአብሔር ቃል የተሞላ እና ለእስራኤል ሁሉ የሰማዩን ምክር የሚያደርስ፣ ከተናገረው ቃል አንዳች የማይወድቅ የእግዚአብሔር ሰው ነበር። በዚህም ከዳን እስከ ቤርሳቤህ ያለው ሕዝቡ ሁሉ ይህን የእግዚአብሔር ሰው ያውቅ ነበር።

> ከምዕራፍ 1 ጀምሮ እስከ ምዕ:3 ከ25 ጊዜ በላይ የተጠራውን እንዲህ ያለውን ሰው፣ በሚያስገርም ሁኔታ ቀጥለው ባሉት ሶስት ተከታታይ ምዕራፎች(4፣ 5፣ 6) ውስጥ ሌላው ቀርቶ ስሙን እንኳ አንዴም አናገኘውም። እነዚህ ምዕራፎች ያያዙት ታሪክ የ20 ዓመታት እንደሆነ ምዕራፍ 7 ይናገራል። እናም ሳሙኤልን ዳግም የምናገኘው ከ20 ዓመታት በኋላ ነው።

" ታቦቱም በቂርያትይዓሪም ከተቀመጠበት ቀን ጀምሮ ወራቱ ረዘመ፥ ሀያ ዓመትም ሆነ"
(መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 7:2)

#ከዳር እስከ ዳር፣ መላ እስራኤል የእግዚአብሔር ቃል እንዳለበት የሚያውቁትን ሰው እንዴት ረሱት?

> ሰዎቹ ማን ጋር እውነተኛውን ቃል እንደሚያገኙ ያውቃሉ። ነገር ግን ልባቸው ልክ አልነበረም(7÷3)። ሳሙኤል ጋር ቢሄዱ መልሱን ያውቁታል። ታማኙ የእግዚአብሔር ሰው ቀጥታ ቅዱስ ቃሉን ስለሚነግራቸው እርሱን ማናገር አልቻሉም(7÷3-4)።

> ፈረንጆቹ "አንድ ዓይነት ላባዎች አብረው ይበራሉ" እንደሚሉት፣ ሕዝቡ አካሄዱን የማይወቅስበት፣ ሐይማኖተኝነቱ እንዳይቀርበት ደግሞ እግዚአብሔርን የሚጠራለት፣ እንደ አፍኒን እና ፊንሐስ ካሉት ጋር እንዳሻው መሆን ፈልጎ ነበር።

> ስለዚህ ሳሙኤል በዚህ ወቅት አይፈለግም። ምክር አይጠየቅም (5÷3-4)።

#የእግዚአብሔር ቃል እንደሚለው የሚናገር ታማኝ የእግዚአብሔር ነብይ፣ የፈለገውን ያህል ሕዝቡ ቢያከብሩት፣ ቃሉን ግን ለመስማት ፍላጎት ከሌላቸው መካከል ምን ያደርጋል?

#ቃሉ ዝም እንዲል በሚፈለግበት ቦታ የሳሙኤል አፍ ሊከፈት፣ እርሱም እዚያ ሊገኝ አይችልም(ምዕራፍ አራት ላይ ያን የሚያክል ትልቅ አገራዊ ክስተት ወቅት ሳሙኤል የለም)።

> ለእኛ ጥያቄው ይህ ነው፦ ውስጣችን እያወቀው፣ አካሄዳችንን ይወቅሱብናል በማለት ከእግዚአብሔር ሰዎች እንርቃለን? የማይረባውን እንደሚነግሩን የምናውቃቸው ሰዎች ጋር ጊዜ ከምናጠፋ እና ሳሙኤሎች ዝም ከሚሉን፣ የእግዚአብሔር ቃል የሚነግሩንን ሰምተን ምልልሳችንን ማስተካከሉ አያዋጣምን?
54 viewsJesus-my-Saviour, 08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 21:06:40 የዘጸአት ትርጓሜ ትረካ ምዕራፍ አራት ነው
63 viewskoreb, 18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 21:05:58 Sharing File...
62 viewskoreb, 18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 17:11:07 ይህ የዘጸአት ትረካ ምዕራፍ ሶስት ከማጀቢያ ጋር ነው።
83 viewskoreb, 14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 15:13:35
በውኃውና ደሙ  (ክፍል 2/2)
ድንቅ ስብከት
    “በውኃና በደም የመጣ ይህ ነው እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ፤ በውኃውና በደሙ እንጂ በውኃው ብቻ አይደለም።”
  — 1ኛ ዮሐንስ 5፥6
62 viewsD Tz, 12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ