Get Mystery Box with random crypto!

የጸጋ ወንጌል

የቴሌግራም ቻናል አርማ abutjesys — የጸጋ ወንጌል
የቴሌግራም ቻናል አርማ abutjesys — የጸጋ ወንጌል
የሰርጥ አድራሻ: @abutjesys
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 376

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-01-31 13:40:10 *መንፈስ ቅዱስ አብ ወልድ!*

የስላሴ አካላት

> ከዚህ በታች የተቀመጡት ጥቅሶች በቅደም ተከተል መንፈስ ቅዱስን፣ አብን እና ወልድን የሚያሳዩ ናቸው፡፡

1ኛ. እግዚአብሔር መባል

- ሶስቱም እግዚአብሔር ተብለው ተጠርተዋል (የሐዋ.5፡1-4፣ ሮሜ.1፡7 ዮሐ.1፡1)፡፡

2ኛ. ያህዌ (ጂኦቫ) መባል

–  ሶስቱም ያህዌ ተብለው ተጠርተዋል (1ሳሙ.23፡2-3፣ መዝ.2፡7፣ ኤር.23፡6)፡፡

3ኛ. መፍጠር

–  ሶስቱም ፈጣሪ ተብለዋል (ኢዮ.33፡4፣ 1ቆሮ.8፡6፣ ዮሐ.1፡3)፡፡

4ኛ. የሕይወት ምንጭ

–  ሶስቱም የሕይወት ምንጭ ሆነው ቀርበዋል (ሮሜ.8፡2፣ ዮሐ.5፡26፣ 11፡25)፡፡

5ኛ. በሁሉ ቦታ መገኘት

–  ሶስቱም በሁሉ ቦታ ይገኛሉ (መዝ.138/9፡7፣ ኤር.23፡24፣ ማቴ.18፡20)፡፡

6ኛ. ሁሉን ቻይነት

–  ሶስቱም ሁሉን ቻይ ናቸው (ሉቃ.1፡35፣ 1ቆሮ.8፡6፣ ማር.4፡39-41)፡፡

7ኛ. ሁሉን አዋቂነት

–  ሶስቱም ሁሉን አዋቂ ናቸው (1ቆሮ.2፡10፣ ዕብ.4፡13፣ ሉቃ.9፡46-47)፡፡

8ኛ. ኢየሱስን መላክ

–  ሶስቱም አሉበት (ኢሳ.48፡16፣ 40፡3-4)፡፡

9ኛ. ኢየሱስን ከሞት ማስነሳት

–  ከኢየሱስ ትንሳኤ ጋር ተያይዞ ሶስቱም ተጠቅሰዋል( 1ጴጥ.3፡18፣ 1ቆሮ.6፡14፣ ዮሐ.2፡19)፡፡

10ኛ. መንፈስ ቅዱስን መላክ

–  ሶስቱም አሉበት (ዮሐ.16፡6፣ 14፡26፣ 15፡26)፡፡

11ኛ. ማዳን

–  ሶስቱም የማዳንን ስራ ይሰራሉ (1ጴጥ.1፡1-2)፡፡

12ኛ. መቀደስ

–  ሶስቱም ይቀድሳሉ (ሮሜ.15፡16፣ ዮሐ.17፡17፣ ዕብ.2፡11)፡፡

13ኛ. ለአገልግሎት መሾም

–  ለአገልግሎት ሶስቱም ሲሾሙ እናያለን (የሐዋ.20፡28፣ ዮሐ.5፡12፣ 1ቆሮ.12፡6፣ 1ጢሞ.1፡12)፡፡

14ኛ. የወደፊት ትንሣኤ

–  ትንሣኤ ጋር ተያይዞ ሶስቱን ተጠቅሰዋል (ሮሜ.8፡11፣ ዮሐ.5፡12፣ 6፡39)፡፡

15ኛ. ጌትነት

–  ሶስቱም ጌታ ተብለዋል (ኢሳ.6፡8፣ ማር.12፡31፣ ሮሜ.10፡9)፡፡ ወዘተ
25 viewsJesus-my-Saviour, 10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-31 09:40:04 የአዳም ልጆች
ዘፍ11:1 ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች። 2 ፤ ከምሥራቅም ተነሥተው በሄዱ ጊዜ በሰናዖር ምድር አንድ ሜዳ አገኙ፤ በዚያም ተቀመጡ። 3 ፤ እርስ በርሳቸውም። ኑ፥ ጡብ እንሥራ፥ በእሳትም እንተኵሰው ተባባሉ። ጡቡም እንደ ድንጋይ ሆነላቸው፤ የምድርም ዝፋት እንደ ጭቃ ሆነችላቸው። 4 ፤ እንዲህም። ኑ ለእኛ ከተማና ራሱ ወደ ሰማይ የሚደርስ ግንብ እንሥራ፤ በምድር ላይ ሳንበተንም ስማችንን እናስጠራው አሉ።
5 ፤ እግዚአብሔርም የአዳም ልጆች የሠሩትን ከተማና ግንብ ለማየት ወረደ። 6 ፤ እግዚአብሔርም አለ። እነሆ፥ እነርሱ አንድ ወገን ናቸው፥ ለሁሉም አንድ ቋንቋ አላቸው፤ ይህንም ለማድረግ ጀመሩ፤ አሁንም ያሰቡትን ሁሉ ለመሥራት አይከለከሉም።
እዚህ ክፍል ውስጥ እናንተ ብዙ ለራሳቹ የሚሆን ትምህርት ታገኙበት ይሆናል። ግን እኔ ኣንድ ነገር ላጋራቹ ወደድኩ። እዚህ ክፍል ውስጥ የአዳም ልጆች የሚል እንመለከታለን። እግዚኣብሄር ለምን የኖህ ልጆች አላለም? ለምን የሴም የካም የያፌት ልጆች አላለም?
1ጢሞ2፥13 አዳም ቀድሞ ተፈጥሮአልና፥ በኋላም ሔዋን ተፈጠረች።
14 የተታለለም አዳም አይደለም፥ ሴቲቱ ግን ተታልላ በመተላለፍ ወደቀች፤
መጸሃፍት እንደሚያሳዩን አዳም ጋር መስማማት ነው እንጂ መታለል አይታይም። እዚህ ጋር እነዚህ ሰዎች ሲስማሙ ነው የምናገኛቸው ሲስማሙ ነው። ስምምነታቸው ልክ አንደ አዳም የራሳቸውን ጥቅምና ፍላጎትን የጠበቀ ነው እንጂ የእግዚኣብሄርን ፍላጎትም ሆነ መሻት የሌለበት መሆኑን እንመለከታለን። ስለዚህ ይህ አይደል ያባቱ ልጅ። የአባታቸው ልጆች ስለሆኑ ስለ ስማቸው እና ስለ ክብራቸው የሚያስቡ እንጂ ስለ እግዚኣብሄር የሚያስቡ አይመስሉም።
የሆነው ሆኖ እኛስ ምን ላይ ነን ? በምን አይነትስ ሃሳብና ስምምነት ውስጥ እንገኝ ይሆን? እግዚኣብሄር ሲጎበኘን ለፍርድ የሚጋብዝ ነው ወይስ ለበረከት በደስታ እጁን የሚዘረጋበት? ያለንበትን እኛው ስለምናውቅ ፍርዱን ለራሳችን ልተው። እራሳችንን አይተን ለመወሰን ግን ጊዜ አንፍጅ ምክንያቱም የጌታ አይኖች ሁሌም ወደኛ ናቸው። እራሳችንን አውቀን መበተን ሳይሆን ንስሃ ገብተብ እራሳችንን እናስተካክል። እና የሁለተናው አዳም ልጆች ነን።
ምዕራፍ 8፥1 እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም። 2 በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው የሕይወት መንፈስ ሕግ ከኃጢአትና ከሞት ሕግ አርነት አውጥቶኛልና። 3 - 4 ከሥጋ የተነሣ ስለ ደከመ ለሕግ ያልተቻለውን፥ እግዚአብሔር የገዛ ልጁን በኃጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ በኃጢአትም ምክንያት ልኮ አድርጎአልና፤ እንደ መንፈስ ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ፈቃድ በባንመላለስ በእኛ የሕግ ትእዛዝ ይፈጸም ዘንድ ኃጢአትን በሥጋ ኰነነ። 5 እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ። 6 ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው።
7 ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል ነውና፤ ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና፥ መገዛትም ተስኖታል፤ 8 በሥጋ ያሉትም እግዚአብሔርን ደስ ሊያሰኙት አይችሉም። 9 እናንተ ግን የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ በመንፈስ እንጂ በሥጋ አይደላችሁም። የክርስቶስ መንፈስ የሌለው ከሆነ ግን ይኸው የእርሱ ወገን አይደለም። 10 ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ ቢሆን ሰውነታችሁ በኃጢአት ምክንያት የሞተ ነው፥ መንፈሳችሁ ግን በጽድቅ ምክንያት ሕያው ነው።
11 ነገር ግን ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ ክርስቶስ ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው እርሱ በእናንተ በሚኖረው በመንፈሱ፥ ለሚሞተው ሰውነታችሁ ደግሞ ሕይወትን ይሰጠዋል።
ስለዚህ እኛ እንደዚህ ቃል ከሆነ ለሃጥያት ነገሮች የሞትን ነን ማለት ነው። በማወቅም ሆነ ባለማወክቅ ለእግዚኣብሄር በማይመች መንገድ ተስማምተን ከሆን አሁን ቆም ብለን የምናስብበት ጊዜ ላይ ነን። ጌታ ማስተዋሉን ይስጠን!
ዮሃ8፥31 ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ። እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ 32 እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው። 33 እነርሱም መልሰው። የአብርሃም ዘር ነን ለአንድም ስንኳ ከቶ ባሪያዎች አልሆንም፤ አንተ። አርነት ትወጣላችሁ እንዴት ትላለህ? አሉት። 34 ኢየሱስ መለሰ፥ እንዲህ ሲል። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ኃጢአት የሚያደርግ ሁሉ የኃጢአት ባርያ ነው። 35 ባርያም ለዘላለም በቤት አይኖርም፤ ልጁ ለዘላለም ይኖራል።
እና ወገኖች ባለንበት ቦታ በስራም ሆነ በትምህርት እንደ እግዚኣብሄር ቃል መመላለሳችንን እናስተውል!!!!


ጸጋና ሰላም ይብዛልን!!!!
40 viewsErmi, 06:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-30 17:01:57 Sharing File...
75 viewskoreb, 14:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-30 09:50:53
90 viewsD Tz, 06:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-29 20:34:37 Sharing File...
93 viewskoreb, 17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-29 12:33:04 Sharing File...
98 viewskoreb, 09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 16:05:15 Sharing File...
106 viewskoreb, 13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 15:29:12 #ራሱንም_ለሁሉ ቤዛ ሰጠ!

(ዮሐ 19 )
------------
17 ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ።
18 በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ።

##።።

(1 ጢሞ 2 )
------------
5 አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤
6 ራሱንም ለሁሉ ቤዛ ሰጠ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ፤

☞ ሰው ሁሉ ኃጠአት በተፈጥሮው ያለበትና ኃጢአት የሚያደርግ በመሆኑ #የሞት(የዘላለም) ፍርድ ይገቧል — የእግዚአብሔር የጽድቁ ባህርይ ይህንን ይጠይቃል! ከሰው መካከል የሰው የኃጢአት ዕዳ መክፈል የሚችል የኃጢአት ባለዕዳ ያለሆነ ሰው የለም! መላእክትም መናፍስት ሰለሆኑ ለሰው #ቤዛ ለሆኑ አይችሉም።

☞ ሰው የሆነው #ክርስቶስ_ኢየሱስ የአምላክነቱ ክብር ሳይገድበው ራሱን በማዋረድ የኃጢአተኞች ስፍራ ያዘ ፣ የኃጢአትን ደመወዝ የሆነውን ሞት በመስቀል በመሞት #ራሱን #ለሁሉ_ቤዛ ሰጠ አዎ እርሱ ኃጢአትን የማያውቅ ፣ኃጢአት የሌለበት ፣ ኃጢአት ያላደረገ ፍጹም ቅዱስ በመሆኑ የሰው ሁሉ ኃጢአት ተሸከመ! ሰለ ሁሉ ሞተ! ሞትንም ድል በመንሳት በሥስተኛ ቀን ተነሣ ፣ በሰማያትም በግርማው ቀኝ ተቀመጠ።

(1 ጴጥ 2 )
------------
22 እርሱም ኃጢአት አላደረገም፥ ተንኰልም በአፉ አልተገኘበትም፤
23 ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም መከራንም ሲቀበል አልዛተም፥ ነገር ግን በጽድቅ ለሚፈርደው ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤
24 ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።

☞ ለሰው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ በተደረገው የቤዛነት ሥራ አምኖ ከመዳን በቀር ሌላ የቀረለት የመዳን መንገድ የለም ሊኖርም አይችለም! ይህ በኃጢአቱ ጕስቋላ ለሆነው ለሰው ልጅ እንደምን ያለ መልካም የምሥራች ነው!

(ሮሜ 3 )
------------
21 አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥
22 እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤
23 ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤
24 በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ።

☞ ኃጢአታችሁ የከበዳችሁ ወገኖች ኃጢአታችሁ ለዘላለም በመስቀል በደሙ ወደ አስወገደላችሁ ወደ ኢየሱስ ትመጡ ዘንድ እርሱ ሊቀበላችሁ ሊመጣ ካለው የቁጣ ፍርድ ለዘላለም ሊያድናችሁም የታመነ ነው።
109 viewsYemane H/mariam, 12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 19:43:59 Sharing File...
114 viewskoreb, 16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 21:08:44 የዘፀአት ትርጓሜ ምዕራፍ ሁለት ክፍል 5 ነው
131 viewskoreb, 18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ