Get Mystery Box with random crypto!

Zehabesha

የቴሌግራም ቻናል አርማ zehabeshanews — Zehabesha Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zehabeshanews — Zehabesha
የሰርጥ አድራሻ: @zehabeshanews
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 58.97K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopian News

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2024-06-12 21:54:06 የመንግስት መስሪያ ቤቶች፤ የብሔር ብሔረሰቦች “ብዙሃነት እና አካታችነትን” ያገናዘበ ስርዓት ተግባራዊ እንዲያደርጉ የሚደነግገው የፌደራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ ማሻሻያ፤ “ለአግላይነት ክፍት ነው” የሚል ትችት ቀረበበት። በፌደራል ደረጃ “አንድም ሰራተኛ የሌላቸው 17 ብሔር ብሔረሰቦች” እንዳሉ የገለጸው የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን፤ የወደፊት ቅጥሮች “ይህን ታሳቢ ማድረግ አለባቸው” ብሏል።
በፌደራል መንግስት ሰራተኞች የአዋጅ ረቂቅ ላይ የቀረቡ ትችት እና ጥያቄዎች የተስተናገዱት፤ በተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በጠራው የህዝብ ይፋ ውይይት ላይ ነው። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን (ኢሰመኮ) በመወከል በውይይቱ የተሳተፉት ሰዊት ዘውዱ፤ በረቂቅ አዋጁ ላይ “ኢትዮጵያን የሚመስል ተቋም” መገንባትን በተመለከተ ስለተቀመጠው ድንጋጌ ጥያቄ አቅርበዋል።
“የብሔር ስብጥርን ማካተት ከዚህ ውስጥ አንዱ የተነሳው ነው። ይህ ለአግላይነት ክፍት የሚሆንበት እድል ሰፊ ስለሆነ፤ አዋጁ ምን አይነት የቁጥጥር ስርዓት አበጅቷል?” ሲሉ በኢሰመኮ የህግ ባለሙያ የሆኑት ሰዊት ጠይቀዋል። እርሳቸው የጠቀሱት የአዋጁ ድንጋጌ “በማንኛውም የመንግስት መስሪያ ቤት ኢትዮጵያን የሚመስል የመንግስት ሰራተኞች ስብጥር መኖሩን በማረጋገጥ፤ የብሔር ብሔረሰቦችን፣ የአካል ጉዳተኞች፣ የጾታ ተዋጽኦ የመሳሰሉትን ብዙሀነት እና አካታችነትን ያገናዘበ የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ስርዓት ተግባራዊ መደረግ አለበት” ይላል። (Source: Ethiopia Insider)
9.1K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-12 21:15:59 በባህርዳር ዛሬ ከ4 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት የተፈጠረው ምንድን ነው? የኤርትራው አምባሳደርስ የዘረገፉት መረጃ ምን ይመስላል? የፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላና የባለሃብቶች ዝግ ስብሰባ ውጤትስ?፡በዕለቱ ዜና ላይ ይመልከቱ።
9.2K views18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-12 21:02:47

9.2K views18:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-12 20:50:26
ቀብር

በቀድሞ ባለቤቷ በአሜሪካ ጆርጂያ ግዛት የተገደለችው የወ/ሮ ባንቻምላክ አቡሃይ ቦጋለ ሥርአተ ቀብር የፊታችን አርብ በዚያው በጆርጂያ አርብ 6/14/2024 በደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስልያን ይከናወናል።
የሥርዓተ ቀብሩ መርሐግብር (program):
ጥዋት በ10፡00 am ሥርአተ ጸሎቱና ስንብቱ ይጀምራል።
ከቀኑ 12:30pm ሜልውድ መቃብር (melwood cemetery) ይደርሳል።

ቤተክርስቲያን መምጣት የማትችሉ ደግሞ በተጠቀሰው ሰዓት ከመቃብር ሥፍራው እንድትገኙ ቤተሰብ ጥሪ አቅርቧል።

የመቃብሩ አድራሻ፡
5170 E Ponce De leon ave
Stone Mountain 30083
9.5K views17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-12 17:17:51

9.1K views14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-12 17:07:11
9.1K views14:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-12 17:06:37 በመጨረሻም ጊዜው የሥራም፣የትግልም መሆኑንላስታውሳችሁ እወዳለሁ፡፡ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ትግል ላይነው፡፡ ትግሉ ደግሞ ራስን የመሆን ክቡር የጎንደር-አማራማንነቱን የማጽናት ትግል ነው፡- የራስን ዕድል በራስ የመወሰንትግል፡፡ ወልቃይት ጠገዴ ጎንደር-አማራ ነው! የትግሉ ዓላማ ግንከዚህም ከፍ ያለ ነው፡፡ ትግሉ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራንኮሪደር አስከብሮ የኢትዮጵያን ህልውና የመጠበቅ ሀገራዊትግልም ነው፡፡ ወልቃይት ጠገዴ ለእኛ መሬት ብቻ ሳይሆንማንነታችንም ነው፡፡ ቀየው፣ ወንዙ-ሸንተረሩ፣ ጋራው፣ ዛፉ፣ የእምነት ቦታው፣ መንደሩ፣ ገበያው ወዘተ…ሁሉ ለእኛ ልዩትርጉም አለው፡፡ ልዩ ስሜት ይፈጥርብናል፡፡ ብዙ የትውልዶችትዝታ፣ወግ፣ትውፊትና ልማድ ያቀፈ ባድማችን ነውና በምንምአይለወጥም! የተከዜ አዳኝ ትውልድ ተቀዳሚ ተልዕኮ ይህንንበምንም የማይለወጥ ክቡር የወልቃይት ጠገዴ አማራዊ ማንነትለማስከበር በነጋ-በጠባ በወያኔ ፕሪፖጋንዳ ሳንደናገርና ሳንዘናጋ፣ዛሬ የማይመች ቢሆን ነገ የተመቸ እንዲሆን በጽናትና በትጋትመሥራት፤መታገልና ወደፊት መግፋት እንጂ መሸነፍ፣ተስፋመቁረጥና ደክሞ መቆም አይገባም፣አያስፈልግም፡፡ ከባሕሩ ማዶያለውን ብርቱኳን የምንፈልገው ከሆነ ባሕሩን ዋኝቶ መሻገርያስፈልጋል እንጂ ሌላ ሰው ዋኝቶ እንዲሰጠን ከጠበቅን ከእሱየተረፈውን እና የማይፈልገውን እንደሚወረውርልን ማወቅይገባል፡፡ የምንፈልገው ጉዳይ በራሳችን ዐቅም ለማሳካትእየተጋን የጎደለብንን እየሞላን፣የጎበጠውን እያቃናን መጓዝበእጅጉ ያስፈልጋል፡፡ ስለሆነም ለጥንካሬ የሚበጁ ሁሉንምነገሮች እንደ ስፖንጅ በመምጠጥ ዐቅም አድርጎ በመጠቀም እናአንድነትን ከሚያላሉ ፣ ጽናትን ከሚያዳክሙ ነገሮች በመራቅሕልማችን እውን በማድረግ ባለታሪክ ለመሆን መረባረብያስፈልጋል፡፡ ትግሉ በውስን ጀግኖች ትግልና መስዋዕትነት ብዙርቀት የመጣ ቢሆንም፤ ገና በጣም ብዙ እንደሚቀረው ተገንዝቦበፅናት መታገልና መቆም ይገባል፡፡ ሁሌም ዝግጁ እንሁን!!ለነፃነት የተከፈለውን መስዋዕትነት በላይ የተገኘውን ነፃነትበዘላቂነትና በአስተማማኝ ማጽናት ያክል ከባድ የለምና እንትጋ!እንበርታ! በወጀብና በንፋስ አንወሰድ!ችግሮችን በምክክርእንፍታ!!
አመሰግናለሁ
ማይካድራ ከተማ
ሰኔ 5/2016ዓ.ም
አሸተ ደምለው ተድላ
የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ
8.6K views14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-12 17:06:37 የማይካድራ ሰማዕታት መቼውንምአንረሳቸውም!
ጊዜው የሥራም፣የትግልም ነው!!
ሀገራችን ኢትዮጵያ በየጊዜው የገጠሟትን ብሔራዊ ፈተናዎችበቀደሙት አርበኞች የከበረ መስዋዕትነት በድልተሻግራቸዋለች፡፡ በረዥሙ የነፃነት ታሪኳ የተለያዩ ወራሪዎችፈትነዋታል እንጂ አላንበረከኳትም፡፡ በብርቱ መስዋዕትነትሀገራዊ ህልውናዋን ማስቀጠል ችላለች፡፡ በየዘመናቱ የታሪክመታጠፊያ የሆኑ ክስተቶች አጋጥመዋታል፡፡ ለታሪካዊ ጠላቶቿተንበርክካ የማታውቀው ኢትዮጵያ፣ በዘመናት መካከልየሚያጋጥሟትን የታሪክ መታጠፊያዎች፣ ራሷን እንደንሥርአድሳ፤ ትንሳዔዋን አብስራ አልፋቸዋለች፡፡  ጥቅምት 24ለኢትዮጵያ የታሪክ መታጠፊያ ማዕዘን ነው የምንልበት ዋነኛምክንያት በአንድ በኩል ጠላት ኢትዮጵያን ወደ ድንጋይ ዘመንለመቀየር ወጥኖት የነበረውን እኩይ ዓላማ ከሽፎሊያስተባብለው የማይቻለው የማይካድራ ጥቅምት 30/2013ሰይጣናዊ ማንነቱ ለዓለም የተገለጠበት  ሲሆን በሌላ በኩልደግሞ የሀገረ-መንግሥቱ የመጨረሻ ምሽግ የሆነውመከላከያ ሠራዊታችን በእናት ጡት ነካሽ ባንዳዎችከጀርባው ተወግቶ፣ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት አደጋ ላይበወደቀበት ሁኔታ የሰራዊቱ አባላት በመስዋዕትነታቸው ታሪክየማይሽረው አዲስ የድል ምዕራፍ የከፈቱልን፤ በህልፈታቸውየኢትዮጵያን ህልውና ያፀኑልን በመሆኑ  ጥቅምት 30የማይካድራ ሰማዕታት፣ በጥንተ-ጠላት ሕወሓትየተፈፀመው የሀገር ክህደት፣የክፋቱ ጥግ ማሳያ ናት፡፡ ይሁንእንጂ የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጭ ግንባር/ትህነግ-ወያኔ/ ከፍጥረቱ ጀምሮ  ፀረ-አማራ እና ፀረ-ኢትዮጵያ  ሆኖ የተነሳአረመኔ ድርጅት ነው፡፡
ወያኔ፣ በአማራ ደምና ሀብት ‹ታላቋ ትግራይ›ን የመመሥረትዕቅዱን ለማሳካት ሲል፤ አማራን ገድሏል፤ አኮላሽቷል፤ ሀብቱንዘርፏል፤ መሬቱንም ወርሯል፡፡ ለዚህ ምስክር የወልቃይት-ጠገዴየሦስት ዐሥርት ዓመታት መዋቅራዊ ግፍና መከራ ቀዳሚተጠቃሽ  ነው፡፡
ባለፉት ሠላሳ ዓመታት ዓለም ጆሮ የነፈገው  የዘር ማጥፋትወንጀል በወልቃይት ጠገዴ የአማራ ሕዝብ ላይ ተፈጽሟል፡፡ ምናልባትም በብዙሃኑ ኢትዮጵያውያንና በተወሰኑ የዓለማቀፉማኅበረሰብ አባላት ዘንድ የተሰማው ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም የሕግ ማስከበር ዘመቻው ከተጀመረ በኋላ ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም በማይካድራ የተፈፀመውን የዘር ማጥፋትወንጀል ብቻ ነው፡፡ የወልቃይት ጠገዴ አማራ ግን ባለፉት ሦስትዐሥርት ዓመታት በርካታ ማይካድራዎችን አይቷል፡፡ በየትኛውምየዓለም ክፍል የተፈጸሙ የዘር ማጥፋት ወንጀሎች አንዴተጀምረው በተወሰነ የጊዜ ገደብ የተጠናቀቁ ቢሆንም፣ ወልቃይት ጠገዴ ላይ የተፈፀመው የዘር ማጥፋት ወንጀል ግንበዓይነትም ሆነ በድርጊት የተለየ ነው፡፡
የማይካድራን ጭፍጨፋ ስናስብ ጭፍጨፋው የፀረ-አማራትርክት ውጤት ስለመሆኑ ልብ ልንለው ይገባል፡፡ ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም በማይካድራ ከተማ የተፈፀመው የጅምላጭፍጨፋ በ1968 ዓ.ም ወያኔ ያዘጋጀው አማራን የማጥፋትፍኖተ መርሁ አካል ነው። 
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ የጥናት ባለሙያዎች ለወራትባደረጉት ጥናት መሠረት በዚህ የጅምላ ጭፍጨፋ 1,644 አማራዎች የጉዳት ሰለባ ሆነዋል።  የተገደሉ1,563 ሲሆኑ፤ የአካልጉዳት የደረሰባቸው ደግሞ 81 ናቸው፡፡ በዚህ ጭፍጨፋ የተነሳበርካታ ሕፃናት ያለ ወላጅ ቀርተዋል። የደረሰውን ግፍለማስረዳት ገና ብዙ መጻሕፍት፣ ፊልሞች፣ ዘገባዎችናዶክመንተሪዎች እንደሚያስፈልጉ አያከራክርም፡፡ በዚህ በኩልከፍትሕ ወዳድ ኢትዮጵያዊያንና ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ብዙእንጠብቃለን፡፡ እኛም ለመተባበር ሁልጊዜም በራችን ክፍትነው፡፡
የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ የማንነት እና ወሰን ጥያቄ ቀንጠብቆ፤ ሒሳብ ሰርቶ ብቅ ያደረገው የዘር ካርድ ሳይሆን በመራርየፈተና እና የመከራ ወቅት ሳይቀር እስከ ኢያሪኮ ጎልቶ የተሰማእውነተኛ የሕዝብ ድምጽ ነው፡፡ የወልቃይት ጠገዴ አማራሕዝብ ግፈኞች ቀን ሰጣቸው ብሎ ሳይፈራ፤ በጀምላ ተገደልኩብሎ ለነፍሱ እና ለቤተሰቡ ሳይራራ ከሦስት አስርት ዓመታትበላይ በጽናት እና በብርታት ፊት ለፊት እንደተጋፈጣቸው ታሪክህያው ምስክር ነው፡፡ የወልቃይት-ጠገዴ አማራ ሕዝብ ይህንሁሉ ግፍና መከራ ተቀብሎ በከበረ መሥዋዕትነቱ ዛሬ ነጻነቱንአስከብሮ ከአብራኩ በወጡ ልጆቹ እየተመራ ይገኛል፡፡
ስለሆነም ጊዜው የሥራም፤የትግልም በመሆኑ በዛሬው ዕለትሰኔ 5/2016ዓ.ም የማይካድራ ሰማዕታት መቼውንምአንረሳቸውም!! በሚል መሪ ሃሳብ የሰማዕታቱ ማስታወሻየሚሆን ሃወልት በማይካድራ ከተማ በ3136 ካ.ሜና በ30ሜ ከፍታ ላይ የሚያርፍ ሲሆን የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ሰውምጎንደሬ፤ መሬቱም የአማራ፣ ወሰኑም ተከዜ መሆኑን በታሪክም፣በጂኦግራፊም፣ በሥነ-ህንፃም፣ በወግ፣ በባህሉ፣ በሥነ-ልቦናየተሳሰረ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በግፈኛው ወያኔቡድን ሲደርስበት የነበረውን ግፍና በደል ከወንድም የአማራህዝብና ፍትህ ወዳድ ኢትዮጵያውያን ጋር በጽናትና በአይበገሬነትየታገለበትን እና የተጎናጸፈውን ነፃነት ትግል በዘላቂነትለትውልዱ ለማስተላለፍ ይረዳ ዘንድ ከታገለበት ዓላማ ጋርየተሳሰረ፣የተሰናሰለና ዘመኑን የዋጀ የአርቴክት ሙያ ተላብሶእንሆ በዛረው ዕለት በይፋ የሰማዕታት የትግል አደራ ሃወልትለማቆም የሚሰራበትን ቦታ ለይተን አስቀምጠናል፡፡
ስለሆነም የማይካድራ ሰማዕታት መታሰቢያ ሃውልት ሰሪዎችእኛው፣መሀንዲሶቹ ከአብራኩ የወጡ ልጆቹ ፣የፋይናንስ ምንጩእኛውና ፍትህ ወዳድ ኢትዮጵያውያን ነን፡፡ ይህ ሃወልት ሲያልቅየወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ትግል አማራ ነን እንጂ አማራ እንሁንአላልንም የሚለውን ጉልህ ምልክት ሁኖ እንደማሳያየሚያገለግል፣የማይካድራ ሰማዕታት በሰው ልጅ አእምሮና ልብማህተም ሁኖ እንዲኖር ከታገለበት ዓላማ ጋር ተሰናስሎ ከዘመኑየዋጀ የኪነ-ህንፃ ሙያ ተገናዝቦ አምሳል የሆነውን የዳግማዊአያናዝጊ ቤት-ሞሎ ከተማ የሚገኘውን ከታሪካዊ የጎንደር-የፋሲል አብያተ መንግስታት ጋር በታሪክ ተጣጥሞ የሚሰራሃወልት መሆኑን ትልቅ የትግሉ ድልና ስኬት ነው፡፡ ስለሆነም ይህሃወልት ተሰርቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ አስተባባሪዎቹ የወልቃይትጠገዴ አማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽና አስጨራሽ ኮሚቴዎችይሆናሉ፡፡
8.5K views14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-12 04:03:23

10.1K views01:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-06-11 21:09:57

10.5K views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ