2023-01-22 22:09:54
እነ አመድ "ሀገር የማዋለዱን" ጉዳይ ተያይዘውታል:: በሙስሊም ውስጥ ገብተው ባለፈው ያደረጉትን ነገር ታውቃላችሁ:: በኦርቶዶክስ ውስጥ ዘረኞች አስቀድመው ተሰግስገው ስራቸውን ይሰሩ እንደነበርም ታውቃላችሁ::
ዘረኛው ሳዊሮስ (አሁን መአት ጳጳሳትን የሾሙት ሰውዬ ራሳቸውን እንደፓትረያርክ ያዩት ሰውዬ) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ሆነው ነበር:: በዛ ወቅት አንድ ቃለመጠይቃቸውን ሰምቼ ነበር:: በ2009 ዓ.ም ነው:: ቃለ መጠይቅ ሲያደርጉ እንዲህ የሚል ቃል ወጥቶአቸዋል:: "ቅዱስ ሲኖዶስን የሚመራውና ሥራውን የሚሠራው መንፈስ ቅዱስ ነው:: ሰው ምክንያት ነው" ብለው ነበር:: ይህን የመንፈስቅዱስን ሀሳብ ዋጡትና ከሰው በታች ወርደው ዘረኛ ባለጊዜ ሆኑ:: ያኔ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ በነበሩበት ወቅት የሰጡትን መንፈስ ቅዱስ ረስተው አሁን ባለዘር ሆኑ:: ባለዛር አላልኩም:: ቅዱስ ሲኖዶሱ ቆባቸውን ከገፈፈው ባለዛር ወይም ቃልቻ ሊሆኑ ይችላሉ:: "ሥራ ያጣ መነኩሴ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል" የሚባለው አባባል ጥሩ ነው:: "ሰው ከማማ" ብሎ ቆቡን ቀዶ ቢሰፋ ከመንፈስ ቅዱስ አይርቅም::
"...ቀለህም ተገኘህ" የምትል ጥቅስ አለች:: "አንተ" እያልኩ ላቀለዎት ነበር:: በሥራዎ አንቱ የሚያስብል ሥራ ስላልሰሩ ህዝቡ እርስዎን አንቱ በማለቴ ሳይናደድብኝ አይቀርም:: ሥራዎ ዝቅ ያደርገዎታል:: በሰማይም በምድርም ዝቅ ያለ የሥጋ ሥራ እንደሰሩ የኢትዮጵያ ህዝብ ይገባዋል:: ህዝብ ደግሞ ካዋረደ አዋረደ ነው አበቃ::
ሳዊሮስ ራሳቸውን እንደ ፓትርያርክ ቆጥረው÷ ለራሳቸው ሹመት ሰጥተው መንጋ ጳጳስ ሾመውብናል:: ቆብ ማምረቻ ካለዎት ሥንት ሥራአጥ አለ:: እባክዎ ፒኤልሲ ከፍተው ሥራ አጡን ያስገቡልን::
በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶሱ ቆበዎትን ገፎ የበግ ሳይሆን የአህያ እረኛ በቅርቡ እንደሚያደርገዎት ጥርጥር የለኝም:: የእናንተ ኃጢአት አይቶ ነው የኢትዮጵያ ህዝብ "ዝናብ" ሳይሆን "ሚስማር" የሚዘንብበት::
በዛሬው ዕለት በእርስዎ እጅ የተሾሙትም ጳጳሳት ተብየዎች ከብልግና ካድሬ በታች ናቸው:: መስቀላቸውም መስቀል ስላልሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ አይሳለምም:: አንዳንዴ እንደ ሥጋ ሳስብ (ስናደድ) የኢትዮጵያ ህዝብ በሳዊሮስ የተሾሙትን ካድሬዎች ቆባቸውን ገፎ የመነኩሴ ልብሳቸውን አውልቆ ቂጣቸውን ገርፎ ቢያባርርልኝ ስል እመኛለሁ:: የሳዊሮስ ካድሬዎች ሆይ ያደረጋችሁት ቆብ እሳት ሆኖ ይፍጃችሁ!
ዘረኞች ምቀኞች ባለጊዜዎች እናንተ በሰማይም በምድርም አሰቃቂ ህይዎት ይኑራችሁ:: ጊዜ የፈጣሪ ነበር:: እናንተ በዘር ተካችሁት:: ነፍስ ብሔር የለውም:: አማራ ስለሆንኩ አልፀድቅም:: ትግራይ ስለሆንኩ አልፀድቅም:: ኦሮሞ ስለሆንኩ አልፀድቅም:: ቢያንስ ስጋችንን ከፋፍላችሁታል:: ነፍሳችንን አትከፋፍሏት:: ነፍሳችን እንደከፋፈላችሁዋት ሥጋችሁን ይከፋፍለው:: የኢትዮጵያዊው አቡነ ጴጥሮስ እርግማን ይድረስባችሁ!
13.0K views19:09