Get Mystery Box with random crypto!

Yalelet Wondye

የቴሌግራም ቻናል አርማ yaleletwondy — Yalelet Wondye Y
የቴሌግራም ቻናል አርማ yaleletwondy — Yalelet Wondye
የሰርጥ አድራሻ: @yaleletwondy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.44K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-04-08 14:04:07 ለጀኔራሉ ይህን መልዕክት አድርሱልኝ!
የርስዎ ጎልያድነት ዛሬ ከናቁት እና ከደነፉበት ህዝብ በታች ነው
******
ትላንት ምሽት በብሄራዊ ጣቢያዎች ላይ የተላለፈው የጀኔራል አበባው ሃይል የተቀላቀለበትን ቃለ መጠይቅ አይቼ እጅግ አዘንኩ፤ አፈርኩም። ከብዙ ጥያቄና መልስ በኋላ የቃለመጠይቁን መዝጊያ "እኔ ሰው ነኝ ፤ ሲቀጥል የኢትዮጵያ ጀኔራል ነኝ ። እኔ የአንድ ብሄር አገልጋይ ልሆን አልችልም" እኔ የህዝብ ልጅ ነኝ ሲሉ ቃለመጠይቃቸውን ደምድመዋል።

መደምደሚያቸውን ተቀብለን እንደ ሰውም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ጀኔራል ሰውኛ የሆኑ የሞራል ጥያቄዎችን ልናነሳላቸው ተገደናል።

እንዴው ለመሆኑ እርስዎ ከተሾሙበት ጊዜ ጀምሮ ዘብ የቆሙለት ውሽልሽሉ መንግስት ጥገናዊ ለውጥ አደረኩ ባለበት ማግስት በቤኒሻንጉል እና በወለጋ ለተከታታይ 5 አመታት የአማራ ህዝብ ታርዶ በጅምላ ሲቀበርና ሲፈናቀል እርስዎ የሚመሩት ተቋም ምን እየሰራ ነበር?

በኦሮሚያ ክልል እና በአዲስ አበባ የሚኖረው የአማራ ህዝብ በብሄሩ ተለይቶ ለዘመናት ያካበተው ሃብት በአንድ ጀንበር ሲወድምበትና ሲፈናቀል በርስዎ የሚመራው የማህበራዊ ፍትህ አስጠባቂ የበላይ ተቋም ምን ሰራ?

እርስዎስ ቢሆኑ እንደ አንድ ትልቅ ተቋም መሪ እንዲሁም ኢትዮጵያዊ ዜጋ የህዝብ ልጅ በሚዲያ ወጥተው ስለምን ድርጊቱን አላወገዙም? ነው ወይስ በርስዎ ስሌት የአማራ ህዝብ ኢትዮጵያዊ ዜጋ አይደለም ማለት ነው?

ሌላው ይቅር ለሃገርና ለህዝብ ደህንነት ስጋት የሆነው የኦሮሚያ ክልል መንግስት ሃይሎች ከመከላከያ ሰራዊቱ በላይ ዘመናዊ መሳሪያዎችንና ወታደራዊ ኮንቮዮችን ታጥቆ ሳለ እርሶም ሆኑ ተቋምዎ አንድም ቀን ጉዳዩን ሊያስተባብል አልቻል። ለምን?

ዛሬ የአገር ህልውና አስጠባቂው፣ የመከላከያ ሰራዊቱ መከታና ደጀን የሆነው የአማራ ልዩ ሃይል እና ፋኖ በታጠቀው ክላሽ ስለምን አይንዎ ቀላ? ለምንስ በዚህ ልክ ሚዲያ ላይ ወጥተው በዕብሪት ሊደነፉ ቻሉ? ከህወሃት ጋር በነበረው ጦርነት እንኳ ይሄን ያህል አልደነፉም ነበር እኮ ክቡር ጄኔራል? ለማንኛውም ሃይል በተሞላበት ቃለ መጠይቅዎ ውስጥ አድር ባይነትዎ ጎልቶ ታይቷል።

እንደው ለመሆኑ ኢትዮጵያዊ ጀኔራልነትዎ እርስዎ የወጡበትን ህዝብ እንዲጠየፉ ያደረገዎት መንፈስ ምን ይሆን?

በአንድ ወቅት የእርስዎ አለቃ ጀኔራል ብርሃኑ ጁላ በስረአቱ ውስጥ ስለሚታየው የተረኝነት ድርጊት ተጠይቀው በድፍረትና በልበ ሙሉነት "አዎ ተራው የኛ ነው፤ ተረኞች ነን" ብለው እንደነበር ክቡር ጀኔራል አበባው ሊረሱት አይችሉም ብለን እናምናለን።

ሲጠቃለል:- ክቡር ጄኔራል ሆይ የሞራል ሚዛንዎን ስተዋል። ምናልባት የእርስዎን አላውቅም እንጂ በርስዎ የሚመራው ሰራዊት ከህዝብ ነው የወጣው። ዛሬ እርስዎ የተማመኑበት ሃይል ሁሉ ከህዝብ በታች ነው።

አዎ የርስዎ ጎልያድነትም ዛሬ ከናቁት እና ከደነፉበት ህዝብ በታች ነው
10.2K views11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 14:38:36
እውነታው ይሄ ነው!
***************
የሌሎች ክልሎች ልዩ ኃይሎች ትጥቅ ይፈታሉ፤ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ግን ትጥቅ አይፈታም ተብሏል።

ትናንት በተደረገው ስብሰባ የተሃድሶ ኮምሽኑ ኃላፊ ተሾመ ቶጋ በሰጠው መግለጫ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ትጥቅ እንደማይፈታ ገልፆአል። በዋነኛነት ትኩረት የተደረገው ሌሎቹ ላይ ሲሆን የኦሮሚያ "ሁኔታዎች ሲመቻቹ" ነው የተባለው። "ሁኔታዎች አልተመቻቹም" እያለ ይቀጥላል። በአጭሩ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ትጥቅ አይፈታም። ትጥቅ እንዲፈቱ የተፈለጉት ሌሎች ናቸው። በዋነኛነት የአማራ ልዩ ኃይል።
2.8K views11:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 14:57:00 ክልል = 6,000,000 (ስድስት ሚሊዮን) ህዝብ

ባልተጻፈ ህግ ሀገር የሚመራው 'the narcissistic' አብይ አህመድ በዛሬ የፖርላማ ውሎው "ከስድስት ሚሊዮን ህዝብ በታች ሆኖ ክልል መጠየቅ አይቻልም" ብሏል:: ይህ በየትኛውም የሀገሪቱ ህግ ያልተጠቀሰ ነው:: በዚህ መሰረት በአሁኑ ሰዓት 'ሀረሬ፣ ጋምቤላ፣ ቤንሻንጉል ጉምዝ፣ ሲዳማ፣ አፋር እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ' በአብይ አህመድ አነጋገር ክልል መሆን የለባቸውም ማለት ነው::
2.4K views11:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 12:38:22
አብይ አህመድ ዛሬ ቁርጡን (እውነቱን) ተናግሯል::

"በዚህ ዘረኛ እና አፖርታይድ ስርዓት (በእሱ አነጋገር 'ዴሞክራሲያዊ' ብሎታል) ሰጥ ለጥ ብላችሁ ካልተገዛችሁ ቀጥሎ ከዚህ የባሰ አምባገነን እንሆናለን:: ከዚያ ቀጥሎ ያው ኢትዮጵያ ትበታተናለች" ብሏል:: ከዚህ በተጨማሪም "ኢትዮጵያን ለማፍረስ ማንም አይከለክለንም" ብሏል::

አብይ አህመድ ጭምብሉን ገልጧል::
2.7K views09:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 22:09:40 በመሃይም ደንቆሮ ጠሚና ጀኔራል የምትመራ ብቸኛዋ የአለማችን ሃገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት።

https://vm.tiktok.com/ZMYCckRDc/
3.3K views19:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 17:04:28
ለወገን የድጋፍ ጥሪ !!!

በጎጃም የሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖችን እናግዝ!

በአሁነ ጊዜ ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች በተለይ ደግሞ ከኦሮሚያ ወለጋ ዞኖች፣ ከመተከል እና ሌሎችም አካባቢዎች በርካታ ወገኖቻቸውን ተነጥቀውና ቤት ንብረታቸውን አጥተው ተፈናቅለው በጎጃም በተለያዩ አካባቢዎች ተጠግተው የሚገኙ ወደ 300,000 የሚጠጉ ተፈናቃዮች ይገኛሉ፡፡

እነዚህ ወገኖች የዕለት ምግብ እና መጠለያ አጥተው በችግር ላይ ይገኛሉ፡፡
በመሆኑም ወገኖቻችንን ለማገዝ የአይነት እና የገንዝብ ድጋፍ በማሰባሰብ ድጋፍ እንዲደረግ የልማት ማኅበሩ የሥራ አመራር ቦርድ ወስኗል።

ስለሆነም፤

ሀ) የአይነት ድጋፎች፡-

ለዕለት ደራሽ ምግብ፦ ፓስታ፤ማኮረኒ፣ ሩዝ፣ ምሥር፣ ቅንጪ፣ ፊኖ ዱቄት፣ ዘይት፣ … ወዘተ

የመመገቢያና ማብሰያ ቁሳቁስ፡- ብረት ድስት፣ ሳህን፣ ኩባያ፣ማንቆርቆሪያ፣ ጀሪካን – ወዘተ

ሳፋ፣ጆክ፣ ማስታጠቢያ፣ ሳሙና፣ ኦሞ፣ ስፖንጅ --- ወዘተ

የማስረከቢያ ቦታ፡-
አዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለከተማ፣ ወረዳ 4 የድሮው ቡልጋሪያ ኤምባሲ አጠገብ በሚገኘው የጎልማ ዋና መስሪያ ቤት፤
ስልክ (+251) 90 499 1984
(+251) 11 470 1327)

ለ) በገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ፦

በጎጃም ልማት ማኅበር ስም የተከፈቱ ሶስት አካውንቶችን ለዚህ ጉዳይ እንዲውሉ ተደርጓል፡፡

እነዚህም ፤

1- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000114348302

2- አቢሲኒያ ባንክ አካውንት ቁጥር 6212972

3- ዳሽን ባንክ፡- አካውንት ቁጥር 0002028935011

ሁሉም ለወገኑ የሚቆረቆር ሁሉ ድጋፍ እንዲያደርግ እየጠየቅን የማህበራችን አባላት እና ደጋፊዎች የላቀ ማስተባበር ሚና እንድትወጡ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

የጎጃም ልማት ማኅበር
4.5K views14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 14:19:51 ወንድሜም ዮሴፍ ይጥና የቀድሞ ዩቱዩብ አካውንቱ ተዘግቶበታል።
በአዲስ አካውንት መጥቷልና ተወዳጁት!
https://youtube.com/@jossytube-4550
1.8K viewsedited  11:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 23:01:35
ብርቱው ወንድሜ @Kumelachew Getahun Mengistie መልካም የስራ ዘመን ይሁንልህ!!!
በተለይ እኔ እና አንተ ከቤጉ እስከ አማራ ክልል የተሰደድንባቸው መንገዶች ያመሳስሉናልና በርታልኝ!
2.4K views20:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 15:18:46 ህዝብ ቋሚ ጥቅም ነው!
*******
በፖለቲካ መስመር እና አመለካከት መስማማትም ሆነ አለመስማማት ከህዝብ ህልውናና ጥቅም ጋር የሚያገናኘዉ አንዳችም ምክንያት የለውም። ህዝብ ሁሌም ቋሚ ጥቅም ነዉ።

ፖለቲከኞች በአመለካከትና በአሰላለፍ ልዩነት (የተለያዩ ፓርቲዎች ስር ሆኖ መታገል፣ ገለልተኛ መሆን ወዘተ) የህዝብን ጥቅም ማስከበር ከተሳናቸዉ፣ ቀድሞዉኑ የሥልጣን ጥም እንጂ ሕዝባዊ አላማ (የሕዝቡን ማህበረ–ፖለቲካዊ ጥቅም የማስከበር ዓላማ) አልነበራቸዉም ማለት ነዉ።

በተለያየ እሳቤ ውስጥ ያሉ፣ የፖለቲካ ሃይሎች በህዝብ ቋሚ ጥቅም ዙሪያ፣ ተመሳሳይ አቋም ከያዙ ግን የፖለቲካን ምንነት በዉል ተረድተዉታል ተብሎ ይወሰዳል። አንዳንድ ግዜ በፖለቲካ ሃይሎች መካከል አለመግባባት የሚፈጠረዉ፣ በህዝብ ጥቅም ዙሪያ የነጠረ አቋም ባለመያዛቸው ሳቢያ ነዉ።

በዚህ ግዜ መወነጃጀል፣ ሴራ መጎንጎን፣ አድርባይነት፣ ጥሎ ለማለፍ የሚደርግ ቡድንተኝነት የአመራሮቹ የዕለት ተዕለት ሥራ ይሆናል። ህዝብ ሙሉ በሙሉ ይረሳል። በሌሎች (በተደራጁ ሃይሎች) አጀንዳ የሚሳብ አመራር ይበረክታል። ህዝብ እንደ ህዝብ ተቅበዝባዥ፣ የተበታተነ እና በሞራል የተዳከመ ሆኖ፣ መፃኢው እድል በሌሎች ይሁንታ ላይ የተመሠረተ ይሆናል።

በዚህ ግዜ መፍትሔው፣ ውጫዊ ሳይሆን ውስጣዊ ይሆናል። በሕዝብ ጥቅም ዙሪያ ተፃራሪ አቋም ያላቸውን ሃይሎችን፣ በተደራጀ የህዝብ ግኑኝነት ሥራ (political indoctrination)፣ ከምልዐተ ሕዝቡ የመነጠል፣ ፖለቲካዊ ቅቡልነታቸዉን የማዳከም፣ ማህበራዊ ትስስራቸውን ማላላት ቀዳሚ ተግባር ይኾናል።
ይህንን ለማድረግ ደግሞ የበቃ ፖለቲካዊ ባሕሪ መላበሥ ያሻል።

Workayehu Chekole Desta
2.8K views12:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 15:47:55 #ፋሽዝም ነው ሲባል ፦

የኦሮሚያ ክልል ባለፉት 5 አመታት በሁሉም አቅጣጫ በጉልበት ተስፋፍቷል።

ይህ የመስፋፋት ፕሮጀክት ከመንግስት ለውጡ በፊት ሶማሌ ክልልን የጀመረ ሲሆን የአብይ አስተዳደር ስልጣን ከያዘ ወዲህ ግን በሁሉም አጎራባች ክልሎች ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ወረራ ፈጽሟል። በዚህም ከቀበሌ እስከ ዞን መዋቅር ደረጃ ያሉ የአጎራባች ክልል መሬቶችን በወረራ ይዟል።
ጋምቤላ ፣ ቤንሻንጉል እና አፋር በወረዳ ደረጃ ያሉ የክልል መዋቅሮችን የተነጠቁ ሲሆን ሌሎችም አጎራባች ክልሎች በተለያዬ መልኩ መዋቅር ነጠቃ እና መሬት ወረራዎች ተፈጽሞባቸዋል። የኦሮሚያው ኦሊጋርክ ከአማራ ክልል በስተቀር ከሁሉም አጎራባች ክልሎች የመሬት ይገባኛል አሉት። እነዚህ ይገባኛሎች የፖለቲካ አጀንዳ ይሁኑ እንጂ ጥያቄዎች አይደሉም። አጀንዳው በጥያቄ መልኩ ያልቀረበበት ሰበብም አሁን በስራ ላይ ካለው የህግ እና የፖለቲካ ማዕቀፍ ውጭ የሆኑ እና የግልጽ የግዛት ማስፋት ትልሞች በመሆናቸው ነው።

ይህ ሀይል ከሶማሌ ክልል ጋር በሚጋራው ድንበር ብቻ ከመቶ ኪሎ ሜትር የሚያልፍ የይገባኛል አጀንዳ ያለው ሲሆን ከመንግስት ለውጡ በኋላ ጉዳዩን በጉልበት ለማስፈጸም አልፎ አልፎ ከተፈጸሙ ሙከራዎች በስተቀር የወረራ ፕሮጀክቱ በይደር ተቀምጧል። የጉልበት አማራጩ በግልጽ ባይፈጸምም የመፈንቅለ መንግስት ሙከራዎችን ጨምሮ የክልሉ መንግስት በተለያዩ የሳቦታጅ ታክቲኮች ለማዳከም እና በህቡዕ የመዋቅር ነጠቃ ለመፈጸም በተደጋጋሚ ተሞክሯል። ሆኖም እነዚህ ሙከራዎች አንድም በመስተዳድሩ የፖለቲካ ካፒታል እና የአስተዳደር ብልሀት እንዲሁም በሌሎች አጋሮች ትብብር ሙከራዎቹ ከሽፈዋል።
ከአፋር በአዋሽ አርባ ያለውን አዋሳኝ ወረዳ እና ከቤንሻንጉል የማኦኮሞ ልዩ አስተዳደር ዞን እንዲሁም በካማሺ ዞን ያለውን የያሶ ወረዳ ሙሉ
በመሉ በወረራ ይዘዋል።

የራሱን ሀገር በጠላትነት የሚወር የሁላችን የብሄራዊ ደህንነት ስጋት የሆነ ፋሽስት ወራሪ ሀይል ታግሎ ማሸነፍ የግድ ይላል።

@Dawit Mehari
4.3K views12:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ