2022-12-30 20:58:02
ከአንድ አመት በፊት የተውኩትን ትግራይ ቴቭ እስኪ ልየው ብየ የ1ሰአት ዜናቸውን ሙሉውን ሠማሁት።
ከሰሯቸው 7ዜናዎች 6ቱ የአማራ ሃይሎች የሚለውን የሚመለከት ነው። ከዘለፋና ማስፈራራት በላይ ጸረ ሰላም የሚሉ ሃረጎችን ሲጠቀሙ አይቻለሁ።
ይህም በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት አደገኛ የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ማድረግ አይፈቀድም የሚለውን የሚጥስ ነው። መቼም ስምምነቱ except Amhara አይልም።
ፌደራል መንግስቱ ላይ የአማራ ህዝብ ተወካይ ካለ ይሄንን ሊያስቆም ይገባል። ሰላም ሲኮን ሁሉም ሰው ሰላም እንደሚገባው ሊታወቅ ይገባል።
አሁንም ድረስ በአማራ ክልል ዋግኽምራ ዞን ከአብርገሌ ወረዳ 40,000+ ከጻግብጂ ወረዳ 32,000+ ህዝብ ተፈናቅሎ ሰቆጣ ይገኛል፤ አከባቢውም በህወሀት ሃይሎች ስር ነው።
ስምምነቱ እነዚህንም ህዝቦች ሰላም የሚሰጥ መሆን አለበት።
@ wonde brehanu
2.5K viewsedited 17:58