2023-02-21 19:39:49
የሰሞኑ ሁኔታ አመላካች (case indicator)*መረጃዎች አስገራሚዎች ናቸው።
1) በስንዴ ምርት እጦት ምክንያት ፋብሪካዎች እየተዘጉ፣ የዳቦ ዋጋም በእጥፍ እየጨመረ ነው። መንግሥት ደግሞ ወደ ውጭ ስንዴ ለመላክ በየክልሎች ኮታ ጥሏል።
2) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር መለስተኛ አውሮፕላን ማስገዛት በሚችል ገንዘብ ባስ ገዝቷል። ይህም የሰሞኑ አስገራሚ ጉዳይ ነበር። ነገርግን በኢመደበኛነት የተሰጠው ማስተባበያ ዋጋው የጨመረው መንግሥት በጥቂር ገበያ ዋጋ በመግዛቱ ነው የሚል ነው። ዶላር በጥቁር ገበያ ከመቶ ብር ዘሏል። መንግሥት ዶላር በጥቁር ገበያ ከገዛ ከመንግሥት የበለጠ ሌላ ፈርጣማ ኢመደበኛ መንግሥት ተፈጥሯል ለማለት ያስደፍራል።
3) የአማራ ክልል የትናንት ታሪክ ጥገኛ እና ጠባብ ብሎ የወረፋቸው አካላት በኢመደበኛ ሁኔታ ምላሽ ሰጥተዋል። የአማራ ክልል ፖለቲከኞች በመንግስት ውስጥ ሆነው ሌላ መንግስት ለመፍጠር እየሞከሩ ቢሆንም አይሳካላቸውም። ምክንያቱም ከአዲስአበባ ፖለቲካ የሉበትም ተብለዋል። ባህርዳር ላይ ሆኖ ማመፅ ለአራት ኪሎ ብዙ አያስደነግጥም የሚል ትንታኔ ተሰጥቷል።
4) የደቡብ ሱዳንታጣቂዎች ሁለት መቶ ኪሎሜትር ዘልቀው ገብተው ኢትዮጵያውያን ጨፍጭፈው የከተማ ስም እስከመቀየር መድረሳቸውን ሪፖርተር አስነብቧል። መቶ ካሬ የመኖሪያ ቦታ ያጣ ኢትዮጵያ በኑሮ ውድነት እያማረረ ሱዳን 200ኪሎሜትር መውሰዷ አስገራሚ ሆኗል።
5) ጃልመሮ እና ሽመልስ አብዲሳ በይፋ ሊታረቁ መሆናቸው የምክርቤት አጀንዳ ነበር። ኦነግ እና የኦህዴድ ብልፅግና ለመታረቅ በይፋ ሁለቱም ተስማምተዋል።መታረቃቸው ማነው ኦነግ፣ የትኛው ነው ኦህዴድ ብሎ ለመለየት ለተቸገረው አንድ ሆነው መታየታቸው መልካም ነው። መደናገሩን ያስቀራል።
6) ሲሸፍቱ አቶ፣ ሲስማሙ አባ እየተባሉ የነበሩ የሀይማኖት አባቶች በስምምነት እና እርቅ ከዋናው ሲኖዶስ ጋር ቢጣመሩም፣ በሀይማኖት ምክንያት እስሩ እና ከስራ መታገዱ ሙሉ በሙሉ እንዳልቀረም ተሰምቷል።
ከሰሞናዊ ሁኔታዎች ተነስቶ ነገሩ ሲተነተን የሀገር ሉዓላዊነት ፈተና ውስጥ እየወደቀ እና ሀገራዊ አንድነትም እየኮሰመነ አጉል ወሬ እና ሀገራዊ ዓላማ ቢስነት እየገነነ መምጣቱን ነው። ይሄን ለማረምም ዕቅድ ቀርቶ ቅን ፍላጎት እንደሌለ ነው።
@የሺሃሳብ አበራ
1.5K views16:39