Get Mystery Box with random crypto!

ዋልድባ ገዳም

የቴሌግራም ቻናል አርማ waldiba — ዋልድባ ገዳም
የቴሌግራም ቻናል አርማ waldiba — ዋልድባ ገዳም
የሰርጥ አድራሻ: @waldiba
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.44K
የሰርጥ መግለጫ

👉 ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ በነገረ መለኮት፣ በነገረ ማርያም፣ በነገረ መስቀል፣ በነገረ ቅዱሳንና በምሥጢራት ላይ፣
👉 ወቅታዊ የቤ/ክ ሁኔታና የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች፣
👉 የመንፈሳዊ ጉዞዎች ዓመታዊ መርሐ ግብር...
ለጥያቄዎ
@zeWaldiba_bot
@Gedamewali
@Elmestoagia
👇 YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCUBStsekCniQtATyZDdFqQQ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-30 11:40:20 መኮሬታ Mekoreta Tube



514 viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, edited  08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 11:53:15 “ባሕረ ወመስዐ አንተ ፈጠርከ፤ ታቦር ወአርሞንኤም በስመ ዚአከ ይትፌሥሑ ወይሴብሑ ለስምከ። - ሰሜንንና ደቡብን አንተ ፈጠርህ ታቦርና አርሞንዔም በስምህ ደስ ይላቸዋል። እጅህ በረታች ቀኝህም ከፍ ከፍ አለች።” መዝ ፹፰፥ ፲፪
እንቋዕ ለበዓለ ደብረ ታቦር ፩ዱ እም፱ቱ ዐበይት በዓላት ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ አብጽሓነ አብጻሕክሙ!

ከጌታችን ዘጠኙ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ የሆነው በዓለ ደብረ ታቦር ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን ወደ ታላቁ የታቦር ተራራ ይዟቸው ሄዶ የምሥጢር ሐዋርያት የተባሉ ፫ አዕማድ ሐዋርያትን ቅዱስ ጴጥሮስን፣ ሁለቱን የዘብዴዎስ ልጆች ቅዱስ ዮሐንስና ቅዱስ ያዕቆብን በርእሰ ደብር ላይ ሌሎቹን በእግረ ደብር አድርጓቸው ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ድንቅ በዓል ነው። በዚህ ጊዜ አማኒያን ሁሉ ሙሴ ነው እንዳይሉ ሞተ ሥጋን ከቀመሱ ቅዱሳን ሊቀ ነቢያት ሙሴን፣ ኤልያስ ነው ብለው እንዳይስቱም እስከ ሐሳዊው መሲህ መነሣት ድረስ ሕያዋን ሆነው ከሚኖሩት (ከብሔረ ሕያዋን) ነቢዩ ኤልያስን አምጥቶ የሙሴና የኤልያስ አምላክ መሆኑን አስረግጦ ገልጦ ጥያቄያቸውን መልሷል። ማቴ ፲፯፥ ፩- ፲፫፣ ማር ፱፥ ፩- ፲፫፣ ሉቃ ፱፥ ፳፰- ፴፮

ደብረ ታቦር በዘመነ ኦሪትም ባርቅና ሰራዊቱ በአምልኮተ እግዚአብሔር በመኖራቸውና በነቢይቱ ዲቦራ ጸሎት ኃይለ እግዚአብሔርን ተጎናጽፈው ለ፳ ዓመታት ያሰቃያቸውን ሲሳራን ከብዙ ሰራዊቱ ጋር ድል ያደረጉበት ቦታ ነው። መሳ ፬፥ ፩- ፳፬

ስለዚህ ታላቅ ተራራ ክብር ነቢየ እግዚአብሔር ኤርምያስ እንዲህ ብሎ ተናግሮ ነበር፦ “እኔ ሕያው ነኝና በተራሮች መካከል እንዳለ እንደ ታቦር፥ በባሕርም አጠገብ እንዳለ እንደ ቀርሜሎስ፥ እንዲሁ በእውነት ይመጣል፥ ይላል ስሙ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር የተባለው ንጉሥ።” ኤር ፵፮፥ ፲፰
2.5K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, edited  08:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 22:05:49 #ደብረ_ስብሐት_አቡነ_ኢዮስያስ_ገዳም
★ Forward & Pin በማድረግ ገዳሙን እናስተዋውቅ
☞ @negeretewahido

★ ገዳሙ በዓድዋ አውራጃ ራህያ አካባቢ ይገኛል። ይህንን በታላቅ ቃልኪዳን የከበረ ገዳም የመሠረቱት ጻድቁ አባታችን መናኔ መንግሥት አቡነ ኢዮስያስ ሲሆኑ ጻድቁ የሸዋው ንጉሥ የአጼ ዓምደ ጽዮን ልጅ ናቸው፡፡ ጻድቁ በልደታቸው ዕለት ጥር 6 ቀን ከእናታቸው ማሕፀን ሲወጡ ቅዱሳን መላእክት ከበዋቸው ታይተዋል፡፡

★ ጻድቁ መናኔ መንግሥት ተብለው ይጠራሉ፤ ምክንያቱም የንጉሥ ልጅ ሆነው ሳለ በዓለም ነግሠው መኖርን ንቀው በምናኔ ሕይወት በብሕትውና ኖረዋልና። በዚህ የምናኔ ሕይወታቸውም በደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፣ በሐይቅ እስጢፋኖስ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ እና በደብረ በንኮል አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳማት ገብተው ለብዙ ዘመናት በታላቅ ተጋድሎ ኖረዋል፡፡ ብሉይንና ሐዲስን፣ መጽሐፈ መነኮሳትን እና መጽሐፈ ሊቃውንትን ከሥርዓተ ገዳምና በቅድስና ከተሞላ የብሕትውና ሕይወት ጋር ተምረዋል።

★ ጻድቁ በታላቁ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ለብዙ ጊዜ በአርድእትነት አገልግለው ሥርዓተ ምንኩስና ከተፈጸመላቸው በኋላ ወደ ትግራይ ደብረ በንኮል አቡነ አድኃኒ (መድኃኒነ እግዚእ) ገዳም በእግዚአብሔር ትእዛዝ ሄዱ፡፡ በዚያም በታላቅ ተጋድሎ ኖረው በታላቁ ጻድቅ በአቡነ መድኃኒነ እግዚእ እጅ አስኬማ መላእክት ተፈጸመላቸው፡፡

★ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም ሰባት ዓመት ከእሳቸው ጋር ካቆዩኣቸው በኋላ አቡነ ኢዮስያስን ወንጌልን ዞረው እንዲሰብኩና የራሳቸውን ገዳም እንዲገድሙ በማዘዝ መርቀው ሸኝተዋቸዋል፡፡ አቡነ ኢዮስያስም ታቦተ ማርያምን ይዘው ወደ ዓድዋ አውራጃ በመምጣት አሁን ክቡር ዐጽማቸው ያለበትን ቦታ በመገደም በርካታ መናኒያንን አፍርተውበታል።

★ ጻድቁ ታቦተ እግዝእትነ ማርያምን ይዘው መጥተው ስለገደሙት ቦታው ማርያም ስረዊቶ ይባል ነበር። በኋላ ደግሞ የጻድቁ ተከታዮች መናኒያን ከመብዛታቸው የተነሳ ማኅበረ ማርያም ተብሎ ይጠራ ነበር። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን "ደብረ ስብሐት አቡነ ኢዮስያስ ገዳም" ተብሎ ተሰይሟል።

★ በገዳሙ ላይ ከተራራው ወረድ ብሎ ጻድቁ ያፈለቁት ፈዋሽ ጠበል አለ። በተጨማሪም የጻድቁ የእጅ መስቀል በገዳሙ ውስጥ ይገኛል፤ ገዳሙን ለመሳለም የሚመጣ ኦርቶዶክሳዊ እንግዳ ይህንን መስቀላቸውን ተሳልሞና በመስቀሉ ታሽቶ ልቡ በሃሴት ተሞልቶ መሻቱ ተፈፅሞለት ይመለሳል።

★ ጻድቁ እንደ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ አንበሳ በረዲእነት የሚያገለግላቸው እጅግ ተአምረኛ አባት ናቸው። በቅዱስ ገድላቸው ላይ ከተጻፈው በርካታ ተአምራቸው ውስጥ ጎላ ባለ መልኩ በስእለ አድኅኗቸው ላይ የተሳለው እንዲህ ነው።

ከደብረ በንኮል ተነስተው አክሱም ጽዮንን እጅ ነስተው ቃልኪዳን ወደተቀበሉበት ወደዚህ ገዳም ሲመጡ በመንገድ ላይ አራት ሰዎች ያለአግባብ ሞተው ቢያገኙ በጸሎታቸው አስነስተዋቸዋል።

በአንድ ወቅት አላዊያን ሠራዊት (ከሃዲያን የሆኑ አረማውያን) የጻድቁን ገዳም ለማጥፋት ጦር ሰራዊት አስከትለው ጋሻ ታጥቀው ጦር ሰብቀው መጥተው ቢያስቸግሯቸው ጻድቁ በጸሎታቸው አምላከ አበው ቅዱስ እግዚአብሔርን ጠየቁ። እግዚአብሔርም በዚህ ጊዜ ጸዓዳ ነጭ የሆነ የንብ መንጋ ላከላቸው። ንቦቹም የአመጣጣቸው ነገር ተአምረኛና በሚገርም ፍጥነት ሲሆን የጻድቁን ጠላት የአረማውያን ሠራዊትን አንድ በአንድ እየነደፉ በመግደል መሉ በሙሉ አጥፍተውላቸዋል፡፡

በገዳማቸው ውስጥ በበዓላቸው ቀን ገድላቸው ሲነበብ አጋንንት ከሰው ልቡና እንደ ትቢያ በነው ይጠፋሉ፡፡

★ ጻድቁ በዓለ ዕረፍታቸው ነሐሴ 6 ቀን ሲሆን በዕረፍታቸው ጊዜ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ዕረፍታቸው ማግስት (ማለትም ከነሐሴ 5 እስከ 7 ድረስ) ለ3 ቀናት ለረጅም ጊዜ ቆመው ይጸልዩበት በነበረውና ኋላም ባረፉበት ሶሀባ ወንዝ ላይ ዓሣ ከሰማይ ዘንቦላቸዋል፡፡

★ ወደ ታላቁ ገዳማቸው መጥቶ መካነ ዐፅማቸውን የተሳለመውን እስከ 30 ትውልድ ድረስ እንደሚምርላቸው ጌታችን ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ይህንን ቃልኪዳናቸውን አስቦ ልጁን በስማቸው ለሰየመ መልአከ ሞትን ፈጽሞ እንደማያይ መጽሐፈ ገድላቸው ይናገራል፡፡ በተጨማሪም ከመቃብራቸው ታፍሶ ለምዕመናን የሚሰጠው እምነት ከማንኛውም አደጋ ሁሉ ይጠብቃል። የጻድቁ አባታችን የአቡነ ኢዮስያስ በረከት ረድኤታቸው ይደርብን፤ በጸሎታቸው ይማረን። አሜን!!!
☞ @negeretewahido

★ የገዳሙ አድራሻ፦
ከዓዲዋ ከተማ ወደ ዕደጋ ዓረቢ ወርዒለኸ ከተማ እና ነበለት ከተማ በሚወስደው መንገድ ራህያ ከምትባለው አነስተኛ ከተማ ላይ በተተከለው የገዳሙ ታፔላ በኩል ወደ ግራ ታጥፈው እስከ 10 ኪ.ሜ የጠጠር መንገድ ከተጓዙ በኋላ ለጎምት ግድብን እንዳለፉ በእግር ከ35 ደቂቃ አይበልጥም።

★ በአክሱም ጽዮን ማርያም ንግሥ የ21 ቀናት ልዩ የዙር ጉዞ ከተሳለምናቸው በቃልኪዳን የከበሩ አስደናቂ ገዳማት መካከል አንዱ ነው። በመንፈሳዊ ጉዞዎቻችን ለመሳተፍ በሚከተሉት የስልክ ቁጥሮች ይደውሉ፦
☞ 0901070707 / 0911289877
☞ @negeretewahido

❖ ብዙዎች የበረከቱ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ጦማሩን Share, Like, Tag & Comment አድርጉት፤ የቅዱሳት መካናትን የቃልኪዳን በረከት እንዲያገኙ ለሌሎች ምክንያት መሆን በራሱ ልዩ በረከት ያሰጣልና Share & Tag በማድረግ ለወዳጆችዎ ያካፍሉት።
"ገዳምህን የረገጠ" ብቻ ሳይሆን "ገዳምህን ለሌሎች ያሳዬ ...እምርልሃለሁ!" ተብሎ ቃል የተገባላቸው ቅዱሳን እንዳሉን ገድለ አቡነ ዘርዓ ብሩክን ያስታውሱ!!!

በቴሌግራም ይቀላቀሉን
☞ @waldiba
☞ @waldiba
☞ @waldiba

በቲክቶክ ይከታተሉን
☞ tiktok.com/@betewali

❖ የዩቲዩብ ቻናላችንን « መኮሬታ Mekoreta Tube »ን በሚከተለው ሊንክ ከፍተው Subscribe & Join ያድርጉ።
☞ https://m.youtube.com/channel/UCUBStsekCniQtATyZDdFqQQ
2.5K viewsዘዋልድባ 0901070707, 19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 13:10:36 በገዳም በበረሓ ያሉት አበውም ምስጋናዋን በማድረስ ፍጹም በረከቷን ሽተው በፊቷ ይማለላሉ፤ ርሷም ለሱባኤዋ በወደቁበት በረሐ እየተገለጸች በረከቷን ታድላቸዋለች፤ ክቡራን ምእመናንም ከልጅ እስከ ዐዋቂ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመሰብሰብ ቅዳሴ ማርያምን በማስቀደስ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በመቀበል፤ እጅግ ድንቅ በኾነ መልኩ ሱባኤውን ይፈጽሙታል፤ በመኾኑም ትውልድ ኹሉ ብፅዕት የሚላት አጋንንትን የምታሸብራቸው የአምላካችን እናትም በቀንም ኾነ በሌሊት ከእኛ በረድኤት ባለመለየት ረድኤቷን በረከቷን ልታትረፈርፍልን የጾመ ፍልሰታ ሱባኤ ደርሷልና በእጅጉ ደስ ይበለን፤ ሐሴትም እናድርግ!!!፡፡

የምእመናን ወዳጅ የመስቀል ሥር ሥጦታችን በዚኽ የፍልሰታ ሱባኤ ለእኛም በረድኤት ትገለጽልን!!! መልካም የበረከት ሱባኤ!!!
2.1K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, 10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 13:10:35 [የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚኽ የፍልሰታ ሱባኤ ለምእመናን መገለጥ]
በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ

ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በመዝ ፵፬፥፲፪ ላይ “ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኲሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር” (የምድር ባለጠጎች አሕዛብ ኹሉ በፊትሽ ይማለላሉ) በማለት ትንቢትን እንደተናገረላት ብዙዎች ቅዱሳን ቅድስት ድንግል ማርያምን ተገልጻላቸው ለማየት ተመኝተዋል፤ ብዙዎቹም ልመናቸው ተሰምቶላቸው የአምላክ እናት ተገልጻላቸው እጅግ አስደናቂ ውበቷን አይተዋል፡፡

ከነዚኽ አባቶች ውስጥ ቅዱስ ኤፍሬም፣ ቅዱስ ያሬድ፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፣ አባ ይሥሐቅ፣ አባ ቴዎፍሎስ እና በደብረ ምጥማቅ የነበሩ ምእመናን ሌሎችም ብዙዎች ንጹሓን ክርስቲያኖች ይገኙበታል፡፡

የመልክአ ማርያም ደራሲም የአምላኩን እናት ቅድስት ድንግል ማርያምን ፊቷን ለማየት ሽቶ በናፍቆት ኾኖ፡-
“ሰላም ለመልክእኪ ዘተሠርገወ አሜረ
ዘያበርህ ወትረ
ፍቅርትየ አንቲ እንተ ታበድሪ ፍቅረ
አርእዪኒ ገጸ ዚኣኪ ማርያም ምዕረ
ዘኢይሰምዖ ካልእ እንግርኪ ነገረ”
(ኹልጊዜ (ዘወትር) የሚያበራ ፀሓይን ጌጥ ላደረገ መልክሽ ሰላምታ ይገባል፤ ፍቅርን የምትመርጪ (የምታስቀድሚ) አንቺ ፍቅረኛዬ ማርያም ሌላ የማይሰማው ነገርን እነግርሽ ዘንድ አንድ ጊዜ ያንቺን ፊት ግለጪልኝ) በማለት ተማፅኗታል፡፡

ቅዱስ ያሬድ አባታችንም በማይ ኪራሕ ሳለ እመቤታችን ተገልጻለት ፊቷን ለማየት ታድሏልና ይኽነን በዐይኑ ያየውን ውበቷን በድጓው ላይ እንዲኽ ሲል ጽፎታል፡-

“አይ ይእቲ ዛቲ እንተ ትወርድ እምሰማይ፤ ብርህት ከመ ፀሓይ፤ አዳም ቆማ ወክሣዳ ከመ አርማስቆስ፤ መዐዛ አፉሃ ከመ ኮል” (ከሰማይ የምትወርደው እንደ ፀሐይም የምታበራው ርሷ ማን ናት! አንገቷ እንደ ግንብ ቀጥ ያለ ነው፤ የአፏም መዐዛ እንደ እንኮይ ነው) በማለት በተመስጦ የተመለከተውን ውበቷን ተናገረ፡፡

ይኽ የቤተ ክርስቲያን ጌጥ ቅዱስ ያሬድ በዚኽ ሳያበቃ በመላእክት እየተመሰገነች ስለተገለጸችለት ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ያየውን የውበቷን ነገር ሲናገር፦
“እምኀበ መላእክት ትሴባሕ አዳም ሥና፤ መዐርዒር ቃላ ወኲሉ ነገራ በሰላም … እምወርኅ ወእምፀሓይ ይሤኒ ላሕያ …ከመ ፍሕሶ ቀይሕ ከናፍሪሃ ወከመ ኮል መዐዛ አፉሃ ወከመ ሮማን ቂሐተ መላትሒሃ … (በመላእክት ትመሰገናለች፤ ደም ግባቷ ያማረ ነው፤ ቃሏ እንደ ማር የጣፈጠ፤ ነገሯ ኹሉ በሰላም የተመላ ነው … ውበቷ ደም ግባቷ ከጨረቃና ከፀሓይ ይልቅ ያምራል፤ ከንፈሮቿ ፍሕሶ እንደሚባል አበባ ቀይ ናቸው፤ የጒንጯ ቅላትም እንደ ሮማን ቅርፍት ነው) እያለ ሊቁ ማሕሌታይ በመንፈስ ተቃኝቶ ይመሰክርላታል፤ አይ መታደል! አይ መባረክ!

ውዳሴዋ በእጅጉ የበዛለት ስለ ርሷ ኆኅተ ብርሃን፣ እንዚራ ስብሐት፣ መዐዛ ቅዳሴ፣ አርጋኖን፣ ሰላምታ፣ መዝሙረ ድንግል እና ሌሎችም ብዙ ብዙ ለመሰከረላት ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ብዙ ጊዜ እየተገለጸችለት በዐይኑ ተመልክቷታልና የመልኳን ውበት በአርጋኖን ዘቀዳሚት ላይም፡-
“አልቦ ዘይሤንዮ ለላሕይኪ ኢ ጎሕ ወኢበርህ ኢ ፀሓይ ወኢወርኅ ኢ ዋካ ወኢጸዳል አልቦ ዘይበርህ እምጸዳለ ዐይንኪ ኢ ቤዝ ዘያንበለብል በገጸ ሰማይ ወኢባሕርይ ዘያንጸበርቅ ዲበ ርእሰ ነገሥት ወአልቦ ዘይምዕዝ እምጼና አንፍኪ ወእምጼና አልባስኪ ኢከልበኔ ወኢሐንክሶ ወኢአስጰዳቶስ ወኢናርዱ ቅድው ዘዕጹብ ሤጡ ወመዐድም ኲለንታኪ ወክሉል በጸጋ መንፈስ ቅዱስ”

(ደም ግባትሽን የሚያምረው (የሚበልጠው) የለም፤ የንጋት ውጋገንም ቢኾን! ብርሃንም ቢኾን! ፀሓይም ቢኾን! ጨረቃም ቢኾን! ወዝሽን ለዛሽን የሚመስለው የለም፤ ከዐይንሽ ብርሃን ይልቅ የሚበራ የለም፤ በሰማይ ፊት የሚንቦገቦግ ኮከብም ቢኾን! በነገሥታት ራስ ላይ የሚያንጸባርቅ ዕንቊም ቢኾን! ከአፍንጫሽም መዐዛ ከልብሶችሽም ሽታ የበለጠ የሚሸት የለም፤ ከልበኔም ቢኾን! ሐንክሶም ቢኾን! አስጰዳቶስም ቢኾን! ዋጋው ውድ የኾነ ናርዱ የሚባል ሽቱም ቢኾን! ኹለንተናሽ ያማረ ነው በመንፈስ ቅዱስ ጸጋም የተጋረደ ነው) ብሏታል፡፡

ልክ እንደ ርሱ የአምላክን እናት ፊቷን ለማየት የተመኙ ብዙዎች ቅዱሳን ነበሩ፤ ለምሳሌም ያኽል ከቅዱሳን አበው መኻከል አባ ይሥሐቅ እመቤታችንን በፍጹም ልቡናው ከመውደዱ የተነሣ ከሠርክ ጸሎት በኋላ ሌሎች መነኮሳት ለመኝታ ወደ የበኣታቸው ሲኼዱ ርሱ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመኼድ በቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ፊት ቆሞ በፊቷ እየተማለለ ሦስት መቶ ስግደትን እየሰገደ፤ በእያንዳንዱ ስግደቱ ላይ “ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ አርእየኒ እመከ አሐተ ሰዓተ” (ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለአንዲት ሰዓት እናትኽን አሳየኝ) እያለ በመጸለይ ለሰባት ዓመት ቆየ።

በሰባተኛው ዓመት በታላቅ ግርማ ተገልጻለት የአምላክን እናት ፊት ለማየት በቅቷል፤ ርሷም ምን እንደሚሻ ብትጠይቀው በታላቅ መንፈሳዊ ደስታ በመኾን የንግሥተ ሰማይ ወምድር የርሷን ገጽ ያዩ ዐይኖቹ ሌላ ነገርን ማየት እንደማይፈልጉና ከልጇ እንድታማልደው ብቻ እንደሚፈልግ ነግሯት፤ ርሷም ከሦስት ቀን በኋላ እንደሚያርፍ ክፍሉም ከርሷ ጋር መኾኑን ገልጻለት ባርካው ዐርጋ፤ መልኳን አይቶ በሦስተኛው ቀን ይኽ ቅዱስ አባት ዐርፏል፡፡

የእመቤታችን ፍቅር በእጅጉ የበዛለት አባ ጽጌ ድንግልም በደብረ ምጥማቅ በታላቅ ክብር ተገልጻ ለምእመናን የታየችው የአምላክ እናት ለርሱም ትገለጽለት ዘንድ በማሕሌተ ጽጌ መጽሐፉ ላይ፡-
“አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኀምሰ ዕለታተ
ትእምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ
ሚ መጠነ ማርያም ታሥተፌሥሒ ትፍሥሕተ
ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሑ መዓልተ
ብፁዕ ዘርእየኪ በሕልሙ ሌሊተ”
(የፊትሽን መልክ ያይ ዘንድ የሞተ ሰው እስኪነሣ ድረስ በደብረ ምጥማቅ ለዐምስት ቀናት ያኽል በተገለጽሽ ጊዜ ማርያም ምን ያኽል ደስ ታሰኚ ኖሯል! በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ምስጉን ነው) በማለት ተማፅኗታል፡፡

የእመቤታችን ታማኝ ወዳጅ አባ ጽጌ ድንግል በተመስጦ በመኾን እጅግ ድንቅ የኾነችውን የአምላክን እናት ሥዕል ካየ በኋላ ይኽነን የምስጋና ቃላት ለርሷ ያቀርባል፡-
“ሥዕልኪ ጽግይተ ላሕይ ዘከመዝ ትኤድም በዓለም
እፎ ይሤኒ በሰማይ ላሕየ ገጽኪ ማርያም
ሐሤተ ትእምርትኪ እጽገብ አስተርእዪኒ በሕልም
እስመ አውዐየኒ ነደ ፍቅርኪ ፍሕም
አጥፍኦቶ ዘኢይክል ዝናም”
(ማርያም ሥዕልሽ በዓለም እንዲኽ የምታበራ ከኾነ በሰማይ የፊትሽ መልክ ምን ያምር! አንቺን ከማየት የሚገኘውን ደስታ እጠግብ ዘንድ በሕልም ተገለጪልኝ፤ ዝናብ ሊያጠፋው የማይቻለው የፍቅርሽ እሳት አንድዶኛልና) ብሏል፡፡

በመኾኑም በዚኽ ሱባኤ ሐዋርያት የአምላክን እናት አይተው እንደተደሰቱ፤ ዛሬም ለእኛ ለልጆቿ በረድኤት ትገለጽልን ዘንድ አበው ካህናት ሌሊቱን በሰዓታት ምስጋና “ንዒ ኀቤየ ኦ ድንግል ምስለ ወልድኪ ፍቁርኪ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ትባርኪ ላዕሌነ” (ድንግል ሆይ ከተወዳጅ ልጅሽ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋራ ወደ እኔ ነዪ እኛን ትባርኪ ዘንድ (በእኛ ላይ በረከትን እንድታሳድሪ) በማለት ይማፀኗታል፤ እኛም የማይጠገበው ውዳሴዋን ቅዳሴዋን በመተርጐም የቅዱስ ኤፍሬም የአባ ሕርያቆስ እመቤት ትባርከን ዘንድ እንለምናታለን፡፡
2.5K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, 10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 20:41:24
1.8K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 20:41:23
1.7K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 20:40:42 #ጥንታዊው_ቅድስት_መስቀል_ክብራ_ገዳም
በትግራይ ክልል ሽሬ አውራጃ ከሽረ ከተማ 24 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ዞማ መዳባይ ታብር በሚባል አካባቢ ውብ በሆኑ በሰንሰለታማ ትላልቅ ድንጋዮች መካከል የሚገኝና በመሠላል የሚወጣ ድንቅ ገዳም ነው። ወደ ገዳሙ ለመሄድ ከሽረ እንዳ ሥላሴ በሞተር መጓዝ አለበለዚያ ግን በእግር ከ4:30 በላይ መጓዝ ግድ ይላል።

እናታችን ቅድስት መስቀል ክብራ ትውልዷ ሰሜን ወሎ ላስታ ቡግና ሲሆን የቅዱስ ላሊበላ ባለቤት ናት። ቅዱስ ላልይበላን እና ቅድስት መስቀል ክብራን ያጋባቸው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል እንደሆነ የሁለቱ ቅዱሳን ዜና ሕይወት (መጽሐፈ ገድላቸው) ይገልጣል። በፈቃደ እግዚአብሔር በተፈጸመው በዚህ ቅዱስ ጋብቻቸውም ከቅዱስ ነአኩቶ ለአብ ቀጥሎ በላስታ ላይ የነገሠውን ደገኛውን ንጉሥ ይትባረክን ወልደዋል፡፡

መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማይ ነጥቆ ወስዶ የሚያንጻቸውን የሕንጻ ዲዛይኖችና ሌሎችንም ብዙ ምሥጢራትን ካሳየውና ወደ ምድር ከመለሰው በኋላ ድጋሚ ተገልጦለት፦ "እንዳንተ የተመረጠች ናት፤ እንደ ልብህም ትሆናለች፤ ሥራዋም ከሥራህ አያንስም፤ እርሷ የተመረጠች የእግዚአብሔር አገልጋይ ናትና።" በማለት መልአኩ የቅድስት መስቀል ክብራን ንጽሕናና ቅድስና መስክሮላታል፡፡

ቅዱስ ላሊባላ 11 እጅግ አስደናቂ የሆኑ ፍልፍል ቤተ መቅደሶቹን ከመላእክት ጋር ሲያንጽ ብታየው ልቧ በመንፈሳዊ ተመስጦ ተመልቶ እርሷም እግዚአብሔር ፈቅዶላት አስደናቂውን የአባ ሊባኖስን ቤተመቅደስ ራሷ እንዳነጸችው መጽሐፈ ገድሏና ገድለ ቅዱስ ላሊበላ ያስረዳል፡፡

ቅድስት መስቀል ክብራን ወደ ትግራይ እየመራ የወሰዳት ራሱ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ እርሷን በትግራይ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል እንዲጠብቃት ከተዋት በኋላ ቅዱስ ላሊበላን ደግሞ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ መንግሥተ ሰማያት አውጥቶታል፡፡ ቅድስት መስቀል ክብራም በትግራይ ሆና መልአኩ እየጠበቃት ከሰው ተለይታ በታላቅ ተጋድሎ ኖረች፡፡ በቀን እልፍ እልፍ እየሰገደች በታላቅ ተጋድሎ ስትኖር ጌታችን ተገልጦ ክብሯ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ጋር እኩል መሆኑን ነግሯታል፡፡

ይህቺም ቅድስት እናት ብዙ ሐዋርያዊ አገልግሎት ፈጽማለች፡፡ ለምሳሌ በመስቀል ጦርነት ጊዜ እስላሞች ከባሕር ማዶ እየፈለሱ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ በፍቅር እየተቀበለችና እያስተናገደች ሃይማኖትንና ሕገ እግዚአብሔርን እያስተማረች ወደ ክርስትና እንዲገቡና እንዲጠመቁ አድርጋለች። የጻድቋ ረድኤት አይለየን፤ አምላከ መስቀል ክብራ በየዓመቱ ሐምሌ 27 ቀን ከሚከበረው በዓለ ዕረፍቷ የቃልኪዳን በረከቷን ያድለን፤ በጸሎት ልመናዋ ይማረን። አሜን!!!

ገዳሙን በምስልና ድምጽ ለመመልከት የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ (Link) ይክፈቱ፤ ለተጨማሪ ቪዲዮዎች የዩቲዩብ ቻናላችንን (መኮሬታ Mekoreta Tubeን) ይቀላቀሉ።


2.1K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, 17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-31 11:18:30 ፬ኛ. የሚጠብቀንን ሰማያዊ ክብር በማሰብ
ክርስትና በሰማያዊ ተስፋ የተሞላ ብርሃናማ ሕይወት ነዉና ይህን ተስፋችንን በማሰብ ነጭ ነጠላን እንለብሳን።
☞ @negeretewahido

✞☞ ስለዚህ ነገረ መስቀሉን በማሰብ ነጠላችንን በትእምርተ መስቀል አጣፍተን መልበስ መንፈሳዊ ትርጉም አለውና እንዲሁ በዘፈቀደ የሚለበስ አለመሆኑን በመገንዘብ ሥርዓቱን ልንተገብር ይገባል። የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ልጆች ሁሉ ወንዶችም ሴቶችም ከላይ የተጠቀሱትን ሁሉ እያሰብን በጸሎተ ኪዳኑም፣ በሥርዓተ ቅዳሴውና በበዓለ ንግሡም ላይ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ጠብቀን ነጠላ ለብሰን በቤቱ ብንገኝ መልካም ነው። «አባቶች የሠሩትን የቀድሞውን የድንበር ምልክት አታፍልስ» /ምሳሌ ፳፪፥ ፳፰/ ሁላችንም ሥርዓተ ቤተክርስትያንን እንድንጠብቅ ልቦና ይስጠን።

✞☞ እግዚአብሔር ሁላችንንም እንደ ፍላጎታችን ሳይሆን እንደ እርሱ ፈቃድ እንድንመራ ዓይነ ልቦናችንን ያብራልን! ይህ እራስን መግዛት ለቃሉ አለመታዘዝ ብዙዎቻችን ጋር ያለ ችግር ነው ይህ የሆነው የእግዚአብሔር ፍቅር በውስጣችን ሳይኖር የዓለምን ፍቅር አብልጠን ምን ችግር አለው? እያልን በእግር ብቻ በቤቱ መመላለስ ስለለመድን ነው። ትልቁ ችግር ያመጣው ምን ችግር አለው? ነው። ለዚህም ማሳያ እንደ ፕሮቴስታንት ተሃድሶ መና*ፍ*ቃን እምነት ያለ ዶግማና ቀኖና በራሳችን አስተያየት የምንጓዝ ቢሆን ብዙ ድርጅት በሆንን ነበር።

✞☞ እንደ ቤተክርስቲያን ስርዓት ለመመላለስ የሚቸግረን ትክክል ያልሆነውን የዓለም ስርዓት ስለተለማመድን እንጅ ቅድስት ቤተክርስቲያናችንማ በተገቢው ሥርዓት ኖረን ሰማያዊ ክብር የምናገኝበትና አንድ ሀሳብ አንድ ዓላማ የሚያረገንን ዶግማና ቀኖና ሰርታልናለች። ከመምህረ ንሰሃችን (ንስሃ አባታችን) ጋር በመመካከር፤ በግልና በማህበራዊ ጸሎቶች በመትጋት፤ አንዱ ለሌላው በመጸለይ፤ ሁልጊዜ ቅዱሳት መጽሐፍትን በመመርመር ሊያዘናጉን ከሚችሉ ሁኔታዎች በመራቅ ለእግዚአብሔር ሕግ መገዛት እንችላለን። ትእዛዙን ፈጽመን ለመኖር የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ሁላችንንም ይርዳን!!!

አንድ እህታችን በውስጥ መስመር «ነጭ ነጠላ ለምን እንለብሳለን? መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ አለውን?» ብላ ለጠየቀቺው ጥያቄ መልስ ለመስጠት እንጅ በሥርዓተ አበው መሠረት በአግባቡ ኖረን መንፈሳዊ ዋጋ ለማግኘት መጀመሪያ ሥጋንና ነፍስን ማንጻት ከዚያም ለፍጻሜ የምታበቃ ልብን ማንጻት እንዲገባ አረጋዊ መንፈሳዊ ይገልጣል። ጌታችን በወንጌል፦ “ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና።” እንዳለ። ማቴ ፭፥ ፰

ቅዱስ ጳውሎስም አንድ በጎ ክርስቲያን በቀና እምነት የጸና የልብና የሕሊናን መንፈሳዊ ዝግጅት ከምግባራዊ ፍቅረ ቢጽ ጋር አስተባብሮ ከያዘ ትእዛዛትን ሁሉ መፈጸሙን በምሥጢር ገልጧል።
“የትእዛዝ ፍጻሜ ግን ከንጹሕ ልብና ከበጎ ሕሊና ግብዝነትም ከሌለበት እምነት የሚወጣ ፍቅር ነው፤” ፩ኛ ጢሞ ፩፥ ፭

በተጨማሪም የመንፈስ ልጁን ጢሞቴዎስን ሲመክር እንዲህ ብሏል፦
“ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት ግን ሽሽ፥ በንጹሕም ልብ ጌታን ከሚጠሩ ጋር ጽድቅን እምነትን ፍቅርን ሰላምን አጥብቀህ ተከተል።” ፪ኛ ጢሞ ፪፥ ፳፪

ጻድቁ ኢዮብም የተወለደበት ቀን እስኪረግም ድረስ መከራው በላይ በላዩ ተደራርቦበት በተጨነቀ ጊዜ ቴማናዊው ኤልፋዝ እንዲህ ብሎ ነበር፦
“አምላክህን መፍራትህ መጽናናትህ፥
የቅንነትህም መንገድ ተስፋህ አይደለምን? እባክህ አስብ፥ ንጹሕ ሆኖ የጠፋ ማን ነው? ከልበ ቅንስ የተደመሰሰ ማን ነው?” ኢዮብ ፬፥ ፮- ፯

ስለዚህ ነው ቅዱስ ዳዊትም፦ “አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።” ብሎ የዘመረው። መዝ ፶፥ ፲
ልበ ንጹሓን ሆነን በቅድመ እግዚአብሔር እንድንቆም አምላከ አበው ይርዳን። አሜን!

❖☞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር
✥☞ ወለወላዲቱ ድንግል
✞☞ ወለመስቀሉ ክቡር!
☞ @negeretewahido

✞❖✞ ወቅታዊ የቤተክርስቲያን ጉዳዮችን፣ መንፈሳዊ ጦማሮቻችንንና የመንፈሳዊ ጉዞዎቻችንን መርሐ ግብራት በሚከተሉት ሊንኮች ከፍተው ይከታተሉን፦

በቴሌግራም
☞ @waldiba እና
☞ @negeretewahido

በቲክቶክ
tiktok.com/@betewali

❖ በዩቲዩብ የሚከተለውን የ«መኮሬታ Mekoreta Tube» ማስፈንጠሪያ ተጪነው በመክፈት Subscribe & Join ያድርጉ።
☞ https://m.youtube.com/channel/UCUBStsekCniQtATyZDdFqQQ
2.0K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, edited  08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-31 11:18:30 #ለምን_ነጭ_ነጠላ_እንለብሳለን?
አንዳንዶች ባለማወቅም ይሁን በቅናት «ክርስትና ነጠላ ለብሶ ቤተክርስቲያን መሄድ አይደለም!» ሲሉ ይደመጣሉ። የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ግን መጽሐፍ ቅዱስን ምክንያት አድርጋ ምሥጢሩን ከተግባር ጋር ትገልጻለች። ወደ ቤተ መቅደስ ስንሄድ ነጭ መልበሳችን የተገባ ነው። ነጭ ነጠላ ጋቢ አደግድገን ወይም በትእምርተ መስቀል ለብሰን ቤተመቅደስ ስንቆም የምናስባቸው ምስጢራት አሉ።

✥ ለምን በትእምርተ መስቀል እንለብሳለን?
የክርስቶስን መከራ ለማሰብ፣ ነጠላው ወደ ግራና ቀኝ በትእምርተ መስቀል አምሳል ይጣፋል። በዚህ ጊዜ ጌታችን በዕለተ አርብ የተቀበላቸው ጸዋትወ መከራ እንዲሁም በቀራንዮ በምልዕልተ መስቀል መሰቀሉን ያስታውሰናል። ይኼንን የተመሳቀለ ነጠላ የሚመለከትም ሁሉ የጌታችንን መከራ መስቀል መቀበሉን ያስባል።

✥ የምናጣፋው ነጠላ ነጭ የሆነባቸው ምክንያቶችስ?
☞ ጌታችንን አብነት በማድረግ
☞ ቅዱሳንን አብነት በማድረግ
☞ ቅዱሳን መላእክትን አብነት በማድረግ
☞ ሰማያዊ ተስፋችንን በማሰብ
☞ @negeretewahido

✥†✥ ማስረጃ፦

፩ኛ. ጌታን አብነት በማድረግና ከጌታችን ጋር እንዳለን በማሰብ
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል የምሥጢር ሐዋርያት የሚባሉትን ቅ.ጴጥሮስን፣ ቅ.ዮሐንስንና ቅ.ያዕቆብን ወደ ደብረ ታቦር ይዟቸው ወጥቶ እየተመለከቱት ተለወጠ፤ ፊቱም ማየት እንደ ፀሐይ ልብሱም አጣቢ ሊያነጣው እስከማይችል ነጭ ሆኖ ብርሃነ መለኮቱን ገልጦላቸው ነበር።

ወንጌላዊው ሐዋርያ ቅዱስ ማቴዎስ፦ “ወእምድኅረ ስሱ መዋዕል ነሥኦሙ እግዚእ ኢየሱስ ለጴጥሮስ ወለያዕቆብ ወለዮሐንስ እኁሁ ወአዕረጎሙ ውስተ ደብር ነዋኅ እንተ ባሕቲቶሙ። ወተወለጠ ራእዩ በቅድሜሆሙ ወአብርሀ ገጹ ከመ ፀሓይ ወአልባሲሁኒ ኮነ ጸዐዳ ከመ ብርሃን። - ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ (ደብረ ታቦር) ብቻቸውን አወጣቸው። በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ።” ማቴ ፲፯፥ ፩- ፪ እንዳለ።

ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስም፦ “ወአመ ሰዱስ ዕለት ነሥኦሙ እግዚእ ኢየሱስ ለጴጥሮስ ወለያዕቆብ ወለዮሐንስ ወአዕረጎሙ ደብረ ነዋኀ በባሕቲቶሙ ወተወለጠ ራእዩ በቅድሜሆሙ። ወአልባሲሁኒ በረቀ ወጻዕደወ ጥቀ ዘኢይክል መሃፔል ከማሁ አጻዕድዎቶ በዲበ ምድር። - ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ዮሐንስንም ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። በፊታቸውም ተለወጠ፥ ልብሱም አንጸባረቀ፤ አጣቢም በምድር ላይ እንደዚያ ሊያነጣው እስከማይችል በጣም ነጭ ሆነ።” ማር ፱፥ ፪- ፫ ብሏልና።

ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስም፦ “ወእምድኅረ ዝንቱ ነገር አመ ሳምንት ነሥኦሙ እግዚእ ኢየሱስ ለጴጥሮስ ወለያዕቆብ ወለዮሐንስ ወዐርገ ደብረ ይጸሊ። ወእንዘ ይጼሊ ተወለጠ ርእየተ ገጹ ወጻዕደወ አልባሲሁኒ ወይበርቅ። - ከዚህም ቃል በኋላ ስምንት ቀን ያህል ቈይቶ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ያዕቆብንም ይዞ ሊጸልይ ወደ ተራራ ወጣ። ሲጸልይም የፊቱ መልክ ተለወጠ፤ ልብሱም ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ።” ሉቃ ፱፥ ፳፰- ፳፱ እንዲል።

እኛም ሊያድነንና አርአያ ሆኖ ሊያስተምረን ሰዉ የሆነዉን ጌታችንን አብነት አድርገን ነጭ ነጨላን ለብሰን የደብረ ታቦር ምሳሌ ወደ ሆነችዉ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን እንሰበሰባለን።

፪ኛ. ቅዱሳንን አብነት አድርገን የቅዱሳን የቃልኪዳን ልጆች መሆናችንንና በምልጃ ቅዱሳን መጠለላችንን በማሰብ

ወንጌላዊው ሐዋርያ ቅ.ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ በራእዩ፦ “አምስተኛውንም ማኅተም በፈታ ጊዜ፥ ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ጠበቁት ምስክር የታረዱትን የሰዎች ነፍሳት ከመሠዊያ በታች አየሁ። በታላቅ ድምፅም እየጮኹ፦ ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ፥ እስከ መቼ ድረስ አትፈርድም ደማችንንስ በምድር በሚኖሩት ላይ እስከ መቼ አትበቀልም? አሉ። ለእያንዳንዳቸውም ነጭ ልብስ ተሰጣቸው፥ እንደ እነርሱም ደግሞ ይገደሉ ዘንድ ያላቸው የባሪያዎች ባልንጀራዎቻቸውና የወንድሞቻቸው ቍጥር እስኪፈጸም ድረስ፥ ገና ጥቂት ዘመን እንዲያርፉ ተባለላቸው።” ራእይ ፮፥ ፱- ፲፩ እንዳለ።

አንድም፦ “ከዚህ በኋላ አየሁ፥ እነሆም፥ አንድ እንኳ ሊቆጥራቸው የማይችል ከሕዝብና ከነገድ ከወገንም ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ነጭ ልብስም ለብሰው የዘንባባንም ዝንጣፊዎች በእጆቻቸው ይዘው በዙፋኑና በበጉ ፊት ቆሙ፤” ራእይ ፯፥ ፱ ብሏልና

እኛም ቅዱሳኑን አብነት በማድረግና በፍርድ ቀን በበጉ ከተመሰለው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቀኝ ነጭ ለብሰን የመቆም ተስፋን በመሰነቅ ነጭ ነጠላን እንለብሳለን።

፫ኛ. ቅዱሳን መላእክትን አብነት በማድረግና ቅዱሳን መላእክት ከእኛ ጋር መሆናቸውን ማሰብ

፬ቱም ወንጌላዊያን ስለነገረ ትንሣዔው ሲገልጡ፦
ሐዋርያው ቅ.ማቴዎስ፦ “ወሰርከ ሰንበተ ለጸቢሐ እሑድ መጽአት ማርያ መግደላዊት ወካልእታኒ ማርያ ይርአያ መቃብረ። ወናሁ ኮነ ድልቅልቅ ዓቢይ እስመ መልአከ እግዚአብሔር ወረደ እምሰማይ ወቀርበ ወአንኰርኰራ ለእብን ወነበረ ዲቤሃ። ወራእዩ ከመ ዘመብረቅ ወልብሱ ጻዕዳ ከመ ዘበረድ። - በሰንበትም መጨረሻ መጀመሪያው ቀን ሲነጋ መግደላዊት ማርያምና ሁለተኛይቱ ማርያም መቃብሩን ሊያዩ መጡ። እነሆም፥ የጌታ መልአክ ከሰማይ ስለ ወረደ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፤ ቀርቦም ድንጋዩን አንከባሎ በላዩ ተቀመጠ። መልኩም እንደ መብረቅ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ነበረ።” ማቴ ፳፰፥ ፩- ፫

ወንጌላዊው ቅ.ማርቆስ፦ “ወረዊጾን ርእያሃ ለእብን ኀበ አንኰርኰረት ወዓባይ ይእቲ ጥቀ። ወበዊኦን ውስተ መቃብር ረከባ አሐደ ወሬዛ እንዘ ይነብር መንገለ የማን ወይለብስ አልባሰ ንጹሐ ወደንገፃ። - ድንጋዩ እጅግ ትልቅ ነበርና፤ አሻቅበውም አይተው ድንጋዩ ተንከባሎ እንደ ነበር ተመለከቱ። ወደ መቃብሩም ገብተው ነጭ ልብስ የተጎናጸፈ ጎልማሳ በቀኝ በኩል ተቀምጦ አዩና ደነገጡ።” ማር ፲፮፥ ፬ - ፭

ወንጌላዊው ቅ.ሉቃስ፦ “ወቦኣ ወኢረከባ ሥጋሁ ለእግዚእነ እግዚእ ኢየሱስ። ወእንዘ ይናፍቃ ወየኀጥኣ በእንተ ዝንቱ አስተርአይዎን ክልኤቱ ዕደው ወቆሙ ኀቤሆን ወይበርቅ አልባሲሆሙ። - ገብተውም የጌታን የኢየሱስን ሥጋ አላገኙም። እነርሱም በዚህ ሲያመነቱ፥ እነሆ፥ ሁለት ሰዎች የሚያንጸባርቅ ልብስ ለብሰው ወደ እነርሱ ቀረቡ፤” ሉቃ ፳፬፥ ፫- ፬

ሐዋርያው ቅ.ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ፦ “ወማርያምሰ ቆመት ኀበ መቃብር አፍኣ ወትበኪ ወእንዘ ትበኪ ሐወጸት ውስተ መቃብር። ወርእየት ክልኤት መላእክተ በጸዓድው አልባስ ወይነብሩ አሐዱ ትርኣሰ ወአሐዱ ትርጋፀ ኀበ ነበረ ሥጋሁ ለእግዚእ ኢየሱስ። - ማርያም ግን እያለቀሰች ከመቃብሩ በስተ ውጭ ቆማ ነበር። ስታለቅስም ወደ መቃብር ዝቅ ብላ ተመለከተች፤ ሁለት መላእክትም ነጭ ልብስ ለብሰው የኢየሱስ ሥጋ ተኝቶበት በነበረው አንዱ በራስጌ ሌላውም በእግርጌ ተቀምጠው አየች።” ብሏልና። ዮሐ ፳፥ ፲፩- ፲፪ ብለው ገልጠውታል።

እኛም ቅዱሳን መላእክትን አብነት በማድረግ ነጭ ለብሰን የትንሣኤያችን ማዕከል በሆነች ቅድስት ቤተክርስቲያናችን እንሰበሰባለን። ታድያ እንደ ቅዱሳን መላእክት ለብሶ በቤተክርስቲያን ማገልገልስ ምኑ ነው የሚያስወቅሰውና የሚያሳፍረው? ያኮራል እንጂ!
1.8K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, edited  08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ