2022-07-06 00:15:42
በፍፁም የማይቀርበት ልዩ የንግሥ ጉዞ ወደ ታላቁ #ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳምና_ተአምረኛው_በርሚል_ጊዮርጊስ
❖ በርካታ ጥንታዊ ገዳማትና አድባራትን የምንሳለምበት እና ታሪካዊ ቦታዎችን የምንጎበኝበት የ10 (11) ቀናት ልዩ የንግሥ ጉዞ ነው።
*** መነሻ፦ ሐምሌ 3 (4) ጠዋት 11:30
*** መመለሻ፦ ሐምሌ 13
★ ውስን ወንበሮች ብቻ ስለቀሩን ይህንን ቅዱስ ቦታ ለመሳለም የምትሹ ያልተመዘገባችሁ የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ልጆች ሁሉ ደውሉልንና አብረን እንጓዝ!
★ ብዙዎች የበረከቱ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ጦማሩን Share, Like, Tag, Comment & Forward... አድርጉት፤ የነዚህን ቅዱሳት መካናት የቃልኪዳን በረከት እንዲያገኙ ለሌሎች ምክንያት መሆን በራሱ ልዩ በረከት ያሰጣልና Share & Tag በማድረግ ለወዳጆችዎ ያካፍሉት።
"ገዳምህን የረገጠ" ብቻ ሳይሆን "ገዳምህን ለሌሎች ያሳዬ ...እምርልሃለሁ!" ተብሎ ቃል የተገባላቸው ቅዱሳን እንዳሉን ገድለ አቡነ ዘርዓ ብሩክን ያስታውሱ!!!
@negeretewahido
✞❖✞ ይህ ልዩ የንግሥ ጉዞ መርሐ ግብር፦
በጎርጎራ የሚገኙ የጣና ገዳማትን ያካተተ ሲሆን በሐይቁ ላይ የጀልባ ጉዞን ጨምሮ የ10 (11) ቀናት ቆይታ ይኖረናል።
✞ በዚህ ጉዟችን በቅዱሱ ሐይቅ ላይ የሚገኙ በርካታ ቅዱሳት መካናትን እንሳለማለን።
✞ ምዕራብ ጎንደር ቋራ ደለጉ ተጉዘን በርሚል ጊዮርጊስ በመሄድ ለ30 ደቂቃ ነፍስ ከሥጋ ለይቶ ሲዖልንና ገነትን ካሳየ በኋላ የሚመልሰውን አስደናቂ ፈዋሽ ጠበል እንጠመቃለን።
→ የጉዞ ዋጋ ማረፊያ ቤትን ጨምሮ 4000 ብር
❖ እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ በጉዟችን የምንሳለማቸው ገዳማትና የምንጎበኛቸው መካነ ቅርሶች፦
• ታላቁ ማኅበረ ሥላሴ ገዳም፣
• ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም፣
• ባህርዳር ቅዱስ ጊዮርጊስ፣
• ጥንታዊው ዛራ ሚካኤል፣
• ታሪካዊቷ ጎንደር ቁስቋም፣
• በርካታ የጎንደር ጥንታዊ አድባራትን (ርእሰ አድባራት አደባባይ ኢየሱስ፣ ታሪካዊቷ ግምጃቤት ማርያም፣ ተአምረኛዋ በዓታ ለማርያም፣ ጥንታዊው ደብረ ብርሃን ቅ/ሥላሴ፣ መንበረ መንግሥት መድኃኔዓለም፣ አጣጣሚ ቅ/ሚካኤል፣ ቅ/ሩፋኤል ወአቡነ ሐራ ድንግል፣ አደባባይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፣ ፊት በር አደባባይ ቅ/ጊዮርጊስ፣ ታሪካዊው ጎንደር ቅ/ዮሐንስ መጥምቅ፣... ወዘተ እንሳለማለን፤ በጎንደር ፋሲለደስ ጊቢ የሚገኙትን ታሪካዊዎቹን አብያተ መንግሥታት እንጎበኛለን።)፣
• ታሪካዊው ጣራ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ወአቡነ ገላውዲዎስ የአባቶች ገዳም፣
• ተአምረኛዋ ጣራ ቅድስት ማርያም ገዳም፣
• ተአምረኛው ወይን ዋሻ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም (ጠበሉ ወይን የመሰለ)፣
• ገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል ወቅ/ኪዳነ ምሕረት፣
• ጥንታዊውና ተአምረኛው መካነ ፈውስ ጎንድ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወአቡነ እጨጌ ዮሐንስ አንድነት ገዳም፣
• ታሪካዊቷና ተአምረኛዋ ሠይፍ አጥራ ቅ/ማርያም፣
• ጥንታዊው ወንጪጥ [ወይን እንጨት] ቅ/ሚካኤል ወመድኃኔዓለም፣
• ጥንታዊው ሽንብጥ ቅዱስ ሚካኤል ገዳም፣
• ተአምረኛው አዴት ጺማ ሥላሴ አቡነ ዘርዓ ብሩክ፣
• ታሪካዊቷ ፍልሰታ ደብር ቅ/ማርያም ወቅ/ክርስቶስ ሠምራ፣
• ታሪካዊው አዴት መድኃኔዓለም፣
• ተአምረኛው ጎንጅ ደብረ ጥበብ ቴዎድሮስ አቡነ ግርማ ሥሉስ አንድነት ገዳም [የተአምረኛው ጻድቅ የአቡነ ግርማ ሥሉስ የቃልኪዳን ቦታና ሊቁ ተዋናይ ቅኔን ያስተማረበት]፣
• ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ ርእሰ አድባራት ወገዳማት መርጡለ ማርያም አንድነት ገዳም፣
• ተአምረኛው ድማ ጊዮርጊስ ገዳም፣
• ታሪካዊው ሲኖዳ ቅ/ዮሐንስ፣
• ደብረ ጽሞና አቡነ ሲኖዳ ገዳም፣
#በጎርጎራ_በኩል_ሰባት_ጥንታዊ_የጣና_ገዳማት፦
• ታሪካዊቷ ጎርጎራ ደብረ ሲና ማርያም (አባ ኤስድሮስ በ1312 ዓ.ም የመሠረቷት)፣
• ጥንታዊው ማን እንደ አባ (ማንዳባ) መድኃኔዓለም ገዳም (አቡነ ያሳይ በ14ኛው መ/ክ/ዘ የመሠረቱትና መካነ ዕረፍታቸው) እንድሁም አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ በጣና ሐይቅ ላይ ለ12 ዓመታት ተጋድሎ ያደረጉባት መካነ ጸሎታቸው እና የአባ አትማረኝ መካነ ጸሎት ዋሻ፣
• ብርጊዳ ቅድስት ማርያም የአባቶች ገዳም (አቡነ ቶማስ በ1314 ዓ.ም የመሠረቷትና ያረፉባት)
• አንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የአባቶች ገዳም (በአቡነ እንድርያስ በ1326 ዓ.ም የተመሠረተች)
• ጫንቋ ቅ/ልደታ ለማርያም የእናቶች ገዳም (አቡነ ቶማስ በ13ኛው መ/ክ/ዘ የመሠረቷት)
• ደብረ ገሊላ ኢየሱስ የአባቶች ገዳም (ታላቁ ጻድቅ አቡነ ዘካርያስ በ13ኛው መ/ክ/ዘ የመሠረቷትና ያረፉባት)
• ጀበራ ቅድስት ማርያም የእናቶች ገዳም (በ1327 ዓ.ም በአጼ ዐምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት የተመሠረተች) በጀልባ ተጉዘን እንሳለማለን።
❖★ ማሳሰቢያ፦ ጊዜያችንን በአግባቡ ከተጠቀምን በሕይወታችሁ የማትረሱትና ግሩም በረከት የምታገኙበት አንድ ተአምረኛ ገዳም ሰርፕራይዝ ይኖራል።
፪ኛ #ቁሉቢ_ቅዱስ_ገብርኤል_ገዳም
* በዚህ ጉዟችን ጅጅጋ ከተማ ገብተን የዘመናችን መካነ ሰማዕታት የሆነችዋን ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና ቅ/አማኑኤልን እንዲሁም ታሪካዊውን ደ/ኃ ቅዱስ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናትን፣ በሐረር ከተማ ውስጥ ደግሞ ታሪካዊውን ጀጎል መድኃኔዓለም እና ጥንታዊውን ቅ/ሥላሴን እንሳለማለን።
* መነሻ ሐምሌ 16 እና 17 ከሌሊቱ 11:00
* መመለሻ ሐምሌ 20
* የጉዞ ዋጋ ማረፊያ ቤትን ጨምሮ በ16 ለሚነሣው 1700 ብር በ17 ለሚነሣው 1500 ብር
☞ @negeretewahido
#መነሻ_ቦታዎች፦ አራዳ ቅ/ጊዮርጊስ፣ መስቀል አደባባይ ቅ/እስጢፋኖስ እና መገናኛ
#የምዝገባ_ቦታዎች፦
1) ቀጨኔ መድኃኔዓለም አካባቢ፦፦
ማትያስ የመኪና ዕቃ መሸጫ፣
ማርሶሊ ፎቶ ቤት፣
2) አራዳ ጊዮርጊስ አካባቢ
ገኒ የወንዶች ፀጉር ቤት
መሲ ሕትመትና ማስታወቂያ
3) ባላችሁበት አካባቢ ለመመዝገብ (ትኬት ለመቁረጥ)
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክና በአዋሽ ባንክ ሁሉም ቅርንጫፎች በካሽ ወይም በሞባይል ባንኪንግ በሚከተሉት የመምህር አንተነህ ውብሸት አካውንቶች አስገብታችሁ ደረሰኙን የጉዞው ቀን ይዞ መምጣት ወይንም Screenshot አድርጋችሁ በቴሌግራም ልትልኩልን ትችላላችሁ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000099794899
አቢሲኒያ ባንክ 73439825
አዋሽ ባንክ 01320104564900
#ለመንፈሳዊ_ጉዞዎቹ_የሚያስፈልጉ_ነገሮች፦ የቀበሌ መታወቂያ (ፓስፖርት)፣ ለብርድ የሚሆን ወፍራም ጃኬት፣ ለእግር መንገድ የሚሆኑና ተቀያሪ ጫማዎች፣ ሌሊት የሚለበስ ስሊፒንግ ባግ / ወፍራም ጋቢ/ ወፍራም ወይባ/ ፎጣ/ ቀለል ያለ ብርድ ልብስ/፣ ክርስቲያናዊ አለባበስ፣ ጃንጥላ፣ የእጅ ባትሪ፣ ሰዓት አክባሪነት፣ ታጋሽነት፣ የወጡበትን መንፈሳዊ ዓለማ ለማሳካት በጋራ መትጋት...
✥ ለበለጠ መረጃ፦
0901070707
0911289877
#ማኅበረ_ቅዱስ_ፊልጶስ_ወአቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ
☞ @negeretewahido
✥✞✥ በዚህ መንፈሳዊ Page ላይ የሚተላለፉ መንፈሳዊ ጦማሮች ለእርስዎም ለሌሎችም እንዲደርሱ ፔጁን Like / Follow ሌሎችንም ወደ ፔጃችን ይጋብዙ።
በቴሌግራም ይቀላቀሉን
☞ @waldiba
☞ @waldiba
☞ @waldiba
የዩቲዩብ ቻናላችንን « መኮሬታ Mekoreta Tube »ን በሚከተለው ሊንክ ከፍተው Subscribe & Join ያድርጉ።
https://m.youtube.com/channel/UCUBStsekCniQtATyZDdFqQQ
8.4K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, edited 21:15