Get Mystery Box with random crypto!

ዋልድባ ገዳም

የቴሌግራም ቻናል አርማ waldiba — ዋልድባ ገዳም
የቴሌግራም ቻናል አርማ waldiba — ዋልድባ ገዳም
የሰርጥ አድራሻ: @waldiba
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.44K
የሰርጥ መግለጫ

👉 ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ በነገረ መለኮት፣ በነገረ ማርያም፣ በነገረ መስቀል፣ በነገረ ቅዱሳንና በምሥጢራት ላይ፣
👉 ወቅታዊ የቤ/ክ ሁኔታና የቅ/ሲኖዶስ ውሳኔዎች፣
👉 የመንፈሳዊ ጉዞዎች ዓመታዊ መርሐ ግብር...
ለጥያቄዎ
@zeWaldiba_bot
@Gedamewali
@Elmestoagia
👇 YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCUBStsekCniQtATyZDdFqQQ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-06-21 13:28:48 ሐዋርያዊትና ዓለማቀፋዊት በሆነቺዋ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅናና መመሪያ የሚተዳደር፣ ገቢና ወጪውም ሁልጊዜ በብፁዓን አበው ሳይቀር የሚመረመረው፤ ቤተክርስቲያንን በጥብዓት የሚያገለግል ቤተክርስቲያንም የምታውቀው፤ በከበሩት አበው ጸሎትና ቡራኬ የተመሠረተና ሲመሠረት ጀምሮ ከተቋቋመበት ዓለማ ዝንፍ ያላለ፣ ዘወትር በጸሎተ አበው የሚጠበቅ፣ በተአማኒነቱና ለቅድስት ቤተክርስቲያን የጀርባ አጥንት በመሆኑ ለማይክሮ ሴኮንድ የማንጠራጠረው ድንቅ ማኅበር - ማኅበረ ቅዱሳን

#ጾመ_ሐዋርያትን_ለግብረ_ሐዋርያት
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ ፲፥ ፲፬ ላይ ቃለ ወንጌሉን መስማት ስለሚገባቸው ሕዝብ ሁሉ፦ “እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?” ብሏል። በቅድስት ሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥም በቀደሙት አበው ስብከተ ወንጌል ተዳርሶ አምልኮተ እግዚአብሔር እየተፈጸመባቸው ቢቆዩም በአንዳንድ ቦታዎች ግን በተለያዩ ጊዜያት በተነሡ አላውያን ተጽዕኖ፣ በመናፍቃን መስፋፋት ምክንያት እንዲሁም በነዚህ ቦታዎች ላይ ቀድሞ የነበረው የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት ተቋርጦ ለብዙ ጊዜ በመቆየቱ ምክንያት ከአምልኮተ እግዚአብሔር ርቀው ቁጥሩ በውል ለማይታወቅ ዘመን ቆይተዋል።

በተለይም በአንዳንድ የምዕራብና ምሥራቅ ኢትዮጵያ አካባቢዎችን ጨምሮ በደቡብ፣ በደቡብ ምዕራብና ደቡብ ምሥራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች አሁንም ከፍተኛ ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ክፍላተ ኢትዮጵያ ናቸው።

ስለዚህም ማኅበሩ ፍኖተ አበውን ሳይለቅ ለስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እነዚህን አካባቢዎች በቅዱስ ወንጌል እያረሠረሰ ይገኛል። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዳዲስ አማኒያንን እና በርካታ በሐሳዊያን መናፍቃን ስተው የነበሩ ተነሣሒያንን ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጅነት መልሷል።

ይህንን ድንቅ ተግባር ለመፈጸም ደግሞ ከየአካባቢው ወጣቶችን መልምሎ በስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት አጽንቶ ወደተወለዱበት አካባቢ ተመልሠው ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ብቻ ሳይሆን በአቅራባያቸው የሚገኙትንና በቋንቋ የሚግባቡትን ሁሉ የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶን አስተምህሮ ያስረዱ ዘንድ በየጊዜው አሰልጥኖ ያሰማራል።

ነቢዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ፦ “ከመ ሠናይ ውስተ አድባር ዘይዜኑ ዜና ሰላም ዘከመ ይዜኑ፤ ዜና ሠናየ እስመ ነገረ እገብራ ለመድኀኒትየ፤ ወእብላ ለጽዮን፦ ይነግሥ ለኪ እግዚአብሔር። - የምስራች የሚናገር፥ ሰላምንም የሚያወራ፥ የመልካምንም ወሬ የምስራች የሚናገር፥ መድኃኒትንም የሚያወራ፥ ጽዮንንም፦ አምላክሽ ነግሦአል፡ የሚል ሰው እግሩ በተራሮች ላይ እጅግ ያማረ ነው።” ኢሳ ፶፪፥ ፯ እንዲል።

ለነዚህ ወገኖቻችን ቅዱስ ወንጌልን ዘወትር በቋንቋቸው የሚሰብካቸውና እውነተኛዋን የጽድቅ መንገድ የሚያሳያቸው መሠረቱ አማናዊት የጽድቅ ተራራ (ሐዋርያዊት ቅድስት ቤተክርስቲያን) የሆነችና አስተምህሮዋን ጠንቅቆ የተረዳ መምህር ያስፈልጋቸዋል። "ናሁ ውስተ አድባር እገሪሆሙ ለሰብአ ዜና ወይዜንዉ ሰላመ፤ - እነሆ፥ የምስራችን የሚያመጣ ሰላምንም የሚያወራ ሰው እግር በተራሮች ላይ ነው!" ናሆም ፩፥ ፲፭ እንዲል።

ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስም እውነተኛ ሐዋርያዊ ሰባኬ ወንጌል ተልኮ መስበክ እንዲገባ ሲገልጽ በሮሜ ፲፥ ፲፭ ላይ፦ “ሠናይ እገሪሆሙ ለእለ ይዜንዉ ሠናየ ዜና - መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ?” ብሏል። ስለሆነም ወገኖቻችን ሰባኪያነ ወንጌል ኖሯቸው ዘወትር ቅዱስ ወንጌልን ይሰሙ ዘንድ በተለያዩ ቋንቋዎች የቅድስት ቤተክርስቲያንን ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ ለመፈጸም የሚላኩ ሰባኪያነ ወንጌልን ስልጠና ይደግፉ ዘንድ ለሁላችሁም ጥሪ አቅርቧል።

→ የአንድ ሰባኬ ወንጌል ስልጠና ሙሉ ወጪ 4000 ብር

→ የቅድስት ቤተክርስቲያንን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት በመደገፍ የግብረ ሐዋርያት ቤተሰብ ይሁኑ።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000195489541
በአቢሲኒያ ባንክ 15376481
በአዋሽ ባንክ 01304024224400
በወጋገን ባንክ 0837534110101
በኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ 1033100028173
ወይም 1033100028297
የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ
☞ @negeretewahido

✥✞✥ ጽሑፉን ሌሎች እንዲያነቡትም Like እና Share ያድርጉ፤ በዚህ መንፈሳዊ Page ላይ የሚተላለፉ መንፈሳዊ ጦማሮች ለእርስዎም ለሌሎችም እንዲደርሱ ፔጁን Like / Follow ሌሎችንም ወደ ፔጃችን ይጋብዙ።

በቴሌግራም ይቀላቀሉን
@waldiba
@waldiba
@waldiba

የዩቲዩብ ቻናላችንን « መኮሬታ Mekoreta Tube »ን በሚከተለው ሊንክ ከፍተው Subscribe & Join ያድርጉ።
https://m.youtube.com/channel/UCUBStsekCniQtATyZDdFqQQ
2.8K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, edited  10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 19:39:30
2.5K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, 16:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 16:50:58 [በሰኔ 8 የጌታችን በምድረ ግብጽ ውሃን ማፍለቅ]
በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ

ሰብአ ሰገልም ጌታን ከእናቱ ጋር አይተው ወድቀው በመስገድ እጅ መንሻውን አቅርበውለት ከሄዱ በኋላ መልአኩ ለዮሴፍ በሕልሙ ተገልጾ “ሕፃኑን ሊገድለው ይፈልገዋልና ተነሣ ሕፃኑንና እናቱንም ይዘኽ ወደ ግብጽ ሽሽ እስክነግርኽም ድረስ በዚያ ተቀመጥ” ባለው ጊዜ ቅዱስ ዮሴፍ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ በሌሊት ወደ ግብጽ ኼዷል፤ ይኽ የቅዱስ ገብርኤል መልእክት የሚያስረዳን እኛም ልክ እንደ አረጋዊዉ ቅዱስ ዮሴፍ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምንና ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስን በኑሯችን ኹሉ በልቡናችን በአንድነት ይዘን እንድንጓዝ ነው (ማቴ 2:1--11)፡፡

ነቢዩ ኢሳይያስ በመንፈሰ እግዚአብሔር እየተቃኘ ቅድስት ድንግል ማርያም የባሕርይ አምላክ ዐማኑኤልን ይዛ ወደ ግብጽ የመሰደዷን ነገር አስቀድሞ ተገልጾለት በምዕ ፲፱፥፩ ላይ፡-
"እነሆ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና እየበረረ ወደ ግብጽ ይመጣል፤ የግብጽም ጣዖታት በፊቱ ይርዳሉ" በማለት ከገነት የተሰደድነውን እኛን ወደ ቀደመ ርስታችን ሊመልሰን እንደመጣ ለማጠየቅ።

ጠላታችን ዲያብሎስን ከሰዎች ልብ አውጥቶ ለመስደድ፤ ክብር ይግባውና ወልደ እግዚአብሔር ልመናዋ ፈጥኖ በሚሰማላት "ደመና መፍጠኒት" በተባለች በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ጀርባ ታዝሎ ወደ ግብጽ የመሰደዱን ነገር አስቀድሞ ገልጾታል፡፡

ይኸውም በቅዱስ ወንጌል እንደተጻፈ ንጉሡ ሄሮድስ ክርስቶስን ለመግደል በፈለገ ጊዜ ቅዱስ ገብርኤል ለአረጋዊዉ ለዮሴፍ በሕልሙ ተገልጾለት "ተንሥእ ወንሣእ ሕፃነ ወእሞ ወጒየይ ውስተ ብሔረ ግብጽ" (ሕፃኑንና እናቱን ይዘኽ ወደ ግብጽ ሽሽ) ባለው ጊዜ ይኽ ኢሳይያስ የተናገረው ትንቢት ሊፈጸም ምልጃዋ ፈጥኖ በሚደርስ "ደመና መፍጠኒት" በተባለች በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ጀርባ ታዝሎ ወደ ግብጽ በኼደ ጊዜ የግብጽ ጣዖታት ኹሉ እየተሰባበሩ ሲወድቁ፤ በነርሱ ዐድረው ያስቱ የነበሩ አጋንንት ኹሉ ሸሽተዋል፤ በመኾኑም በዚኽ የነገረ ማርያም አስተምህሮ እመቤታችን "ደመና መፍጠኒት" ወይም "ደመና ኢሳይያስ" ተብላ ተጠርታለች፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በስደቷ ወቅት ልጇን እንዳይገድሉባት በረሓ በረሓውን እንኺድ ስትል ዮሴፍና ሰሎሜ ለልመና እንዲመቻቸው ከተማ ከተማውን መኼድ ፈለጉ ያን ጊዜ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል ተገልጸው ዮሴፍን “እመቤትኽ አይደለች ያለችኽን አትሰማም” ብለውታል።

ጌታም “ኢትትናገራ ለእምየ” (በኾነ ባልኾነው እናቴን አትናገራት!) ብሎታል፤ ወዲያው ከከተማ አጠገብ ስትደርስ ዮሴፍና ሰሎሜን ጓዝ አስጠብቃ ርሷ ጌታን ዐዝላ እኽል ውሃ ለመጠየቅ ከተማ ብትገባ ሰይጣን በሰዎቹ ልብ በማደር የሰውን ልቡና ኹሉ አጽንቶባት የሚዘከራት አጥታ በሐዘን ተመልሳለች፡፡

ሊቁም ስለዚኽ ነገር የስደቷን ነገር በሚያነሣው በሰቈቃወ ድንግል መጽሐፉ ላይ በሐዘን ኾኖ፡-

“ተንሥዒ ወንዒ ሌዋዊት ሐና
ትጼውዓኪ ወለትኪ ከመ ትርአዪ ሐዘና
እምርስትኪ ወጽአት ወተሰደት በድክትምና
ትበኪ እምዋዕየ ሐጋይ ኃጢኣ በፍና
ሕፍነ ማይ ዘታሰትዮ ለጽሙዕ ሕጻና”

(ከሌዊ ወገን የኾንሽ ሐና! ልጅሽ ከቦታሽ ወጥታ በድኅነት ተሰድዳ ከበጋ ሙቀት የተነሣ ለተጠማ ልጇ የምታጠጣው ዕፍኝ ውሃን በመንገድ ዐጥታ ታለቅሳለችና ዐዘኗን ታይላት ዘንድ ልጅሽ ትጠራሻለችና ፈጥነሽ ነዪ) በማለት ገልጾታል፡፡

ከዚያም ዮሴፍና ሰሎሜ ወዳሉበት ብትመለስ አረጋዊ ዮሴፍና ሰሎሜ በመንገድ ስለደከሙ እንቅልፍ ወስዷቸው ሰብአ ሰገል የገበሩለትን የወርቅ ጫማ ለሌቦች አስወስደው ቆይዋት፤ ርሷም “ከተማ ቢገቡ ልጅ የሚሸነግሉበት ትንሽ ቊራሽ ጥሩ ውሃ ማጣት እዚኽ ቢመጡ የወርቅ ጫማ ማጥፋት” ምርር ብላ አልቅሳለች ዕንባዋም በፊቱ ወርዷል፡፡

ሊቁም ይኽነን ይዞ በሰቈወ ድንግል መጽሐፉ ላይ ፡-
“መለኮት ዕጓላ ሶበ ጸምዐ ከመ ደቂቅ
ዘይሰፍሮ በኅፍኑ ለማየ ባሕር ዕሙቅ
በከየት ወትቤ ማርያም ማዕነቅ
አልቦ እምሰብአ ሀገር ዘየአምራ ለጽድቅ
ሶበ ሰአልክዎሙ ማየ ኢወሀቡኒ በሕቅ
ወአኅጐልኩ ለወልድየ አሣዕኖ ዘወርቅ”

(ጥልቅ የኾነ የባሕር ውሃን በእጁ የሚሠፍረውና የማይመረመር መለኮት የተባለ የባሕርይ አምላክ ልጇ በተጠማ ጊዜ ከዚች ሀገር ሰዎች ቸርነትን የሚያውቃት የለም፤ ውሃን በእጅጉ ለመንኋቸው አልሰጡኝም የልጄ የወርቅ ጫማውን አስጠፋኊ እያለች ዋኖስ ማርያም አለቀሰች) በማለት መሪር ዕንባዋን ጽፏል፡፡

ልጇም ዕንባዋን አይቶ ሰኔ 8 ቀን ከማር ከወተት ይልቅ የምትጣፍጥ ውሃ አፍልቆ አጠጥቷቸዋል፤ በዚኽም ውሃ የተጠመቀውን ከሕመሙ እንዲፈወስ ቃል ኪዳን ሲሰጣት፤ ሰይጣን ልቡናቸውን ላጸናባቸው ለዚያች ሀገር ሰዎች ግን መሪር እንደምትኾንባቸው ነግሯታል፡፡ ይኽችም ደገኛ ተአምር የተሠራችባት ሰኔ 8 ከቅድስት ድንግል ማርያም 33ቱ በዓላቷ እንዳንዱ በመቈጠር በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዓለም እስኪያልፍ ድረስ ትታሰባለች፡፡

ሊቁም በሰቈቃወ ድንግል ይኽነን ይዞ፡-
“ሰሚኦ ሕፃን ለእሙ ገዐራ
ባረከ ኰኲሐ ወአንቅዐ ማየ እምታሕተ እግራ
ወእምኔሁ ለጽምዐ ትስተይ አመራ
ከመ ኢይስተይዋ እምሰብአ ሀገር ለይእቲ ማይ አምረራ
ወለርኁቃን ፈውሰ ወጥዕምተ ገብራ”

(የእናቱን ጭንቅ ልጇ ሰምቶ ዐለቱን ባርኮ ውሃን ከእግሯ በታች አፈለቀ፤ ከዚኹም ውሃ ለጥማቷ ትጠጣ ዘንድ አመለከታት የዚች ሀገር ሰዎችም ይቺን ውሃ እንዳይጠጧት መራራ ለሩቅ ሰዎች ግን የጣፈጠች የፈውስ ውሃ አደረጋት) በማለት የጌታን ተአምር መስክሯል፡፡

ሊቁ አባ ጊዮርጊስም ይኽነን ታሪክ ይዞ በሰዓታቱ ላይ
“ወጽአት በፍርሃት እምሀገረ ዳዊት ዘይሁዳ
በብሥራተ መልአክ እንግዳ
ኢረከበት ማየ በፍኖት ዘታሰትዮ ለወልዳ”

(በእንግዳ መልአክ ብሥራት የይሁዳ ክፍል ከምትኾን ከዳዊት ከተማ ከይሁዳ በፍርሀት በወጣች ጊዜ ለልጇ የምታጠጣው ውሃ በመንገድ አላገኘችም) በማለት ገልጾታል፡፡

ድንግል ሆይ የሕይወት ውሃ ከተባለ ልጅሽ ምሕረትን ለምኚልን፡፡ አሜን!
☞ @negeretewahido

እጅግ ታሪካዊ ወደሆነው ምሥጢራዊው መንዝ
#እመጓ_ደብረ_ቆጵሮስ_ቅዱስ_ዑራኤል_ገዳም
የሚኖረን ፫ኛው ዙር መንፈሳዊ ጉዞ እንደተጠበቀ ነው።
* መነሻ ዐርብ ሰኔ 10
* መመለሻ እሑድ ሰኔ 12
* የጉዞ ዋጋ ቦታው ላይ ምግብና ማረፊያ ጨምሮ 1000 ብር

★ በማኅበራችን የጉዞ መርሐ ግብራት መሳተፍ ከፈለጉ ሳያመነቱ ይደውሉልንና አብረን እንጓዝ!!! ውስን ወንበሮች ብቻ ስለቀሩን ይህንን ቅዱስ ቦታ ለመሳለም የምትሹ ያልተመዘገባችሁ የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ልጆች ሁሉ ቀድማችሁ ደውሉልንና አብረን በረከት እናግኝ! ለበለጠ መረጃ፦
→ 0911289877
→ 0901070707
#ማኅበረ_ቅዱስ_ፊልጶስ_ወአቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ

✥✞✥ ጽሑፉን ሌሎች እንዲያነቡትም Like እና Share ያድርጉ፤ በዚህ መንፈሳዊ Page ላይ የሚተላለፉ መንፈሳዊ ጦማሮች ለእርስዎም ለሌሎችም እንዲደርሱ ፔጁን Like / Follow ሌሎችንም ወደ ፔጃችን ይጋብዙ።

በቴሌግራም ይቀላቀሉን
@waldiba
@waldiba
@waldiba

የዩቲዩብ ቻናላችንን « መኮሬታ Mekoreta Tube »ን በሚከተለው ሊንክ ከፍተው Subscribe & Join ያድርጉ።
https://m.youtube.com/channel/UCUBStsekCniQtATyZDdFqQQ
2.3K viewsአንተነህ ውብሸት, edited  13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 11:37:56 ፫ኛ ዙር መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ምሥጢራዊው መንዝ
#እመጓ_ደብረ_ቆጵሮስ_ቅዱስ_ዑራኤል_ገዳም
*** መነሻ ዐርብ ሰኔ 10
*** መመለሻ እሑድ ሰኔ 12
* የጉዞ ዋጋ ቦታው ላይ ምግብና ማረፊያ ጨምሮ 1000 ብር
በጉዞው ለመሳተፍ፦ 0911289877 / 0901070707

★ እመቤታችን ከተወዳጅ ልጇ ጋር አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍንና ቅድስት ሰሎሜን አስከትላ በተሰደደች ጊዜ ያረፈችበትና በኪደተ እግራቸው የባረኩት ቅዱስ ቦታ፣

★ ዳግመኛም ጌታችን ከትንሣኤው እስከ ዕርገቱ ድረስ ያለውን ፵ውን ቀን የተቀመጠበት ምስጢራዊ በዓቱ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፣

★ ግማደ መስቀሉ፣ ከመስቀሉ ጋር የመጡ ዐጽመ ቅዱሳንና በርካታ ንዋያተ ቅድሳት ለ14 ቀናት ያረፉበት፣

★ መስቀሉን ይዘው ከግብጽ ወደ ኢትዮጵያ ያመጡት ፲ሩ ቅዱሳን የጸለዩበት፣

★ ለሊቀ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል አስራት ተደርጎ የተሰጠው ልዩ የቃል ኪዳን ቦታ፣

★ ደመ ክርስቶስ የተቀዳበት ተአምረኛው የብርሃን ጽዋ በአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም ላይ ተንጠፍጥፎ በሰከላ ግሽ ዓባይ ገዳም ላይ ከተለቃለቀ በኋላ በክብር የተቀመጠበት ድንቅ ቦታ፣

★ ዳግመኛም በምሴተ ሐሙስ በቤተ አላዕዛር በደርቡ ላይ በቀረበው የመጨረሻው የጌታ ራት ጌታችን፦ "ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ፦ ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።" ብሎ ምስጢረ ቁርባንን የመሠረተበት (በቅዱሳት መለኮታዊ እጆቹ ይዞ ወይኑን ወደ አማናዊ ደሙ የለወጠበት) ቅዱስ ጽዋ (የኪዳኑ ቅርስ) የሚገኝበት ድንቅ ገዳም፤ ማቴ ፴፮፥ ፲፫→

★ ራሱ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በልሳነ አረማይክ የሰየማት ታሪካዊ ቦታ፣

★ የእመቤታችን ቀሚስ የሚገኝበት ታሪካዊ ገዳም፣

★ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህንን ቅዱስ ቦታ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ 6000 ዕሳታዊያን መላእክት እንደሚጠብቁት ለእመቤታችን ቃል የገባበት ክቡር ገዳም፣

★ ዳግመኛም ጌታችን፦ "አስቀድሜ በታላቁ ዐምደ ወርቅ ስሙን ያልጻፍኩትን ይህንን ቅዱስ ቦታ አላስረግጠውም..." ብሎ ለቅዱስ ዑራኤል ቃል የገባበት ድንቅ ገዳም፣

★ ዳግመኛም ጌታችን ለቅዱስ ዑራኤል፦ "ይህንን ደጅ የረገጠና በዚህ ቅዱስ ቦታ ከበቀለው ማንኛውም ነገር የቀመሰ ሁሉ የቅዱስ ዑራኤል ስም በግንባሩ ላይ ይጻፍበታል፤ ባረፈም ጊዜ ስምህ ዋስ ጠበቃ ሆኖት ከገሃነም ሞት ይድናል" ብሎ ክቡር ቃል ኪዳን የሰጠበት ግሩም ቦታ፣

★ ለሊቀ ሰማእታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅድስት ሐገራችን ኢትዮጵያን አስራት ተደርጋ የተሰጠችበት ድንቅ ገዳም፣
☞ @negeretewahido

★ ቀጣይ ጉዞዎቻችን፦
፩) #ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳምና_ተአምረኛው_በርሚል_ጊዮርጊስ
→ ከባህርዳር እስከ ጎርጎራ የሚገኙ የጣና ገዳማትን ጨምሮ በርካታ ጥንታዊ ገዳማትና አድባራትን የምንሳለምበት እና ታሪካዊ ቦታዎችን የምንጎበኝበት የ9 ቀናት ልዩ የንግሥ ጉዞ ነው።
→ በጉዟችን በቀን 3 ጊዜ በመዓዛ ገነት የሚታጠነውንና እመቤታችን በየቀኑ በጣና ቂርቆስ ገዳም እየተገለጸች የምትባርከውን ባለ ልብ ቅርጹን የጣና ሐይቅን ከባህርዳር እስከ ጎርጎራ በዘመናዊ ጀልባ እየቀዘፍን በቅዱሱ ሐይቅ ላይ የሚገኙ በርካታ ቅዱሳት መካናትን እንሳለማለን።
→ ጊዜያችንን በአግባቡ ከተጠቀምን ደግሞ በሕይወታችሁ የማትረሱትና ግሩም በረከት የምታገኙበት አንድ ተአምረኛ ገዳም ሰርፕራይዝ ይኖራል።
→ መነሻ፦ ሐምሌ 3 ጠዋት 11:30 መመለሻ፦ ሐምሌ 13
→ የጉዞ ዋጋ 4000 ብር

፪) ቁሉቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ከሐምሌ 16- 20
☞ @negeretewahido

#የምዝገባ_ቦታዎች፦
1) ቀጨኔ መድኃኔዓለም አካባቢ፦፦
ማትያስ የመኪና ዕቃ መሸጫ፣
ማርሶሊ ፎቶ ቤት፣

2) አራዳ ጊዮርጊስ አካባቢ
ገኒ የወንዶች ፀጉር ቤት
መሲ ሕትመትና ማስታወቂያ

3) ባላችሁበት አካባቢ ለመመዝገብ (ትኬት ለመቁረጥ)
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክና በአዋሽ ባንክ ሁሉም ቅርንጫፎች በካሽ ወይም በሞባይል ባንኪንግ በሚከተሉት የመምህር አንተነህ ውብሸት አካውንቶች አስገብታችሁ ደረሰኙን የጉዞው ቀን ይዞ መምጣት ወይንም Screenshot አድርጋችሁ በቴሌግራም ልትልኩልን ትችላላችሁ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000099794899
አቢሲኒያ ባንክ 73439825
አዋሽ ባንክ 01320104564900

#ለመንፈሳዊ_ጉዞዎቹ_የሚያስፈልጉ_ነገሮች፦ የቀበሌ መታወቂያ (ፓስፖርት)፣ ለብርድ የሚሆን ወፍራም ጃኬት፣ ለእግር መንገድ የሚሆኑና ተቀያሪ ጫማዎች፣ ሌሊት የሚለበስ ስሊፒንግ ባግ / ወፍራም ጋቢ/ ወፍራም ወይባ/ ፎጣ/ ቀለል ያለ ብርድ ልብስ/፣ ክርስቲያናዊ አለባበስ፣ ጃንጥላ፣ የእጅ ባትሪ፣ ሰዓት አክባሪነት፣ ታጋሽነት፣ የወጡበትን መንፈሳዊ ዓለማ ለማሳካት በጋራ መትጋት...
☞ @negeretewahido

★ በማኅበራችን የጉዞ መርሐ ግብራት መሳተፍ ከፈለጉ ሳያመነቱ ይደውሉልንና አብረን እንጓዝ!!! ውስን ወንበሮች ብቻ ስለቀሩን ይህንን ቅዱስ ቦታ ለመሳለም የምትሹ ያልተመዘገባችሁ የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ልጆች ሁሉ ቀድማችሁ ደውሉልንና አብረን በረከት እናግኝ! ለበለጠ መረጃ፦
→ 0911289877
→ 0901070707
#ማኅበረ_ቅዱስ_ፊልጶስ_ወአቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ

✥✞✥ ጽሑፉን ሌሎች እንዲያነቡትም Like እና Share ያድርጉ፤ በዚህ መንፈሳዊ Page ላይ የሚተላለፉ መንፈሳዊ ጦማሮች ለእርስዎም ለሌሎችም እንዲደርሱ ፔጁን Like / Follow ሌሎችንም ወደ ፔጃችን ይጋብዙ።

በቴሌግራም ይቀላቀሉን
@waldiba
@waldiba
@waldiba

የዩቲዩብ ቻናላችንን « መኮሬታ Mekoreta Tube »ን በሚከተለው ሊንክ ከፍተው Subscribe & Join ያድርጉ።
https://m.youtube.com/channel/UCUBStsekCniQtATyZDdFqQQ
2.5K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, 08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-08 16:29:56
2.3K viewsእልመስጦአግያ ዘሐዋርያት, 13:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ