የአማራ ፋኖ በጎጃም አገዉ ምድር ክፍለ ጦር ዘንገና ብርጌድ ቲሊሊ
100ተራሮች ዘመቻና ዉጤቱ
ይህ ብርጌድ ከሰሞኑ ታምር ሲሰራ፤ እጅግ አስደሳች ድሎችን የተጎናፀፈበትና ለወገን እፎይታን ሲሰጥ ነዉ የሰነበተዉ።
100 ተራሮች በተጀመረ የመጀመሪያው ቀን ካለበት ማዘዣ ጣቢያ ተንቀሳቅሶ ወደ ማንኩሳ ከተማ በመዉረድ ከሌሎች ቀጠና ጓዶቹ ጋ ተናቦ አስጨናቂ ኦፕሬሽን ሰርቶ ማንኩሳ ከተማን ሙሉ በሙሉ ከጠላት ነፃ አዉጥቷል።
በዚህ ዘመቻ የጠላት ጦር ብትንትኑ ወጥቶ አስክሬን ሳያነሳ፤ሃብት ንብረቱን ሳይሸክፍ የተረፈው ጥሎ እንዲፈረጥጥ ተደርጓል።
እንግዲህ ይህ የቲሊሊ ዘንገና ብርጌድ ፋኖ ማንኩሳ ከተማን ከጠላት ነፃ አድርጎ በሁለተኛው ቀን ለወገን አስረክቦ ትልቅ አላማና ሞራል ሰንቆ ወደ ቲሊሊ እየገሰገሰ ባለበት ሰሃት ቲሊሊ ከተማ የነበረዉ የአራዊት ቡድን መረጃዉ ቀድሞ ደርሶት ኖሮ የኖረበትን ካምፕ ለቆ ወደ ቡሬ ይፈረጥጣል።
አሁንም የልቡ ያልደረሰዉ ነበልባል ፋኖ ከስሜነህ ደስታ እንጅባራ ብርጌድ(ሳትሜዎቹ) ጋር ሲዶልት፤ ሲመክር ከዋለ በኋላ የተዶለተበት ጠላት አሁንም የነበረበትን የሰከላ ካምፕ በሌሊት ለቆ ወደ ቲሊሊ መጓዝ ይጀምራል። እንግዲህ ነገሩ የተጀመረ አሁን ነዉ ቲሊሊዎችና ሳትሜዎችም ከያሉበት ተጠራርተዉ በሌሊት እየበረሩ ቦታ ቦታ ይዘዉ ጠበቁት። ጠላትም እየተንቀጠቀጠ ካለንበት ቦታ ሰተት እያለ ሲነጋ ደረሰ። በሶስት አቅጣጫ ተከበበ። 10ደቂቃ ባልሞላ ወጊያ አንዱን ድሽቃ ተቀበልናቸዉ፤ በራሱ ድሽቃና ተተኳሽ እናባክናቸዉ ጀመር፤ ወደ ፊት ይፈረጥጡ ጀመር። ነገር ግን በኋላ ሰከላዎቹ ከበቡ፣ በፊት ቲሊሊዎች፣ በግራና በቀኝ ሳትሜዎቹና አጉቶቹ ይለበልቡት ጀመር በዚህ ሰሃት ነዉ ነገሩ የከረረ። እሬሳ በሬሳ ጩኸት ተበጩኸት ዋይታ በረከተ። የጨነቀዉ ጠላት እግሬ አዉጭኝ እሩጫ በየ አቅጣጫዉ ሆነ፤ እድለኛዉ እጅ ሰጠ።ካሰበበት ሊደርስ ያሰበዉ ጠላት ለራት ሳይሆን ቁርስና ምሳ ብቻ ሁኖ ቀረ፤ ከ500_600 የሚሆነዉ ጠላት ዳዋ በላዉ።
በዚህም ዘመቻ ዘንገና ብርጌድ በግሉ፦
32 ምርኮኛ፣
3 ብሬን
45 ጥቁር ክላሽ
ቁጥሩ በዉል ያልታወቀ ተተኳሽ አግኝቷል።
እንደ አጠቃላይ በአገዉ ምድር ክፍለ ጦር
2 ድሽቃ፣
ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ
5 መኪና ከነ ሙሉ የወታደር ሀብት ንብረት
7 ብሬን
4 ስናይፐር
ከ400 በላይ ክላሽ
ብዙ መገናኛ ሬድዮ
ተቆጥሮ የማያልቅ ተተኳሽና ትጥቅ ተማርኳል።
አስደናቂ ጀብድ የተፈፀመበት ሰከላ የኖረዉ ባንዳና የጠላት ሀይል ሙሉ በሙሉ የተበተነበት የ100 ተራሮች ዘመቻ ሁኖ ተጠናቋል
ፋኖ አለበል አወቀ የዘንገና ብርጌድ የህዝብ ግንኘነት