Get Mystery Box with random crypto!

Tiriyachen | ጥሪያችን

የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን
የሰርጥ አድራሻ: @tiriyachen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.91K

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 20

2022-11-09 18:44:12 https://vm.tiktok.com/ZMFfxChfT/
 
ቲክቶክ ቻነላችን ላይ አዲስ ቪዲዬ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
262 views15:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-06 21:22:08 የጀነት ዛፍ በቁርአን እና በባይብል

“ጀናህ” جَنَّة የሚለው ቃል “ጀነ” جَنَّ ማለትም “ተሰወረ” ወይም “ተደበቀ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን “ድብቅ” ወይም “ስውር” ማለት ነው፥ በጀነት ውስጥ ያለው ለሙሥሊሞች የተደበቀላቸውን ፀጋ ደግሞ ማንኛይቱም ነፍስ ስለማያውቅ ድብቅ እና ስውር ነው። በሐዲሰል ቁድሢይ ላይ የተዘጋጀው የጀነት ጸጋ ዓይን ዓይቶት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ ልብ አስቦት የማያውቅ መሆኑ ተገልጿል፦

ይሠሩትም በነበሩት ለመመንዳት ከዓይኖች መርጊያ ለእነርሱ የተደበቀላቸውን ጸጋ ማንኛይቱም ነፍስ አታውቅም፡፡
ሱራ አስ ሳጂድ 32፥17

አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ ነብዩ እንዲህ ብለው አሉ፦ “አላህም እንዲህ አለ፦ እኔ ለደጋግ ባሮቼ ዓይን ዓይቶት የማያውቅ፣ ጆሮ ሰምቶት የማያውቅ እና በሰው ልቦና ውል ብሎ የማያውቅ ጸጋን አዘጋጅቻለው”።
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 123

ስለዚህ በጀነት ውስጥ ያሉትን አሏህ ለባሮቹ ያዘጋጃቸው ፀጋዎች ዓይን ዓይቶት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ ልብ አስቦት የማያውቅ ከሆነ ጀነት ውስጥ ያለው ሙዝ፣ ዘንባባ፣ ወይን፣ ተምር እንዲሁ ዛፍ ከዱንያው ውስጥ ካለው ነገር ጋር የስም መመሳሰል እንጂ ቅርጽና ይዘቱ አሊያም ጥፍጥናውና ጣዕሙ አንድ አይደለም፦

ዛፎችዋም በእነርሱ ላይ የቀረበች እና ፍሬዎችዋም ለለቃሚዎች መግገራትን የተገራች ስትኾን ገነትን መነዳቸው፡፡
ሱራ አል ኢንሳን 76፥14

አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም እንዲህ አሉ፦ “በጀናህ ውስጥ በጥላ ሥር ፈረሰኛ መቶ ዓመት የሚምታስጓዝ ዛፍ አለች”።
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 53 ሐዲስ 7

ጊዜ የሚለካው በሰከንድ፣ በደቂቃ፣ በሰዓት፣ በቀን፣ በወር፣ በዓመት ሲሆን በተመሳሳይ ከሜትር ቁጥጥር ውጪ ያለ ርዝመት የሚለካው በዓመት ነው፥ በፈረሰኛ መቶ ዓመት መገለጹ በራሱ ጀናህ ምን ያክል ሰፊ እንደሆነች በቀላሉ መረዳት ይቻላል። ቀለብ እንጂ ቀልብ የሌላቸው ሚሽነሪዎች በጀናህ ውስጥ ዛፍ መኖሩ ለመሳቅ እና ለመሳለቅ ሲቃታቸው ዓይተን ነበር፥ እንዚህ ዘንጋታዎች እየተጎማለሉ እና ዘንፈል እያሉ ቁርኣን እና ሐዲስ ውስጥ እንደገቡ እኛም እንዲማሩበት በጨዋ ደንብ እና ሥርዓት ከባይብል በጀነት ውስጥ ዛፍ እንዳለ ጠቅሰንና አጣቅሰን እናቀርባለን፦

በእግዚአብሔርም ገነት በዔድን የነበሩ “ዛፎች” ሁሉ ቀኑበት።
ሕዝቅኤል 31፥ 9

ድል ለነሣው በእግዚአብሔር ገነት ካለው ከሕይወት “ዛፍ” እንዲበላ እሰጠዋለሁ።
ራእይ 2፥7

በወንዙም ወዲያና ወዲህ በየወሩ እያፈራ አሥራ ሁለት ፍሬ የሚሰጥ የሕይወት “ዛፍ” ነበረ፥ የዛፉም ቅጠሎች ለሕዝብ መፈወሻ ነበሩ።
ራእይ 22፥2

እነዚህ ሦስት አናቅጽ ላይ በገነት ውስጥ ዛፎች እንዳሉ አስረግጠውና ረግጠው ያስረዳሉ፥ “የሕይወት ዛፍ” ማለት አዳም እና ሔዋን በገነት እያሉ እንዲበሉት የበቀለ ዛፍ ነው፦

በገነትም መካከል “የሕይወትን ዛፍ”፥ መልካምንና ክፉን የሚያስታውቀውንም ዛፍ አበቀለ።
ዘፍጥረት 2፥9

እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፦ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ፤
ዘፍጥረት 2፥16

እሥልምና እንዲጠፋ ሙሥሊም እንዲገፋ ቀን ከሌሊት የሚዋትሩ እነዚህ እብሪተኞች እና ዳተኞች የሚሰበሰቡበት አዳራሽ ክበብ ይሁን ክለብ ለይተው ሳያውቁ እነዚህ አናቅጽ ያነቡአቸዋል ብለን አናስብም፥ ሚሽነሪዎች ሆይ! መቅኖ አጥታችሁ መቀመቅ ከመውረዳችሁ በፊት ጨርቄን እና ማቄን ሳትሉ ወደ ዱኑል ኢሥላም እንድትመጡ ጥሪአችን ነው። አምላካችን አሏህ ለኢሥላም ጸር እና አጽራር ከመሆን አርነት አውጥቶ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። 

ለተጨማሪ ንባብ ድረገጻችንን ይጎብኙ።
https://tiriyachen.org/?p=4066
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen 
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
336 views18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-06 21:22:03
296 views18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-06 19:03:52 https://vm.tiktok.com/ZMFy6Y3Fq/
 
ቲክቶክ ቻነላችን ላይ አዲስ ቪዲዬ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
358 views16:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 21:09:26 https://vm.tiktok.com/ZMFD5Uawv/
 
ቲክቶክ ቻነላችን ላይ አዲስ ቪዲዬ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
150 views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 22:21:58 ቡሄ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና። وَمَآ ءَاتَىٰكُمُ ٱلرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَىٰكُمْ عَنْهُ فَٱنتَهُوا۟ ۚ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ ۖ إِنَّ ٱللَّهَ شَدِيدُ ٱلْعِقَابِ

መጣና መጣና
ደጅ ልንጥና፤
መጣና ባመቱ
እንዴት ሰነበቱ፣
ክፈት በለዉ በሩን
የጌታዬን፣
ክፈት በለዉ ተነሳ
ያንን አንበሳ፣
መጣሁኝ በዝና
ተዉ ስጠኝ ምዘዝና።
እየተባለ ሆያ ሆዬ በልጅነት ያለ ዕውቀት ሙሥሊሙ ከክርስቲያኑ ጋር ተደባልቆ የክርስቲያን ሠው ሥራሽ በዓል ሲያከብር አድጓል። "ቡሄ" ማለት "ገላጣ" "የተገለጠ" ማለት ነው፥ በአገራችን የክረምቱ አፈና ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታየውም በዚህ በዓል አካባቢ ስለሆነ ይህ ዕለት "ቡሄ" ተባለ። ኢየሱስ ሦስቱን ተከታዮች ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ አወጣቸው፦
ማቴዎስ 17፥1 *ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው*።

ይህ ተራራ የትኛው ተራራ እንደሆነ በባይብል አልተጠቀሰም። አንዳንድ ምሁራን አርሞንኤም ነው ይላሉ፥ የእኛዎቹ ታቦር ነው ይላሉ። "ደብር" ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን "ተራራ" ማለት ነው፥ የደብር ብዙ ቁጥር "አድባር" ሲሆን "ተራሮች" ማለት ነው። "ደብረ-ታቦር" ማለት "የታቦር ተራራ" ማለት ነው፥ ይህ ቡሄ በዓል ደብረ-ታቦር ይባላል።
በባይብል የተራራው ስም የለም፣ ይህ እለት ነሃሴ 13 ነው የሚል የለም፣ ይህንን ቀን አክብሩ የሚል የለም፣ በዚህ ቀን ዳንኪራ ሆያ ሆዬ አድርጉ የሚል የለም። ይህ ሁሉ ሰው ሠራሽ ሕግ ነው። በገጠርም ሆነ በየከተማው ልጆች ጅራፋቸውን ገምደው ሲያጮሁ ይሰነብታሉ። እናቶችም ለበዓሉ ዝግጅት ስንዴ ሲለቅሙ፣ ሲፈትጉ፣ ሲፈጩ ይሰነብታሉ። ቡሄ ለሚሉ ልጆች ሙልሙል ዳቦ በመስጠት እና ችቦ በማብራት በዓሉን ያከብራሉ። ይህ ሁሉ ከንቱ እዚሁ የሚቀር ምድራዊ ነገር ነው። ይህንን የክርስትና ሰው ሰራሽ በዓል ሙሥሊሙ ባለማወቅ ሲያከብረው ኖሯል። ይህ ስህተት ነው። ነቢያችን”ﷺ” የነገሩን ዓመታዊ በዓል ሁለት ብቻና ብቻ ናቸው፤ እነርሱም፦ ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓ ናቸው፦
ሡነን አቢ ዳዉድ : መጽሐፍ 2, ሐዲስ 745
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፤ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” መዲና ሲገቡ የመዲና ሠዎች የሚደሰቱባቸው ሁለት በዓላት እንዳሏቸው አወቁ። እርሳቸውም እነዚህ ሁለቱ ቀናት ምንድን ናቸው? በማለት ጠየቁ፤ ሰዎችም በጃሂሊያ ጊዜ እንጫወትባቸው የነበሩ በዓላት ናቸው አሏቸው። የአላህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ “አላህ ከእነርሱ የተሻሉ ሁለት ዒዶችን ሠጥቷችኋል፤ እነርሱም፦ ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓን። አሏቸው። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ قَدِمَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم الْمَدِينَةَ وَلَهُمْ يَوْمَانِ يَلْعَبُونَ فِيهِمَا فَقَالَ ‏”‏ مَا هَذَانِ الْيَوْمَانِ ‏”‏ ‏.‏ قَالُوا كُنَّا نَلْعَبُ فِيهِمَا فِي الْجَاهِلِيَّةِ ‏.‏ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ إِنَّ اللَّهَ قَدْ أَبْدَلَكُمْ بِهِمَا خَيْرًا مِنْهُمَا يَوْمَ الأَضْحَى وَيَوْمَ الْفِطْرِ ‏”‏ ‏.‏
ጃሚዒ አት-ተርሚዲህ : መጽሐፍ 8, ሐዲስ 121
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ዒዱል ፈጥር ሰዎች ጾም የሚፈቱበት ነው፤ ዒዱል አደሐ ደግሞ መስዋዕት የሚያቀርቡበት ቀን ነው። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْفِطْرُ يَوْمَ يُفْطِرُ النَّاسُ وَالأَضْحَى يَوْمَ يُضَحِّي النَّاسُ ‏”‏
ጃሚዒ አት-ተርሚዲህ : መጽሐፍ 8, ሐዲስ 91
አቡ ሰዒደል ኹድሪይ እንደተረከው፥ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” በሁለቱ በአል በኢደል አደሐ እና ኢደል ፈጥር መጾም ከልክለዋል። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ، قَالَ نَهَى رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم عَنْ صِيَامَيْنِ يَوْمِ الأَضْحَى وَيَوْمِ الْفِطْرِ ‏.

ቡሄ የአገር ባህል ይመስለን ነበር፥ ቅሉ ግን እንደዛ አይደለም። ይህንን በዓል መልእክተኛው ያልሰጡን ዕቡይ ተግዳሮት መሆኑን ዐውቀን መሳተፍ የለብንም። የታሪክ ምፀት ከዐሊሞቻችን ለሚቀጥለው ትውልድ የሚሆን ሰፊ ምዕላድ ትተን መሄድ ግድ ይለናል፥ ይህን ለማድረግ አስረግጦ እና ረግጦ መረዳትና ማስረዳት ይጠበቅብናል። ያኔ የኢሥላም ልዕልና ለካፊሩን የልብ ፍልጠት፣ የራስ ምታት፣ የሆድ ቁርጠት፣ የጎን ውጋት እና የእግር ቁርጥማት ኢንሻላህ ይሆናል።

ለተጨማሪ ንባብ ድረገጻችንን ይጎብኙ።
https://tiriyachen.org/?p=4050
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen 
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
170 views19:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 22:21:40
162 views19:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 12:34:18 21፥19 በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉም የእርሱ ነው፡፡ *”እርሱ ዘንድ ያሉትም መላእክት እርሱን ከመገዛት አይኮሩም”*፡፡ አይሰለቹምም፡፡ وَلَهُ مَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ وَمَنْ عِندَهُ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِ وَلَا يَسْتَحْسِرُونَ
66፥6 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነፍሶቻችሁንና ቤተሰቦቻችሁን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ደንጋዮች ከኾነች እሳት ጠብቁ፡፡ በእርሷ ላይ ጨካኞች፣ ኀይለኞች የኾኑ መላእክት አሉ፡፡ *”አላህ ያዘዛቸውን ነገር በመጣስ አያምጹም፤ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ”*፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا قُوا أَنفُسَكُمْ وَأَهْلِيكُمْ نَارًا وَقُودُهَا النَّاسُ وَالْحِجَارَةُ عَلَيْهَا مَلَائِكَةٌ غِلَاظٌ شِدَادٌ لَّا يَعْصُونَ اللَّهَ مَا أَمَرَهُمْ وَيَفْعَلُونَ مَا يُؤْمَرُونَ

መላእክት አላህ ያዘዛቸውን ነገር በመጣስ አያምጹም፤ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ። እዚህ ድረስ ከተግባባን የሚቀጥለውን አንቀጽ ጥልልና ጥንፍፍ ባለ መልኩ እንይ። በባቢሎት በሚገኙት በሀሩትና በማሩት ላይ የተወረደው የሲሕር ትምህርት ሰዎችን እንዴት እንደሚጎዳ ማስጠንቀቂያ ሆኖ ነው። ነገር ግን ሰይጣናትም በሱለይማን ዘመነ መንግስት ሰዎችን የሚያስተምሩት ለአሉታዊ ነገር ነበር፦
2፥102 *”ሰይጣናትም በሱለይማን ዘመነ መንግስት የሚያነቡትን ተከተሉ፡፡ ሱለይማንም አልካደም፤ ግን ሰይጣናት ሰዎችን ድግምትን የሚያስተምሩ ሲኾኑ ካዱ፡፡ ያንንም በባቢል በሁለቱ መላእክት በሃሩት እና ማሩት ላይ የተወረደውን ነገር ያስተምሩዋቸዋል፡፡ «እኛ መፈተኛ ነንና አትካድ» እስከሚሉም ድረስ አንድንም አያስተምሩም፡፡ ከእነሱም በሰውየውና በሚስቱ መካከል በእርሱ የሚለዩበትን ነገር ይማራሉ”*፡፡ وَٱتَّبَعُوا۟ مَا تَتْلُوا۟ ٱلشَّيَٰطِينُ عَلَىٰ مُلْكِ سُلَيْمَٰنَ ۖ وَمَا كَفَرَ سُلَيْمَٰنُ وَلَٰكِنَّ ٱلشَّيَٰطِينَ كَفَرُوا۟ يُعَلِّمُونَ ٱلنَّاسَ ٱلسِّحْرَ وَمَآ أُنزِلَ عَلَى ٱلْمَلَكَيْنِ بِبَابِلَ هَٰرُوتَ وَمَٰرُوتَ ۚ وَمَا يُعَلِّمَانِ مِنْ أَحَدٍ حَتَّىٰ يَقُولَآ إِنَّمَا نَحْنُ فِتْنَةٌۭ فَلَا تَكْفُرْ ۖ فَيَتَعَلَّمُونَ مِنْهُمَا مَا يُفَرِّقُونَ بِهِۦ بَيْنَ ٱلْمَرْءِ وَزَوْجِهِۦ

እዚህ አንቀጽ ላይ “ሃሩትና ማሩት” እንዳመጹ የሚያሳይ ኃይለ-ቃል ወይም ፍንጭ ሽታው የለም። ምናልባት፦ “እነርሱም በአላህ ፈቃድ ካልኾነ በእርሱ አንድንም ጎጂዎች አይደሉም” የተባለው ስለ ሃሩትና ማሩት መስሏችሁ ከሆነ ተሳስታችኃል፦
2፥102 *”እነርሱም በአላህ ፈቃድ ካልኾነ በእርሱ አንድንም ጎጂዎች አይደሉም፥ የሚጎዳቸውንና የማይጠቅማቸውንም ይማራሉ”*፡፡ وَمَاوَمَا هُم بِضَارِّينَ بِهِ مِنْ أَحَدٍ إِلَّا بِإِذْنِ اللَّهِ ۚ وَيَتَعَلَّمُونَ مَا يَضُرُّهُمْ وَلَا يَنفَعُهُم

ምክንያቱም ሃሩትና ማሩት ሁለት ስለሆኑ ለእነርሱ የምንጠቀምበት ተውላጠ-ስም በሙተና “ሁማ” هُمَا ነው፥ ነገር ግን “በአላህ ፈቃድ ካልኾነ በእርሱ አንድንም ጎጂዎች አይደሉም” የተባሉትን ላይ “እነርሱም” ለሚለው የገባው “ሁም” هُم ሲሆን ከሁለት በላይ ጀመዕ መሆኑ “ሸያጢን” شَّيَٰطِين የሚለውን ተክቶ የመጣ ነው። ሸያጢን ሰዎችን ድግምትን የሚያስተምሩ ሲኾኑ ካዱ፥ ሰዎች ከሸያጢን የሚጎዳቸውንና የማይጠቅማቸውንም ይማራሉ።
ሲጀመር እዚህ አንቀጽ ላይ “ወ” وَ የሚለው መስተጻምር ሕዝብን ሲሕር የሚያስተምሩት ሸያጢን እና ሀሩትና ማሩትን የሚያስጠነቅቁበትን ትምህርት ለመለየት የገባ መስተፃምር ነው። ከመነሻው ሸያጢን የሚያስተምሩት ድግምት እና ለሀሩትና ማሩት ተወረደ የተባለው ነገር ሁለት ለየቅል የሆኑ ሀረግ መሆናቸው ፍንትውና ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። ሃሩትና ማሩት፦ “እኛ መፈተኛ ነንና አትካድ” እስከሚሉም ድረስ አንድንም አያስተምሩም፥ እነርሱ ላይ የተወረደው ስለ ሲሕር አውንታዊነት ሳይሆን አሉታዊነት የሚያስረዳ ትምህርት ነው።

ሲቀጥል “ማ” مَا የሚለው ቃል ሁለት ፍቺ ይኖረዋል፤ አንዱ “ማ” مَا “መውሱላ” ሲሆን ሁለተኛው “ማ” مَا “መስደሪያ” ነው።
1ኛ. “ማ” مَا የሚለውን “መውሱላ” ማለትም “አንፃራዊ ተውላጠ-ስም” ሆኖ ከተቀራ በባቢሎት በሚገኙት በሀሩትና በማሩት ላይ የተወረደ ነገር እንዳለ ያመለክታል፥ ያ ነገር ግን ከላይ ባየነው የሰዋስም ሙግት ከሸያጢን ሲሕር ተለይቶ በመስተፃምር ተቀምጧል።
2ኛ. “ማ” مَا የሚለው መስደሪያ ማለት “አፍራሽ-ቃል” በሚለው ከተቀራ ደግሞ በባቢሎት በሚገኙት በሀሩትና በማሩት ላይ የሸያጢን ሲሕር አልተወረደም የሚል ፍቺ ይኖረዋል። ምክንያቱም አይሁዳውያን ሚድራሽ በሚባለው መፅሐፋቸው ላይ፦ “ሲሕር በሁለቱ መላእክት በኩል ባቢሎን ላይ ከፈጣሪ የተወረደ ነው” የሚሉትን ቅጥፈት አላህ እያጋለጣቸው ነው። ምክንያቱም አይሁዳውያን አስማት የሰለሞን ጥበብ ነው የሚል እምነት አላቸው፤ ይህንን እሳቤ አንዳንድ ዐበይት ክርስትና በትውፊት ይጋሩታል። ይህንን ነጥብ ኢብኑ ዐባሥ፣ ኢብኑ ጀሪር፣ ቁርጡቢ ያነሱታል።

ሢሰልስ “ሀሩትና ማሩት” ማንና ምን ናቸው? የሚለውን ነጥብ ሁለት አመለካከቶች አሉት፤ ይህንም ጤናማ የተለያየ አመለካከት ያመጣው ጤናማው የቂርኣት ውበት ነው፥ “መለከይኒ” مَلَكَيْنِ የሚለው ቃል ”መለክ” مَلَك ማለትም ”መልአክ” ለሚለው ቃል ሙተና”dual” ሲሆን “ሁለት መላእክት” የሚል ፍቺ የሚኖረው “ላምን”ل ላም ፈትሓ “ለ” لَ ተብሎ ሲቀራ ነው። ሌላው “መሊከይኒ” مَلِكَيْنِ የሚለው ቃል “መሊክ” مَلِك ማለትም “ንጉሥ” ቃል ሙተና ሲሆን “ሁለት ነገሥታት” የሚል ፍቺ “ላምን” ل ላም ከስራ “ሊ” لِ ተብሎ ሲቀራ ነው። ሁለቱም ቂርኣት ከመለኮት የተወረደ እስከሆነ ድረስ በሁለቱም መቅራት ይቻላል። ይህ ነጥብ በጀላለይን፣ በአጥ-ጠበሪ፣ በዛማኽሻሪ፣ በባጋዊ እና በራዚ ተወስቷል። የውይይታችን ዋናውና ተቀዳሚው ሙግት ሀሩትና ማሩት ማንና ምን ናቸው? ሳይሆን መላእክት በፍጹም አምጸው አያውቅም የሚል ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
350 views09:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 12:33:45
ሃሩት እና ማሩት በፍፁም አላህን አላመፁም!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

2፥102 *”ሰይጣናትም በሱለይማን ዘመነ መንግስት የሚያነቡትን ተከተሉ፡፡ ሱለይማንም አልካደም፤ ግን ሰይጣናት ሰዎችን ድግምትን የሚያስተምሩ ሲኾኑ ካዱ፡፡ ያንንም በባቢል በሁለቱ መላእክት በሃሩት እና ማሩት ላይ የተወረደውን ነገር ያስተምሩዋቸዋል፡፡ «እኛ መፈተኛ ነንና አትካድ» እስከሚሉም ድረስ አንድንም አያስተምሩም፡፡ ከእነሱም በሰውየውና በሚስቱ መካከል በእርሱ የሚለዩበትን ነገር ይማራሉ”*፡፡ وَٱتَّبَعُوا۟ مَا تَتْلُوا۟ ٱلشَّيَٰطِينُ عَلَىٰ مُلْكِ سُلَيْمَٰنَ ۖ وَمَا كَفَرَ سُلَيْمَٰنُ وَلَٰكِنَّ ٱلشَّيَٰطِينَ كَفَرُوا۟ يُعَلِّمُونَ ٱلنَّاسَ ٱلسِّحْرَ وَمَآ أُنزِلَ عَلَى ٱلْمَلَكَيْنِ بِبَابِلَ هَٰرُوتَ وَمَٰرُوتَ ۚ وَمَا يُعَلِّمَانِ مِنْ أَحَدٍ حَتَّىٰ يَقُولَآ إِنَّمَا نَحْنُ فِتْنَةٌۭ فَلَا تَكْفُرْ ۖ فَيَتَعَلَّمُونَ مِنْهُمَا مَا يُفَرِّقُونَ بِهِۦ بَيْنَ ٱلْمَرْءِ وَزَوْجِهِۦ

ሰማያውያን ፍጥረታት መላእክት እንደ ጂን እና እንደ ሰው የራሳቸው ነጻ ምርጫ የላቸውም። ይህ ነጻ ምርጫ ስለሌላቸው በባሕያቸው ውስጥ ኩራትና አመጽ የለም፦
16፥49 ለአላህም በሰማያት ያለው ከተንቀሳቃሽም በምድር ያለው ሁሉ፣ *”መላእክትም ይሰግዳሉ፡፡ እነርሱም አይኮሩም”*፡፡ وَلِلَّهِ يَسْجُدُ مَا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ مِن دَابَّةٍ وَالْمَلَائِكَةُ وَهُمْ لَا يَسْتَكْبِرُونَ
318 views09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-28 18:41:32 https://vm.tiktok.com/ZMFSh7L9n/
 
ቲክቶክ ቻነላችን ላይ አዲስ ቪዲዬ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
402 views15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ