Get Mystery Box with random crypto!

Tiriyachen | ጥሪያችን

የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን
የሰርጥ አድራሻ: @tiriyachen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.91K

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-05-13 16:05:07 አላህን የምናመልከው ለምንድነው? | ኡስታዝ አቡሀይደር





  አዲስ ቪድዮ በዩትዩብ ቻነላችን ላይ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
252 views13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 21:41:07 እነዚህ አናቅጽ ላይ "ንጹሕ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ሠሊም" سَلِيم ነው፥ አንድ በኢሥላም ልቡን ሢያሠልም ልቡ ውስጥ "ሠላም" سَلَام ስላለ ልቡ ሠሊም ስትሆን እርሱ ደግሞ "ሣሊም" سَالِم‎ ይሆናል፦
ኢማም አሕመድ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 17027
ዐምር ኢብኑ ዐባሣህ እንደተረከው፦ "አንድ ሰው የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" ሆይ! ኢሥላም ምንድን ነው? ብሎ ጠየቀ፥ እርሳቸውም"ﷺ"፦ "ልብህን ለአሏህ ዐዘ ወጀል ማሥለም ነው" አሉት"። عَنْ عَمْرِو بْنِ عَبَسَةَ قَالَ قَالَ رَجُلٌ يَا رَسُولَ اللَّهِ مَا الْإِسْلَامُ قَالَ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أَنْ يُسْلِمَ قَلْبُكَ لِلَّهِ عَزَّ وَجَلَّ

አንድ ሰው ልቡን ለአሏህ ካሠለመ ጀነት ይገባል፥ ልቡን ለአሏህ ያሠለመ ሰው ከጀሀነም ይድናል፦
አል አደቡል ሙፍረድ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 260
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ነፍሴ በእጁ በሆነው እምላለው፥ እስካልሠለማችሁ ድረስ ጀነት አትገቡም"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ‏:‏ وَالَّذِي نَفْسِي بِيَدِهِ، لاَ تَدْخُلُوا الْجَنَّةَ حَتَّى تُسْلِمُوا
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 12, ሐዲስ 163
ዐምር ኢብኑ አል ዓስ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የሠለመ ዳነ"። عَنْ عَمْرِو بْنِ الْعَاصِ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ قَدْ أَفْلَحَ مَنْ أَسْلَمَ ‏"‏ ‏.‏

አምላካችን አሏህ በልባችን ውስጥ ያለውን እውነተኛ ሀብት እንድንጠቀም ይርዳን! በሠሊም ቀልብ ወደ እርሱ የምንመጣ ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ

ጥሪያችን በሁሉም ቦታ
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
300 views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 21:41:06 ቀልብ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

37፥84 ወደ ጌታው "በ-ንጹሕ ልብ” በመጣ ጊዜ የኾነውን አስታውስ፡፡፡ إِذْ جَاءَ رَبَّهُ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ

"ቀልብ" قَلْب የሚለው ቃል "ቀለበ" قَلَبَ ማለትም "ለበወ" "ኀለየ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ልብ" "ኃልዮ" ማለት ነው፥ "ልብ" የሚለው የግዕዝ ቃል "ለበወ" ማለትም "አጤነ" "አስተዋለ" "አመዛዘነ" "ዐወቀ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ማጤኛ" "ማስተዋያ" "ማመዛዘኛ" "ማወቂያ" የሚል ፍቺ አለው። "ፉአድ" فُؤَاد ስሜትን"emotion" የያዘ የውስጥ ክፍል ሲሆን "ዐቅል" عَقْل ደግሞ አመክንዮን"intellect" የያዘ የውስጥ ክፍል ነው፥ ፉኣድን እና ዐቅልን አመዛዝኖ የሚይዝ ውሳጣዊ ክፍል "ቀልብ" قَلْب ነው። "ቁሉብ" قُلُوب ደግሞ የቀልብ ብዙ ቁጥር ሲሆን "ልቦች" ማለት ነው፦
15፥51 አላህም "በልቦቻችሁ" ውስጥ ያለውን ሁሉ ያውቃል፡፡ አላህም ዐዋቂ ታጋሽ ነው፡፡ وَاللَّهُ يَعْلَمُ مَا فِي قُلُوبِكُمْ ۚ وَكَانَ اللَّهُ عَلِيمًا حَلِيمًا

"ነፍሥ" نَفْس ማለት "እራስነት"own self" ማለት ሲሆን አንፉሥ" أَنْفُس የነፍሥ ብዙ ቁጥር ነው፥ ነፍሥ በሰው ውስጥ ያለውን ልብ ለማመልከት ይመጣል፦
2፥284 በ"ነፍሶቻችሁ" ውስጥ ያለውን ብትገልጹ ወይም ብትደብቁት አላህ በእርሱ ይቆጣጠራችኋል"፡፡ وَإِن تُبْدُوا مَا فِي أَنفُسِكُمْ أَوْ تُخْفُوهُ يُحَاسِبْكُم بِهِ اللَّهُ ۖ

"ቁሉቢኩም" قُلُوبِكُمْ የሚለው "አንፉሢኩም" أَنفُسِكُمْ በሚል ተለዋዋጭ ከመጣ ዘንዳ ቀልብ ወይም ነፍስ ውስጥ ያለው ሀብት እውነተኛ ሀብት ሲሆን ይህም ውሳጣዊ ሀብት ነው፦
ሶሒሕ ኢብኑ ሒባን መጽሐፍ 1 ሐዲስ 3055
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ሀብት በውጪ አይኖርም፥ እውነተኛ ሀብት የነፍሥ ሀብት ብቻ ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ عَنْ رَسُولِ اللهِ صَلى الله عَلَيه وسَلم أَنَّهُ قَالَ لَيْسَ الْغِنَى عَنْ ظَهْرٍ إِنَّمَا الْغِنَى غِنَى النَّفْسِ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 35
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ "ሀብት ማለት መጠነ ሰፊ ንብረት መያዝ አይደለም፥ ነገር ግን ሀብት ማለት የነፍሥ ሀብት ነው። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ لَيْسَ الْغِنَى عَنْ كَثْرَةِ الْعَرَضِ، وَلَكِنَّ الْغِنَى غِنَى النَّفْسِ ‏”‌‏.‏

የውስጥ ሀብት እምነት፣ እሳቤ፣ አሳብ፣ የአስተሳሰብ ቅኝነት፣ ጥልቅ አመለካከት፣ ዕውቀት ነው፥ የውስጥ ድህነት ክህደት፣ ጭፍንነት፣ ጸለምተኝነት፣ ድንቁርና፣ መሃይምነት ነው። እውነተኛ ሀብትም ሆነ ድህነት በልብ ውስጥ ያለ ነው፦
አል-ሙዕጀመል ከቢር መጽሐፍ 4, ሐዲስ 154
አቢ ዘር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አቢ ዘር ሆይ! "የተትረፈረፈ ገንዘብ ሀብት ነው" ትላለህን? እኔም፦ "አዎ" አልኩኝ፥ እርሳቸውም፦ "የገንዘብ አለመኖር ድህነት ነው" ትላለህን? እኔም፦ "አዎ" አልኩኝ፥ እርሳቸውም ይህንን ሦስት ጊዜ ደጋገሙት። ከዚያም "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ"፦ "ሀብት በልብ ውስጥ ነው፥ ድህነትም በልብ ውስጥ ነው" አሉ"። عن أبي ذر قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَا أَبَا ذَرٍّ تَقُولُ كَثْرَةُ الْمَالِ الْغِنَى قُلْتُ نَعَمْ قَالَ تَقُولُ قِلَّةُ الْمَالِ الْفَقْرُ قُلْتُ نَعَمْ قَالَ ذَلِكَ ثَلاثًا ثُمَّ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ الْغِنَى فِي الْقَلْبِ وَالْفَقْرُ فِي الْقَلْبِ.
መጥፎ ሥራ የሚያሠራን ከልብ የተቀመጠው እውነተኛ ድህነት ነው፥ መልካም ሥራ የሚያሠራን ከልብ የተቀመጠው እውነኛው ሀብት ነው። አምላካችን አሏህ የሚመለከተው ልባችንን እና ሥራችንን እንጂ ቅርጻችንን እና ገንዘባችንን አይደለም፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 45, ሐዲስ 42
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ ወደ ቅርጻችሁ እና ገንዘባችሁ አይመለከትም፥ ነገር ግን ወደ ልባችሁ እና ሥራችሁ ይመለከታል"፡፡ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ إِنَّ اللَّهَ لاَ يَنْظُرُ إِلَى صُوَرِكُمْ وَأَمْوَالِكُمْ وَلَكِنْ يَنْظُرُ إِلَى قُلُوبِكُمْ وَأَعْمَالِكُمْ ‏"‏

ልብ የምንነይትበት የኒያህ መቀመጫ ነው፥ ሥራ የሚለካው በኒያህ ስለሆነ ሥራችን የልባችን ውጤት ነው። ጽድቅ መልካም ሥነ ምግባር"ethics" ሲሆን በግልጠተ መለኮት በኩል ከሥነ መለኮት የሚመጣ ነው፥ በተቃራኒው ኃጢአት በልብህ ውስጥ የሚሸረብ ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ, 45, ሐዲስ 16
አን ነዋሥ ኢብኑ ሠዕማል አል አንሷሪይ እንደተረከው፦ "እኔም "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" ስለ ጽድቅ እና ኃጢአት ጠየኳቸው፥ እርሳቸውም፦ "ጽድቅ መልካም ሥነ ምግባር ነው፥ ኃጢአት በልብህ ውስጥ የሚሸረብ ነው" አሉ"። عَنِ النَّوَّاسِ بْنِ سَمْعَانَ الأَنْصَارِيِّ، قَالَ سَأَلْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم عَنِ الْبِرِّ وَالإِثْمِ فَقَالَ ‏ "‏ الْبِرُّ حُسْنُ الْخُلُقِ وَالإِثْمُ مَا حَاكَ فِي صَدْرِكَ ‏"‏ ‏.‏
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ, 45, ሐዲስ 17
አን ነዋሥ ኢብኑ ሠዕማል አል አንሷሪይ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጽድቅ መልካም ሥነ ምግባር ነው፥ ኃጢአት በነፍስ ውስጥ የሚሸረብ ነው"። عَنِ النَّوَّاسِ بْنِ سَمْعَانَ الأَنْصَارِيِّ، قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ الْبِرُّ حُسْنُ الْخُلُقِ وَالإِثْمُ مَا حَاكَ فِي نَفْسِكَ ‏"‏ ‏

"ልብ" እና "ነፍስ" በአንድ ዐውድ ላይ ተለዋዋጭ ቃል ሆኖ መምጣቱ በራሱ ነፍስ ውሳጣዊ ልብን ያመለክታል፥ ልብ ይህን ያክል በሰው ሕይወት ላይ አውንታዊ ሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ አለው። ጀነት ወደ አሏህ በንጹሕ ልብ ለመጣ ትቀረባለች፥ ለምሳሌ፦ ኢብራሂም ወደ ጌታው በንጹሕ ልብ የመጣ ሰው ነው፦
50፥33 አልረሕማንን በሩቁ ኾኖ ለፈራ እና "በ-ንጹሕ ልብ" ለመጣ ትቀረባለች፡፡ مَّنْ خَشِيَ الرَّحْمَـٰنَ بِالْغَيْبِ وَجَاءَ بِقَلْبٍ مُّنِيبٍ
37፥84 ወደ ጌታው "በ-ንጹሕ ልብ” በመጣ ጊዜ የኾነውን አስታውስ፡፡፡ إِذْ جَاءَ رَبَّهُ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
26፥89 ወደ አላህ "በ-ንጹሕ ልብ" የመጣ ሰው ቢኾን እንጂ፡፡ إِلَّا مَنْ أَتَى اللَّهَ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
281 views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 21:40:58
247 views18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 20:48:30 ልጅ ቢኖረው

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

43፥81 «ለአልረሕማን ልጅ ቢኖረው እኔ ለልጁ የተገዢዎቹ መጀመሪያ ነኝ» በላቸው፡፡ قُلْ إِن كَانَ لِلرَّحْمَـٰنِ وَلَدٌ فَأَنَا أَوَّلُ الْعَابِدِينَ

ዐበይት ክርስቲያኖች፦ "ወልድ ከአብ ባሕርይ ባሕርይን ወስዶ፣ ከአካሉ አካልን ወስዶ እና አብን አህሎና መስሎ ከእርሱ ወጣ፣ ተወለደ፣ ተገኘ" በማለት አሏህን ወላዲ መሢሑን ተወላዲ በማድረግ ለአሏህ ቁራጭን አደረጉለት፦
43፥15 ከባሮቹም ለእርሱ ቁራጭን ልጅ አደረጉለት፡፡ ሰው በእርግጥ ግልጽ ከሓዲ ነው፡፡ وَجَعَلُوا لَهُ مِنْ عِبَادِهِ جُزْءًا ۚ إِنَّ الْإِنسَانَ لَكَفُورٌ مُّبِينٌ

ይህ የባሕርይ ልጅ የሚባል ለአሏህ የለውም፥ አሏህ አንድ ነው፥ እርሱ ከማንነቱ እና ከምንነቱ ማንንም አልወለደም። ከእርሱ ማንነት እና ምንነት የተወለደ ማንም የለም፥ ከእርሱ የተወለደ ማንም አምላክ የለም፦
112፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው፡፡ قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
112፥3 አልወለደም፤ አልተወለደምም፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ
23፥91 አላህ ምንም ልጅን አልወለደም፡፡ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ مَا اتَّخَذَ اللَّهُ مِن وَلَدٍ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ

ወደ ፈትለ ነገሩ ስንገባ አምላካችን አሏህ የባሕርይ ልጅ እንደሌለው ለማመላከት የተጠቀመበት ሐርፉ አሽ-ሸርጥ በመጠቀም ነው፥ "ሐርፉ አሽ-ሸርጥ" حَرْف الشَرْط ማለት "ሁኔታዊ መስተዋድድ"conditional particle" ነው፦
43፥81 «ለአልረሕማን ልጅ ቢኖረው እኔ ለልጁ የተገዢዎቹ መጀመሪያ ነኝ» በላቸው፡፡ قُلْ إِن كَانَ لِلرَّحْمَـٰنِ وَلَدٌ فَأَنَا أَوَّلُ الْعَابِدِينَ

"ኢን" إِن ወይም "ለው" لَوْ በሰዋሰው አቀማመጥ ሐርፉ አሽ-ሸርጥ ነው፥ እዚህ አንቀጽ ላይ "ኢን" إِن የሚለው የገባው ሐርፉ አሽ-ሸርጥ "አሏህ ልጅ የለውምና ስለዚህ ዒሣን አትገዙት" እንጂ "ልጅ ካለው መገዛት ይቻላል" የሚል በፍጹም አይደለም። ለዚህ አንቀጽ ተመሳሳይ አንድ የሙግት ናሙና እናቅርብ፦
7፥143 ሙሳም ለቀጠሯችን በመጣና ጌታውም ባነጋገረው ጊዜ፡- *«ጌታዬ ሆይ! አሳየኝ ወደ አንተ እመለከታለሁና» አለ፡፡ አላህም፡- «በፍጹም አታየኝም ግን ወደ ተራራው ተመልከት፡፡ "በስፍራውም ቢረጋ በእርግጥ ታየኛለህ"» አለው፡፡ ጌታው ለተራራው በተገለጸ ጊዜ እንኩትኩት አደረገው፡፡ ሙሳም ጮሆ ወደቀ፡፡ በአንሰራራም ጊዜ «ጥራት ይገባህ፡፡ ወደ አንተ ተመለስኩ፡፡ እኔም የምእምናን መጀመሪያ ነኝ» አለ፡፡ وَلَمَّا جَاءَ مُوسَىٰ لِمِيقَاتِنَا وَكَلَّمَهُ رَبُّهُ قَالَ رَبِّ أَرِنِي أَنظُرْ إِلَيْكَ ۚ قَالَ لَن تَرَانِي وَلَـٰكِنِ انظُرْ إِلَى الْجَبَلِ فَإِنِ اسْتَقَرَّ مَكَانَهُ فَسَوْفَ تَرَانِي ۚ فَلَمَّا تَجَلَّىٰ رَبُّهُ لِلْجَبَلِ جَعَلَهُ دَكًّا وَخَرَّ مُوسَىٰ صَعِقًا ۚ فَلَمَّا أَفَاقَ قَالَ سُبْحَانَكَ تُبْتُ إِلَيْكَ وَأَنَا أَوَّلُ الْمُؤْمِنِينَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ኢን" إِن የሚለው የገባው ሐርፉ አሽ-ሸርጥ "ተራራው አይረጋምና ስለዚህ አታየኝም" እንጂ "ቢረጋ ታየኛለህ" ማለት እንዳልሆነ ሁሉ በተመሳሳይ ከላይ ያለውን አንቀጽ በዚህ ልክ እና መልክ መረዳት ይቻላል።
"በስፍራውም ቢረጋ" ማለት "አይረጋም" ማለት ከሆነ "ልጅ ቢኖረው" ማለት "የለውም" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "በስፍራውም ቢረጋ በእርግጥ ታየኛለህ" ማለት "አይረጋም አታየኝም" የሚለውን ለመግለጽ የመጣ ግነታዊ አገላለጽ እንደሆነ ሁሉ "ለአልረሕማን ልጅ ቢኖረው" ማለት "ለአልረሕማን ልጅ የለውም" የሚለውን የሚለውን ለመግለጽ የመጣ ግነታዊ አገላለጽ ነው።
ዕውቀት አልባ የሆነ ባተሎ እና ዘባተሎ እሳቤ ይዞ የአሏህን ንግግር ለመተቸት የሚያስችል የሞራል ብቃት፣ አቅም፣ ወኔም የላችሁም። አሏህ ሂዳያ ይስጣችሁ፥ ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ

ጥሪያችን በሁሉም ቦታ
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
353 views17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 20:48:14
318 views17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 19:33:00 ጥያቄአችን!

የእግዚአብሔር ፍጥረት መጀመርያው ማን ነው? ጉማሬ? ሰማይና ምድር? ወይስ ኢየሱስ?

A. ጉማሬ፦

”ከአንተ ጋር የሠራሁትን ጉማሬ እስኪ ተመልከት”፤ እንደ በሬ ሣር ይበላል።
ኢዮብ 𝟒𝟎፥𝟏𝟓

”እርሱ የእግዚአብሔር ፍጥረት “አውራ” רֵאשִׁ֣ית ነው”።
ኢዮብ 𝟒𝟎፥𝟏𝟗

“he Is thE FIRst OF THe worKS OF God; Let HIM Who MaDe hIm BRiNg near HIs swoRD!

enGlish sTAndArD versiOn

“አውራ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “መጀመሪያ”The firsT” ተብሎ ከላይ ተቀምጧል። የዕብራይስጡ ላይ ደግሞ “ረሺት” רֵאשִׁ֣ית ሲሆን ይህ “ረሺት” ቃል ለሰማይና ምድር ጅማሬነት አገልግሎት ላይ ውሏል።

B. ሰማይንና ምድር፦

በመጀመሪያ בְּרֵאשִׁ֖ית እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።
ዘፍጥረት 𝟏፥𝟏

“በ” ב ማለት “በ” ማለት ሲሆን መስተዋድድ ነው። “ረሺት” רֵאשִׁ֣ית ደግሞ “መጀመሪያ” ማለት ነው።

c. ኢየሱስ፦

እዚህ አንቀጽ ላይ ደግሞ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ፍጥረት መጀመሪያ ነው ይለናል፦

አሜን የሆነው፥ የታመነውና እውነተኛው ምስክር፥ ”የእግዚአብሔር ፍጥረት መጀመሪያ” የነበረው እንዲህ ይላል፦ The BegInNING Of ThE cReatiOn OF gOD. (EnGLish reVised VERsIon)
ራእይ 𝟑፥𝟏𝟒

ግሪኩ፦ Ἡ ἈΡΧὴ ΤΗ͂ς κΤίΣεως ΤΟΥ͂ ΘεΟΥ͂:

“የእግዚአብሔር ፍጥረት መጀመሪያ” የሚለው ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ “መጀመሪያ” ለሚለው የገባው ቃል ልክ እንደ የሙታን መጀመሪያ “አርኬ” ἀΡΧΉ መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል፦

አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኵር ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል።
𝟏 ቆሮንቶስ 𝟏𝟓፥𝟐𝟎

ግሪክ፦ νΥνὶ δῈ ΧρισΤῸΣ ἘγήγΕΡταΙ ἐΚ νΕκρῶΝ, ἀπΑρχῊ Τῶν ΚΕΚοιΜΗΜένωΝ.

“በኵር” የሚለው የግሪኩ ቃል “አፕ-አርኬ” ἀπαΡχὴ ሲሆን የሁለት ቃላት ውቅር ነው፤ “አፓ” ἀΠό ማለትም “ከ” እና “አርኬ” ἀΡχΉ ማለትም “መጀመሪያ” ነው፤ ላንቀላፉት ሙታን “መጀመሪያ” ነው ማለት መጀመሪያ የተነሳ ማለት ከሆነ የእግዚአብሔር ፍጥረት መጀመሪያ ማለት መጀመሪያ የተፈጠረ ማለት ነው።

ስለዚህ የእግዚአብሔር ፍጥረት መጀመርያው ማን ነው? ጉማሬ? ሰማይና ምድር? ወይስ ኢየሱስ?

ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

ጥሪያችን በሁሉም ቦታ
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
634 views16:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 19:32:48
484 views16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 00:11:32 የመጽሀፍ ቅዱስ የእርስበርስ መኮራረጅ

አንድ መጽሀፍ ኮረጀ የሚባለው ከሌላ መጽሀፍ ሀሳብን እንደወረደ ሲወስድ ነው። ልብ በሉ “ከሌላ መጽሀፍ”..! መጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ ግን መፀሀፍቱ እራሱ እርስበርስ እዚያው ሲኮራረጁ ታስተውላላችሁ። የሚኮራረጁት አንድ አንቀጽ ወይንም ሁለት አንቀፅ ብቻ አይደለም፤ ከሞላ ጎደል ሙሉ ምዕራፍ ነው። ይህንን አስቂኝም አስገራሚም ጉዳይ እስኪ በማስረጃ እናድርገው።

መጽሀፍ ቅዱስን ስንከፍት የትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ 𝟑𝟕 ስር ያሉ አንቀፆች ያለምንም መለዋወጥ በመጽሀፈ ነገስት ካልዕ 𝟏𝟗 ላይ ይገኛሉ። እንዲሁ ተራ መመሳሰል ብቻ እንዳይመስላችሁ። ኩረጃ እንደሆነ በሚያሳብቅ መልኩ ቃል በቃል ያለምንም መለዋወጥ ነው አንደኛው ከአንደኛው የቀዳ..!

❐ አንቀፆቹን አስቀምጨ ፍርዱን ለእናንተ ከመስጠቴ በፊት መጽሀፍቶቹ የተፃፉበትን ጊዜ እንደ መረጃ ሰጥቻችሁ ልለፍ፦

፩-በርግጥ ከነ አካቴው መጽሀፈ ነገስት የተፃፈበት ጊዜ እንደማይታወቅ የመጽሀፍ ቅዱስ ምሁራን ይገልፃሉ። መምህር ያሬድ ሽፈራው “የመጽሀፍ ቅዱስ ታሪካዊ አመጣጥ” በሚለው መጽሀፉ ቅጽ 𝟏 ገፅ 𝟐𝟓 ላይ ከመገመት ውጭ ትክክለኛው ጊዜ እንደማይታወቅ ገልፆ ግምቱ ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ𝟓𝟖𝟔-𝟓𝟑𝟗 ሊሆን እንደሚችል ያስቀምጣል። ማኅበረ ቅዱሳን ባዘጋጀውና መምህር ቸርነት አበበ ባዘጋጁት “መሠረታዊ የመጽሀፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴ” በሚለው መጽሀፍ ላይ ገፅ 𝟏𝟑𝟖 ጀምሮ በደፈናው ጸሀፊውም ጊዜውም እንደማይታወቅ ጠቅሶ ያልፋል።

፪- ትንቢተ ኢሳያስን በተመለከተ መምህር ቸርነት አበበ እንደገለፁት የተጻፈው ከክርስቶስ ልደት በፊት 𝟖𝟖𝟖-𝟕𝟒𝟎 ሊሆን እንደሚችል ያስቀምጣሉ። iBiD 𝟐𝟎𝟒

ይህንን እንደመግቢያ ካየን ሁለቱን ምዕራፎች ከታች ላስቀምጥላችሁና በፍጹም ተመሳሳይነታቸው ተገረሙ። በርግጥ ኮርጇል ብላችሁ የምትወቅሱት ሰው ላይኖር ይችላል፤ ምክንያቱም የሁለቱም መጽሀፍት ጸሀፊዎች ከግምት ውጭ በትክክል ማን እንደጻፈው አይታወቅም።

ማስታወሻ፦ ቦታ ለመቆጠብ ከምዕራፎቹ የምጠቅሰው ሶስት አንቀፆች ብቻ ሲሆን የቀረውን ክፍል እናንተው ከፍታችሁ ማረጋገጥ ትችላላችሁ።

“እንዲህም ሆነ፤ ንጉሡ ሕዝቅያስ ይህን በሰማ ጊዜ ልብሱን ቀደደ፥ ማቅም ለበሰ፥ ወደ እግዚአብሔርም ቤት ገባ። የቤቱንም አዛዥ ኤልያቄምን ጸሐፊውንም ሳምናስን የካህናቱንም ሽማግሌዎች ማቅ ለብሰው ወደ ነቢዩ ወደ አሞጽ ልጅ ወደ ኢሳይያስ ይሄዱ ዘንድ ላካቸው። እነርሱም፦ ሕዝቅያስ እንዲህ ይላል፦ ይህ ቀን የመከራና የተግሣጽ የዘለፋም ቀን ነው፤ ልጆች የሚወለዱበት ጊዜ ደርሶአል ለመውለድም ኃይል የለም።”

ትንቢተ ኢሳይያስ 𝟑𝟕፥𝟏-𝟑

እንለፍ

“ንጉሡም ሕዝቅያስ ይህን በሰማ ጊዜ ልብሱን ቀደደ፥ ማቅም ለበሰ፥ ወደ እግዚአብሔርም ቤት ገባ። የቤቱንም አዛዥ ኤልያቄምን ጸሐፊውንም ሳምናስን የካህናቱንም ሽማግሌዎች ማቅ ለብሰው ወደ ነቢዩ ወደ አሞጽ ልጅ ወደ ኢሳይያስ ይሄዱ ዘንድ ላካቸው። እነርሱም፦ ሕዝቅያስ እንዲህ ይላል፦ ይህ ቀን የመከራና የተግሣጽ የዘለፋም ቀን ነው፤ ልጆች የሚወለዱበት ጊዜ ደርሶአል፥ ለመውለድም ኃይል የለም።”
መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 𝟏𝟗፥𝟏-𝟑

(የሕያ ኢብኑ ኑህ)

ጥሪያችን በሁሉም ቦታ
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
524 views21:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 00:11:19
375 views21:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ