Get Mystery Box with random crypto!

Tiriyachen | ጥሪያችን

የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን
የሰርጥ አድራሻ: @tiriyachen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.91K

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-02-14 23:02:27
249 views20:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-14 20:28:16
ጥያቄዎቻችን - ዘፍጥረት

በመጀመሪያ የዘፍጥረት አንቀፆች ስንመለከት እግዚአብሄር ብርሀንን በመጀመሪያ ቀን እንደፈጠረው ይነግረናል (ዘፍጥረት 1:3) ነገር ግን ቀጥሎ ፀሀይና ጨረቃ ከዛ በኃላ ባሉት ቀናት እንደተፈጠሩ ይነግረናል (ዘፍጥረት 1:16)

1- ጥያቄው የብርሀን ምንጭ የሆነው ፀሀይ ሳይፈጠር እንዴት ብርሀን ሊፈጠር ቻለ? ካለ ፀሀይ አብሪነት ብረሀን እንዴት ሊኖር ቻለ?

2- የብርሀን ምንጭ ፀሀይ የመሆኗን ሳይንሳዊ እውነታ የዘፍጥረት ፀሀፊ ወይንም እግዚአብሄር አያውቅም ነበር ማለት ነው?
የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
276 views17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-14 18:37:05 አድመኝነት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

3፥54 “እነርሱም አደሙ አላህም አድማቸውን መለሰባቸው። አላህም ከአድመኞች ሁሉ በላጭ ነው”፡፡ وَمَكَرُوا وَمَكَرَ اللَّهُ ۖ وَاللَّهُ خَيْرُ الْمَاكِرِينَ

አምላካችን አሏህ ከእስራኤል ልጆች እነዚያ የካዱት ዒሣን ሊገሉት ሲማከሩ፣ ሲያቅዱ፣ ሲያሴሩ እና ሲያድሙ በአሸናፊነቱ እና በጥበቡ አከሸፈባቸው፥ አሏህ ምክራቸውን፣ ዕቅዳቸውን፣ ሴራቸውን፣ ተንኮላቸውን እና አድማቸው ዒሣን ወደ ራሱ በመውሰድ መለሰባቸው፦
3፥54 “እነርሱም አደሙ አላህም አድማቸውን መለሰባቸው፡፡ አላህም ከአድመኞች ሁሉ በላጭ ነው”፡፡ وَمَكَرُوا۟ وَمَكَرَ ٱللَّهُ ۖ وَٱللَّهُ خَيْرُ ٱلْمَٰكِرِينَ

“መከሩ” مَكَرُوا۟ ማለት “አሳሳቱ” ማለት ሳይሆን “መከሩ” “ዐቀዱ” “አሴሩ” “አደሙ” ማለት ነው፥ አሏህም ዒሣን ለመግደል የተማከሩትን ምክር፣ ያቀዱትን ዕቅድ፣ ያሴሩትን ሴራ፣ ያደሙትን አድማ ወደ ራሱ በመውሰድ አከሸፈባቸው፥ አሏህም ከአድመኞች ሁሉ በላጭ ነው። “አድመኞች” ለሚለው የገባው ቃል “ማኪሪን” مَٰكِرِين ሲሆን “መካሪዎች” “አቃጂዎች” “ተንኮለኞ” “ሴረኞች” እና “አድመኞች” ማለት ነው፥ እዚህ አንቀጽ ላይ “ማኪሪን” مَٰكِرِين የተባሉት ከእስራኤል ልጆች እነዚያ የካዱት ዒሣን ሊገሉት ሲያሴሩ የነበሩት ናቸው። አሏህ ከእነዚህ ሴረኞች ሁሉ በላጭ ነው፥ ለምሳሌ እነዚያን የመካ ከሃድያን ነቢያችንን”ﷺ” ሊያስሩ ወይም ሊገሉ ወይም ከመካ ሊያወጡ በእሳቸው ላይ በመከሩ ጊዜ አሏህ ምክራቸውን መልሶባቸዋል፦
8፥30 እነዚያም የካዱት ሊያስሩህ ወይም ሊገድሉህ ወይም ከመካ ሊያወጡህ በአንተ ላይ ”በመከሩብህ” ጊዜ አስታውስ፡፡ ”ይመክራሉም” አላህም ”ተንኮላቸውን ይመልስባቸዋል”፡፡ አላህም ”ከመካሪዎቹ ሁሉ በላይ ነው”፡፡ وَإِذْ يَمْكُرُ بِكَ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ لِيُثْبِتُوكَ أَوْ يَقْتُلُوكَ أَوْ يُخْرِجُوكَ ۚ وَيَمْكُرُونَ وَيَمْكُرُ ٱللَّهُ ۖ وَٱللَّهُ خَيْرُ ٱلْمَٰكِرِينَ

እዚህ አንቀጽ ላይ “መከሩ” ለሚለው የገባው ቃል “የምኩሩ” يَمْكُرُ መሆኑን እና “ይመክራሉ” ለሚለው የገባው ቃል “የምኩሩነ” يَمْكُرُونَ እንደሆነ አንባቢ ልብ ይለዋል። “መክር” مَكْر ማለት “ምክር” “ዕቅድ” “ሴራ” “ደባ” “ተንኮል” ማለት ነው፥ መላእክት ሰዎች በሚስጥር የሚመሳጠሩትን ምክር ሰምተም ይጽፋሉ፦
10፥21 “አላህ ቅጣተ ፈጣን ነው፥ «መልክተኞቻችን የምትመክሩትን “ምክር” በእርግጥ ይጽፋሉ» በላቸው”፡፡ قُلِ اللَّهُ أَسْرَعُ مَكْرًا ۚ إِنَّ رُسُلَنَا يَكْتُبُونَ مَا تَمْكُرُونَ

ወደ ባይብል ስንመጣ ክርስቲያኖች ወደ ራሳቸው የሚያስጠጉበት ጳውሎስ አድመኝነት "የሥጋ ሥራ" እንደሆነ ተናግሯል፦
ገላትያ 5፥20 መዳራት፥ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት።

እዚህ አንቀጽ ላይ "አድመኝነት" ብቻ ሳይሆን "ቁጣ" እራሱ የሥጋ ሥራ እንደሆነ ከተገለጸ እግዚአብሔር ቁጠኛ ሆኖ ይቆጣል፥ በማይታዘዙት ላይ የእርሱ ቁጣ ይመጣል፦
መዝሙር 95፥11 ወደ ዕረፍቴም እንዳይገቡ፡ "በቁጣዬ" ማልሁ።
ዘዳግም 1፥34 እግዚአብሔርም የቃላችሁን ድምፅ ሰምቶ "ተቆጣ"።
ሮሜ 9፥22 ነገር ግን እግዚአብሔር "ቍጣውን" ሊያሳይ ኃይሉንም ሊገልጥ ወዶ።
ኤፌሶን 5፥6 ከዚህ የተነሣ በማይታዘዙት ልጆች ላይ "የእግዚአብሔር ቁጣ" ይመጣልና።

"ቁጣ" የሥጋ ሥራ ከሆነ እግዚአብሔር የሥጋ ሥራ እየሠራ ነውን? የሥጋ ሥራ የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት የማይወርሱ ከሆነ እግዚአብሔር መቆጣቱ እና ቁጠኛ መሆኑን ግምት ውስጥ አስገቡት፦
ገላትያ 5፥21 እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።

በሰፈሩት ቁናህ መሰፈር ይልኩካል እንደዚህ ነው። አሏህ ማደሙ የሥጋ ሥራ ነው ካላችሁ እግዚአብሔር መቆጣቱስ የሥጋ ሥራ አይደለምን? አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
287 views15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-14 18:36:41
262 views15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 21:34:23
የኢየሱስ ክርስቶስ ኣምላክና አባት ማነው?
"የርኅራኄ አባት የመጽናናትም ሁሉ አምላክ የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።”
(2ኛ ቆሮንጦስ 1:3)

"ለዘላለም የተባረከ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት እንዳልዋሽ ያውቃል።”
(2ኛ ቆሮንጦስ 11:31)

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።”
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1:3)

የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ”
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1:17)

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ”
( 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1:3-5)

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
128 views18:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 19:05:44 https://vm.tiktok.com/ZMYMkrPcq/
 
ቲክቶክ ቻነላችን ላይ አዲስ ቪዲዬ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
172 views16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 21:38:40
266 views18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 21:38:38 7፥197 *እነዚያም ከእርሱ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱም*። وَٱلَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِهِۦ لَا يَسْتَطِيعُونَ نَصْرَكُمْ وَلَآ أَنفُسَهُمْ يَنصُرُونَ

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ

ጥሪያችን በሁሉም ይገኛል
መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
249 viewsedited  18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 21:38:37 ለመስቀል ይሰገዳልን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

41፥37 ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ *"ለፀሐይና ለጨረቃ አትስገዱ፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው ለአላህ ስገዱ ፡፡ እርሱን ብቻ የምትገዙ እንደ ኾናችሁ ለሌላ አትስገዱ”*፡፡ وَمِنْ آيَاتِهِ اللَّيْلُ وَالنَّهَارُ وَالشَّمْسُ وَالْقَمَرُ ۚ لَا تَسْجُدُوا لِلشَّمْسِ وَلَا لِلْقَمَرِ وَاسْجُدُوا لِلَّهِ الَّذِي خَلَقَهُنَّ إِن كُنتُمْ إِيَّاهُ تَعْبُدُونَ

በቁርኣን "ሡጁድ” سُّجُود የሚለው ቃል “ሠጀደ” سَجَدَ ማለት “ሰገደ” ወይም “ታዘዘ” ከሚል ሥርወ-ቃል የተገኘ ሲሆን “ስግደት” ወይም “መታዘዝ” ማለት ነው፤ ሡጁድ ደግሞ በሁለት ይከፈላል፦ አንዱ “ሡጁዱል ዒባዳ” سُّجُود العبادة ማለትም “የአምልኮ ስግደት” ሲሆን ሌላው “ሡጁዱ አተሒያ” سُّجُود التحيه ማለትም “የአክብሮት ስግደት” ነው፤ ነገር ግን ይህ አክብሮት አቅጣጫውን ቀይሮ አምልኮ እየሆነ ስላለ ከሰላምታ ውጪ በሱጁድ ለፍጡራን ማጎብደድ፣ መተናነስ፣ ማሸርገድ ቁርአን ሲወርድ ቆሟል፤ የአክብሮት ስግደት ከአምልኮ ስግደት ጋር እንዳይደባለቅ የተከለከለው በነቢያችን”ﷺ” ጊዜ ነው፤ አላህም፦ "ሁሉን ለፈጠረው ለእርሱ እንጂ ለሌላ አትስገዱ" ብሎናል፤ ከአላህ ሌላ የሚገዙት ግዑዛን ነገር የገሀነም ማገዶዎች ናቸው፦
41፥37 ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ *"ለፀሐይና ለጨረቃ አትስገዱ፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው ለአላህ ስገዱ ፡፡ እርሱን ብቻ የምትገዙ እንደ ኾናችሁ ለሌላ አትስገዱ”*፡፡ وَمِنْ آيَاتِهِ اللَّيْلُ وَالنَّهَارُ وَالشَّمْسُ وَالْقَمَرُ ۚ لَا تَسْجُدُوا لِلشَّمْسِ وَلَا لِلْقَمَرِ وَاسْجُدُوا لِلَّهِ الَّذِي خَلَقَهُنَّ إِن كُنتُمْ إِيَّاهُ تَعْبُدُونَ
21፥8 እናንተ *"ከአላህ ሌላ የምትገዟቸውም የገሀነም ማገዶዎች ናችሁ*፡፡ እናንተ ለእርሷ ወራጆች ናችሁ። إِنَّكُمْ وَمَا تَعْبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ حَصَبُ جَهَنَّمَ أَنتُمْ لَهَا وَٰرِدُونَ

ማገዶዎች በሚለው ቃላት “ማ” َمَا የሚለው አንፃራዊ ተውላጠ-ስም አቅል የሌላቸውን ጣዖታት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፤ አቅል ያላቸውን ማንነቶች “መን” مَّن የሚል አንፃራዊ ተውላጠ-ስም የሚጠቀመው፤ ግን እዚህ አንቀፅ ላይ “ማ” የሚል አንፃራዊ ተውላጠ-ስም መጠቀሙ አቅል የሌላቸውን ጣዖታት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፤ ከአላህ ውጪ የሚደረግ ባዕድ አምልኮ “ጣጉት” لطَّاغُوتِ ማለትም "ጣዖት" ይባላል።
ወደ ባይብል ስንመጣ “ስግደት” የሚለው ቃል በዕብራይስጥ “ሻቻህ” שָׁחָה ሲሆን በግሪክ ደግሞ “ፕሮስካኒኦ” προσκυνέω ይባላል፤ ይህም ለተለያየ ምንነት ሆነ ማንነት በኒያ”intention” የሚቀርብ አምልኮን”Adoration” ወይም አክብሮትን”prostration” ነው ለማመልከት በባይብል ተጠቅሞበታል፤ የአምልኮት ስግደት በባህርይ የአንድ አምላክ ሃቅና ገንዘብ ሲሆን የአክብሮት ስግደት ደግሞ በፀጋ ለህያዋን ማንነት ማክበርን ያመለክታል፤ ግን ለግዑዛን ነገሮች አምልኮም ይሁን ስግደት ተከልክሏል፤ በዕብራይስጥ “ኤሊል” אֱלִיל ማለት “ምስል”፣ “ቅርፅ”፣ “ጣዖት” ማለት ሲሆን በግሪክ ደግሞ “ኤዶሎን” εἴδωλον ነው፤ ትርጉሙ ተመሳሳይ ነው። የሙሴ አምላክ ለሙሴ “”ለእናንተ ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ፣ የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፣ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም”” ብሎ ተናግሯል፤ እንደውም ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ ይላል፦
ዘሌዋውያን 26፥1 እኔ ያህዌህ አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ *”ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ”*፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ።
ዘጸአት 20፥4 በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር *”የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፤ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም”*፤
መዝሙር 97፥7 *”ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ፥ በጣዖቶቻቸውም የሚመኩ ይፈሩ*”፤ መላእክቱ ሁሉ ስገዱለት።

መስቀል በሃውልት ድንጋይ፣ እንጨት፣ ወርቅ፣ ብር፣ ብረት፣ ነሐስ ወዘተ ነው፤ ይህ ግዑዝ ነገር በአበይት ክርስቲያኖች ይሰገድለታል፥ ምስጋና ይቀርበለታል፤ ይህ በተግባር ሲሆን በጽሑፍ ደግሞ የዘወትር ፀሎት ላይ እንዲህ ይነበባል፦
ግዕዙ፦
“እሰግድ “ለ”መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘተቀደሰ በደሙ ክቡር”
ትርጉም፦
“ዓለምን ለማዳን ሲል ኢየሱስ ክርስቶስ “ለ”ተሰቀለበት መስቀል እሰግዳለው”
ግዕዙ፦
“ስብሐት “ለ”መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ በምህረቱ ይዘከረነ”
ትርጉም፦
” “ለ”ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ምስጋና ይገባዋል”
“ለ”ተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ እየተባለ ለምንድን ነው ለግዑዝ ነገር የፀጋ ስግደት የሚሰገድለት? የሚሰማበት ዐቅል የት አለውና ነው ምስጋናስ የሚቅብለት? ይህንን ስንላቸው ለመስቀል ስግደት እንደሚገባው ይህ ጥቅስ ያሳያል ይላሉ፦
መዝሙር 132፥7 ወደ ማደሪያዎቹ እንገባለን፤ *እግሮቹ በሚቆሙበት ስፍራ እንሰግዳለን*።

እዚህ አንቀጽ ላይ "መስቀል" የሚለው ቃል ይቅርና ስለ መስቀል እሳቤው እንኳን የለም። "እግሮቹ የቆሙበት በመስቀል ላይ ነው" የሚል ተልካሻ ምክንያት በማቅረብ ይዳዳሉ። ቅሉ ግን "እግሮቹ "በ"ሚቆሙበት ስፍራ እንሰግዳለን" አለ እንጂ "እግሮቹ "ለ"ሚቆሙበት ስፍራ እንሰግዳለን" አላለም፤ "ለ" እና "በ" የሚሉ በይዘትና በአይነት ሁለት መስተዋድዶች ናቸው። ሲቀጥል "በ"ሚቆሙበት "ስፍራ" አለ እንጂ "በ"ሚቆሙበት "መስቀል" መቼ አለ? አውዱ ላይ "ስፍራ" የሚለው ቦታን እንደሆነ ይናገራል፦
መዝሙር 132፥5 *ለእግዚአብሔር "ስፍራ"፥ ለያዕቆብ አምላክ "ማደሪያ" እስካገኝ ድረስ ብሎ*።

ምን ትፈልጋለህ? "ስፍራ" የተባለው መስቀል ሳይሆን "የቅድስናው ስፍራ" ነው፤ "በ"ዚህ ስፍራ "ለ"እግዚአብሔር ይሰገዳል ይላል፦
መዝሙር 96፥9 *"በ"ቅድስናው ስፍራ "ለ"እግዚአብሔር ስገዱ"*፤

አሁንም "ለ" እና "በ" የሚሉ ሁለት መስተዋድዶች ለዩ፤ "በ" ቦታን "ለ" ምነነትን ያመለክታል፤ በቅድስና ስፍራ ለእግዚአብሔር ይሰገዳል እንጂ ለስፍራ አይሰገድም። የእግሮቹ መቆሚያ ማለትም የእግሮቹ መረገጫ የቅድስናው ስፍራ እንጂ መስቀሉ አይደለም፦
ሕዝቅኤል 43፥7 እንዲህም አለኝ፦ የሰው ልጅ ሆይ፥ በእስራኤል ልጆች መካከል ለዘላለም የምቀመጥበት *የዙፋኔ ስፍራና የእግሬ ጫማ መረገጫ ይህ ነው*።

ይህንን ጉድ እያየ ወደ ክርስትና የሚገባ ሰው ቂል ካልሆነ ወይም በጥቅማ ጥቅም አሊያም በተቃራኒ ጾታ ፍቅር መነደፍ ካልሆነ በስተቀር አይሞክረውም። መስቀል በሃውልት ድንጋይ፣ እንጨት፣ ወርቅ፣ ብር፣ ብረት፣ ነሐስ ወዘተ ነው፤ ለዚህ ግዑዝ ነገር የምትሰግዱ ካላችሁ ጊዜው ሳይረፍድ ወደ አላህ በንስሃ ተመለሱ። ከአላህ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱምና፦
231 views18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 19:27:31 አምላክ ወይስ ጌታ?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

5፥72 እነዚያ *«አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው»* ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ

በግሪክ ኮይኔ የተዘጋጁ የአዲስ ኪዳን እደ-ክታባታት 5800 ገደማ ሲሆኑ፥ ከእነዚህ ዋና ዋናዎቹ ደግሞ ኮዴክስ ሳይናቲከስ፣ ኮዴክስ ቫቲካነስ፣ ኮዴክስ አሌክሳንድሪየስ፣ ኮዴክስ ኤፍሬማይ ናቸው። በ 330 ድኅረ-ልደት በተዘጋጀው በኮዴክስ ሳይናቲከስ እና በ 350 ድኅረ-ልደት በተዘጋጀው በኮዴክስ ቫቲካነስ መካከል የቃላት ሆነ የአሳብ ልዩነት አላቸው፥ ፊተኛው ኮዴክስ ሳይናቲከስ ያዘጋጁት ኢየሱስን "ጌታችን" ሲሉት ኃለኛው ኮዴክስ ቫቲካነስ ያዘጋጁት ደግሞ "አምላካችን" ብለውታል፦
2ኛ ጴጥሮስ 1፥1 የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያና ሐዋርያ የሆነ ስምዖን ጴጥሮስ፥ *በጌታችን እና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ* ጽድቅ ካገኘነው ጋር የተካከለ የክብር እምነትን ላገኙ። ϲυμεων πετροϲ δουλοϲ και αποϲτο λοϲ ιυ χυ τοιϲ ϊϲο τιμον ημιν λαχου ϲιν πιϲτιν ειϲ δι καιοϲυνην του κυ ημων και ϲωτη ροϲ ιυ χυ

እዚህ አንቀጽ ላይ በኮዴክስ ሳይናቲከስ "ኮዩ" κυ ብሎታል፥ "ኮዩ" የሚለው ቃል "ኩስ" κος ለሚለው አገናዛቢ ዘርፍ ሲሆን "ጌታችን" ማለት ነው። "ኩስ" κος የሚለው "ኩርዮስ" κύριος ማለትም "ጌታ" ለሚለው ምጻረ ቃል ነው። ቀጣዩን ልዩነት ደግሞ እንመልከት፦
2ኛ ጴጥሮስ 1፥1 የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያና ሐዋርያ የሆነ ስምዖን ጴጥሮስ፥ *በአምላካችን እና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ* ጽድቅ ካገኘነው ጋር የተካከለ የክብር እምነትን ላገኙ። ϲυμεων πετροϲ δουλοϲ και αποϲτο λοϲ ιυ χυ τοιϲ ϊϲο τιμον ημιν λαχου ϲιν πιϲτιν ειϲ δι καιοϲυνην του θυ ημων και ϲωτη ροϲ ιυ χυ

እዚህ አንቀጽ ላይ በኮዴክስ ቫቲካነስ "ቶዩ" θυ ብሎታል፥ "ቶዩ" የሚለው ቃል "ቴስ” Θς ለሚለው አገናዛቢ ዘርፍ ሲሆን "አምላካችን" ማለት ነው። "ቴስ” Θς የሚለው “ቴኦስ” θεός ማለትም "አምላክ" ለሚለው ምጻረ ቃል ነው።
ታዲያ የቱ ነው ትክክል? ስንል ኮዴክስ ሳይናቲከስ በእድሜ ኮዴክስ ቫቲካነስን በ 20 ዓመት ስለሚበልጥ የቀደመው በአንጻራዊ ተአማኒት አለው።
ሲቀጥል የ 2ኛ ጴጥሮስ ደብዳቤ ዐውደ ንባቡን ስንመለከት በኮዴክስ ሳይናቲከስ የተቀመጠው ቃል "ጌታችን እና መድኃኒታችን" τοῦ Κυρίου ἡμῶν καὶ Σωτῆρος Ἰησοῦ Χριστοῦ የሚለው ሦስት ጊዜ ሐቲታዊ ፍሰት"exegetical outline" ሆኖ መምጣቱ በራሱ የ 2ኛ ጴጥሮስ ደራሲ የኮዴክስ ሳይናቲከስ አዘጋጆች አንጻራዊ እውነታ እንዳላቸው አመላካች ነው፦
2ኛ ጴጥሮስ 1፥11 እንዲሁ ወደ ዘላለሙ ወደ *ጌታችን እና መድኃኒታችን* ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መንግሥት መግባት በሙላት ይሰጣችኋልና።
2ኛ ጴጥሮስ 2፥20 *በጌታችን እና በመድኃኒታችን* በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት።
2ኛ ጴጥሮስ 3፥18 ነገር ግን *በጌታችን እና በመድኃኒታችን* በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ።

የሚያጅበው ይህ የጴጥሮስ ድርሰት ኢፕስቴሌ ነው፥ "ኢፕስቴሌ" ἐπιστολή ማለት "ደብዳቤ" ማለት ነው። ይህ ደብዳቤ ለግለሰብ ወይም ለአጥቢያ የሚላክ ምክር እንጂ የፈጣሪ ንግግር ወይም የነቢይ ንግግር በፍጹም አይደለም።
ሲቀጥል የ 2ኛ ጴጥሮስ ደራሲ በተለምዶ "ጴጥሮስ ነው" ይባል እንጂ አብዛኛውን ለዘብተኛ ሆነ ጽንፈኛ ምሁራን በጴጥሮስ ስም የተዋሸ"Pseudepigrapha" እንደሆነ ያትታሉ፥ ጴጥሮስ የሞተው ከ 65–67 ድኅረ-ልደት በሚገመት ጊዜ ሲሆን ይህ ደብዳቤ የተጻፈው ግን ከ 100–150 ድኅረ-ልደት በሚገመት ጊዜ ነው። ዋቢ መጽሐፍ ይመልከቱ፦
Brown, Raymond E., Introduction to the New Testament, Anchor Bible, 1997, p. 767.

ስለዚህ በሥላሴ አማንያን ዘንድ "ኢየሱስ አምላክ ነው" ተብሎ ከሚጠቀሱት ተወዳጅ አናቅጽ መካከል ይህ አንቀጽ ለኢየሱስ አምላክነት ማስረጃም መረጃም አይሆንም። በሐሰት ሰነድ ቴኦሎጂን ቴኦሎጃይስ ማድረግ እጅጉኑ ሲበዛ ወጨበሬነት ነው። "ጌታ" ማለት ደግሞ "አምላክ" ማለት አይደለም፥ ምክንያቱም "አምላክ ኢየሱስን ጌታ አደረገው" ስለሚል፦
የሐዋርያት ሥራ 2፥36 አለ። እንግዲህ ይህን እናንተ የሰቀላችሁትን *ኢየሱስን አምላክ θεός ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው* የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ።

መቼም አንድ ጤነኛ የሆነ ሰው፦ "ፈጣሪን ፈጣሪ ጌታ አደረገው" ብሎ እንደማይቀበል እሙና ቅቡል ነው። ይስሐቅ ያዕቆብን ጌታ አደረግሁት ይላል፥ ዮሴፍ፦ “እግዚአብሔር ጌታ አደረገኝ” ይላል፦
ዘፍጥረት 27፥37 ይስሐቅም መለሰ ዔሳውንም አለው። እነሆ፥ *ጌታህ አደረግሁት*፥
ዘፍጥረት 45፥9 *እግዚአብሔር በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ ጌታ አደረገኝ*፤ ወደ እኔ ና፥ አትዘግይ!

"እግዚአብሔር ጌታ አደረገኝ" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት፥ ይህም ስልጣንና ሹመትን አሊያም እልቅናና ክብርን ያመለክታል። "ኢየሱስ ጌታ ተደረገ" ሲባል "ያዕቆብ ጌታ ተደረገ" አሊያም "ዮሴፍ ጌታ ተደረገ" በተባለበት ሒሳብና ቀመር እንጂ እግዚአብሔር እግዚአብሔርን ጌታ ማድረግ አያመለክትም። የኢየሱስ ጌትነት ልክ እንደ እግዚአብሔር በራሡ የተብቃቃ አሊያም የባሕርይ ገንዘቡ ሣይሆን እንደ ያዕቆብን እና ዮሴፍ በስጦታ ያገኘው ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር

ጥሪያችን በሁሉም ይገኛል
መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
291 views16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ