Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Silver
Platinum
Golden
Choleraupdate
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.37K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 147

2023-01-04 10:23:40
በ5 ወራቱ በወባ በሽታ መያዛቸው ለተረጋገጠ 1.3 ሚሊዮን ሰዎች በላይ የህክምና አገልግሎት ተሰጥቷል።

በሀገራችን የወባ በሽታ የሚከሰተው በአብዛኛው ከመስከረም እስከ ታህሳስ ወር ድረስ ዋናውን የክረምት ዝናብ ተከትሎ ነው። ከባለፉት ዓመታት ተመሳሳይ ጊዜያት ጋር ሲነጻጸር የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ስርጭት መጠን በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩ ተገልጿል።

የወባ ማጥፋት ፕሮግራም የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 5 ወር የአፈፃፀም ግምገማ በአዳማ ከተማ የተካሄደ ሲሆን በመድረኩ ህዳር መጨረሻ ያለው ሪፖርት ቀርቧል።

ሪፖርቱ እንደሚያመለክተውም 6,330,753 ለሚሆኑ የወባ ህሙማን ተጠርጣሪዎች ምርመራ ተደርጎ፤ በወባ በሽታ መያዛቸው ለተረጋገጠ 1,330,888 ሰዎች የህክምና አገልግሎት ተሰጥቷል። ይሄም ትኩሳት ኖሮባቸው ምርመራ ካደረጉ ሰዎች መካከል 21% ወባ ተገኝቶባቸዋል፡፡

የወባ በሽታን ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንጻር ከ449 በላይ በሚሆኑ ወረዳዎች እና ከ6435 በላይ ቀበሌዎች ከፍተኛና መካከለኛ የወባ ስርጭት ባለባቸው የወባ ሳምንት ንቅናቄ የተከናወነ ሲሆን የሚዲያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራም ተሰርቷል።

ከ19 ሚሊዮን በላይ አጎበር ከውጭ ተገዝቶ ወደ አገር ዉስጥ እንዲገባ በተደረገው መሰረትም የመጀመሪያው 8,367,000 አጎበር ለክልሎች ተሰራጭቷል። 1,207,897 ቤቶችን ለመርጨት ታቅዶ 96% ቤቶችን መርጨት መቻሉ ተነግሯል።

@tikvahethmagazine
12.6K viewsedited  07:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 10:22:44
የኢትዮጵያ በአምስት ወራት የወጪ ንግድ ከ1.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች።

በበጀት አመቱ ባለፉት አምስት ወራት የተለያዩ ምርቶችን ለዓለም አቀፍ ገበያ በማቅረብ ከ1 ነጥብ 528 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

በበጀት አመቱ ከውጭ ንግድ ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረው 1.899 ቢሊዮን ዶላር እንደነበር በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ቁምነገር እውነቱ ለኢፕድ ተናግረዋል።

"በዚህም የዘንድሮ የአምስት ወራት የወጪ ንግድ አፈጻጸም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ90 ሚሊዮን ዶላር ቅናሽ አሳይቷል" ብለዋል።

በአምስት ወራቱ የግብርና ምርቶች 78.4% ድርሻ ሲኖራቸው የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ 11.9%፣ የማዕድን ዘርፍ 6.3% ድርሻ የያዙ ሲሆን ከሌሎች ዘርፎች 3.43% ገቢ መገኘቱ ነው የተጠቆመው።

@tikvahethmagazine
12.1K viewsedited  07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 10:21:42
ኢትዮጵያ የትራንስፖርት ሙዚየም ልትገነባ ነው

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የኢትዮጵያን የትራንስፖርት ታሪክ፣ ወቅታዊ ገጽታና የመጪውን ዘመን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የሚያስቃኝ ሙዚየም ለመገንባት ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡

ሙዚየሙ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ዘመናት የተጠቀሟቸው ታሪካዊ ተሸከርካሪዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ የትራንስፖርት አማራጮችና ቁሳቁሶችን አካቶ የሚይዝ ሲሆን ዓለም የደረሰበትን የትራንስፖርት የዕድገት ደረጃና በዘርፉ የኢትዮጵያን የወደፊት መሻቶቿን የሚያስቃኝ እንደሚሆን ተብራርቷል።

በአዲስ አበባ አፍሪካ ህብረት አካባቢ ግንባታው በቅርቡ እንደሚጀመርም የተነገረለት ሙዚየሙ ዜጎች የሀገራቸውን የትራንስፖርት ታሪካዊ ዳራ እንዲያውቁ እንደሚያግዝና በመስኩ ጥናትና ምርምር ለሚያደርጉ አካላት ማጣቀሻ ሊሆኑ የሚችሉ ሰነዶች የሚቀርቡበት መሆኑን ከሚንስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

@tikvahethmagazine
9.6K views07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 10:20:09
#ጥቆማ

በምግብ ዋስትና ዙሪያ ለሚሰሩ ጀማሪዎች የንግድ ስራን ለማሳደግ ሥልጠና ተዘጋጅቷል። መርኃ ግብሩ የ10 ቀን የተዋቀረ ስርዓተ ትምህርት እና የ6 ወራት የቴክኒክ ድጋፍ ፣ ኢንኩቤሽን፣ ኔትዎርኪንግ እና ሌሎች ተግባራትን ያካትታል።

ምዝገባው እስከ ጥር 6 ይቆያል።

ለመመዝገብ  bit.ly/3XF7CtW

@tikvahethmagazine
8.9K viewsedited  07:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 10:19:58
ጤና ይስጥልን አያቶች ነን፣
በኢትዮጵያ #ሪል_ስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደሙ እና የዘርፈ ብዙ ድርጅቶች ባለቤት የሆነው አያት አክስዮን ማህበር በከተማችን እምብርት ካሳንችስ እና በግዙፋ ሲ ኤም ሲ ሳይታችን ለሽያጭ ካቀረበቸው ዘመናዊ አፓርትመንቶች በተጨማሪ የኩባንያውን ጥቂት አክሲዮኖች በመሸጥ ላይ ይገኛል።
እንዳያመልጥዎ
ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲኖርዎትና እስከ 44% የሚደርስ የትርፍ ክፍፍል (ዲቪደንድ) ተካፋይ ለመሆን የዚህ ግዙፍና ትርፋማ ድርጅት ባለቤት ለመሆን አሁኑኑ ይወስኑ።

በካሳንችስ ሳይታችን ከ90% በላይ ግንባታቸው የተጠናቀቁ ውስን ቤቶች ለሽያጭ የቀረቡ ስለሆነ ለመግዛት ይፍጠኑ።
አያትን የሰማ ትርፋማ!
#ለበለጠ_መረጃ:
0930653333 ላይ ይደውሉ
9.7K views07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 10:19:47
Flowers are nature's expression of LOVE
#Christmas packages
#For your love once
#For your friend
#For your family
#Preorder always recommended
Contact us on -0911359234
                         -0954882764
Adress-22 Next to axum hotel at tigat
F2-23
https://bluebell-gifts.com
https://t.me/bluebellgiftstore
10.1K views07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 18:15:40
በተከሰተው ድንገተኛ የእሣት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ስሙ ገነት ሼዶች ተብሎ በሚጠራው ቦታ ዛሬ ከቀኑ 9:40 ሰዓት በማምረቻ ሼዶች ላይ በተከሰተ ድንገተኛ የእሣት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።

አደጋው ተጨማሪ ጉዳት ከማድረሱ በፊት በቁጥጥር ሥር ማዋል የተቻለ ሲሆን፤ የአደጋው መንስኤም በመጣራት ላይ መሆኑን የክፍለ ከተማ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ አመላክቷል፡፡

በመዲናዋ ባለፈው ቅዳሜና እሁድ በደረሱ እሳትና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ማስታወቁ ይታወሳል።

@tikvahethmagazine
19.2K viewsedited  15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 18:15:15
በአራት ዓመት ህፃን ልጅ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በሃያ ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ

በሳውላ ከተማ በአራት ዓመት ህፃን ልጅ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በሃያ ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወሰነበት፡፡

ተከሳሹ ወጣት አሳቻ ሰዓት በመጠቀምና ህፃኗን ከጓደኞቿ ጋር ስተጫወት በማባበል ታህሳስ 1 ቀን 2015 ዓ.ም አስገድዶ የመድፈር ወንጀል መፈጸሙ በዐቃቤ ህግ ማስረጃዎች በመረጋገጡ ነው ውሳኔው የተላለፈበት።

የህፃኗ ወላጅ አባት አቶ አማኑኤል ዱበና በበኩላቸው አሰገድዶ የመድፈር ወንጀል የደረሰባትን ህፃን ለጤናም ሆነ ለስነ-ልቦና ጉዳት የሚዳርግ ተግባር ከመሆኑ አንጻር የሳውላ ከተማ  የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የውሳኔ አስጣጥ አስተማሪ አይደለም ብለዋል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተበራከተ የመጣውንና በህጻናት ላይ የሚደርሰው ፆታዊ ጥቃት መንግሥትና መንግታዊ ያልሆኑ ተቋማትን ጨምሮ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች  በጋራ መከላከል አለባቸው ሲሉ የሳውላ ከተማ አቃቤ ህግ ጽ/ቤት የልዩ ልዩ ወንጀል ጉዳዮች ዋና ሥራ ሂደት አሰተባባሪ አቶ ማስረሻ ሰለሞን ተናግረዋል። (ደሬቴድ)

@tikvahethmagazine
16.8K viewsedited  15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 18:15:05
እናስተዋውቆ

መኪና መግዛት እና መሸጥ ለምትፈልጉ የተከፈተ ነው! ማንኛውንም አይነት መኪና መግዛትና መሸጥ ከፈለጋቹ ከስር ያለዉን ሊንክ በመጫን ይቀላቀሉን ::

ETHIO CAR BROKER
Join
Telegram: https://t.me/ethiocar2

www.ethiocarbroker.com

በምርጫዎ ይደሰታሉ!
14.9K views15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 18:14:53
Design + Build ለሚያሰሩ ደንበኞቻችን ነፃ የዲዛይን አገልግሎት እንሰጣለን።

የምንሰጣቸው አገልግሎት
የኢንቴርየር ዲዛይን እና የፊኒሺንግ ስራ
የህንፃ ዲዛይንና ማማከር አገልገሎት
አጠቃላይ የእንጨት ስራ
የኢፓክሲ ስራ ( Epoxy Work )

Contact us  @etheldesign1
0939902740
0919361804

ኢትኤል ዲዛይን ጥራትና ውበት አንድ ላይ Ethel Design

Join Telegram: t.me/etheldesign
15.4K views15:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ