Get Mystery Box with random crypto!

መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese

የቴሌግራም ቻናል አርማ rodas9 — መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese
የቴሌግራም ቻናል አርማ rodas9 — መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese
የሰርጥ አድራሻ: @rodas9
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 37.81K
የሰርጥ መግለጫ

ትክክለኛው ቻናሌ ይሄ ብቻ ነው። በዚ ብቻ ትምህርተ ሃይማኖትንና የኢትዮጵያ ምስጢራትን ሳይንሳዊ ጉዳዮችን በጥልቀት እንዳስሳለን። ሌሎቹ ቻናሎች የእኔ አይደሉም

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-14 01:07:42
13.2K views22:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-10 23:30:08

12.7K views20:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 18:20:32 Thank you for giving us this award for our scientific presentation on April 8, 2024 total solar eclipse with Dr. Abebe, who taught physics for 35 years.
13.0K views15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 18:20:17
12.8K views15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 10:15:33 [ተጠባቂው የመጋቢት 30 ሙሉ የፀሐይ ግርዶሽ]
በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
የመላው ዓለም የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ዐይን በመላ መጋቢት 30 በሰሜን አሜሪካ የሚከሰተውን ሙሉ የፀሓይ ግርዶሽ ላይ ሙሉ በሙሉ ተተክለዋል፤ ይኽ ግርዶሽ ከተለመደው ውጪ የብዙዎችን ትኩረት የወሰደበት ምክንያት፡-

1ኛ. ግርዶሹ የሚያልፍበት መሥመር ከተለመደው ሰፋ ያለ በመኾኑ እጅግ ብዙ የሰሜን አሜሪካ ቦታዎች ይጨልማሉ ማለት ነው፡፡ ይኽ ደግሞ እጅግ ብዙ ሰዎች የሚመለከቱት ታላቅ የሥነ ፈለክ ክስተት ሊኾን መኾኑ ነው፡፡

ኦገስት 21/ 2017 (ሰኞ ነሐሴ 15, 2009) በነበረው ሙሉ የፀሓይ ግርዶሽ 12 ሚሊየን ሰዎች ተመልክተውታል፡፡ ይኽኛውን የመጋቢት 30 የፀሐይ ግርዶሽ ግን 32 ሚሊየን ሰዎች ይመለከቱታል፡፡

2ኛ. ይህ ሙሉ የፀሓይ ግርዶሽ በሰሜን አሜሪካ ላይ የመጣው ልክ በ7 ዓመቱ ነው፡፡ 7 ፍጹምነትን የሚያሳይ የሥነ ፍጥረት ቊጥር ነው፡፡ በምድሪቱ ላይ ፍጹም ክስተትና ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል እየተነገረለት ይገኛል፡፡

3ኛ. ከ7 ዓመት በፊት እ.ኤ.አ. በ2017 የተከሠተው ግርዶሽ 7 በሰላም ስም የተሠየሙ የዩኤስ ግዛቶችን አቋርጧል፤ የአሁኑ ደግሞ በነነዌ ስም፣ በዮናስና በመነጠቅ ስም የተሰየሙት የዩኤስ ግዛቶችን ማቋረጡ ልክ እንደ ነነዌ ከአርያም የተላለፈ ታላቅ የንስሐ ምልክት እንደሆነ በተለያዩ አጥኚዎች ጭምር በስፋት እየተነገረ ይገኛል፡፡

4ኛ. ግርዶሹ በአማካይ ለ4 ደቂቃ ከ28 ቅጽበት በናዛስ ሜክሲኮ መውሰዱ ነው፤ እንደ ጎርጎርዮሳዊ የዘመን ቀመር ከ2010 በኋላ ትልቁ የግርዶሽ ጨለማ ነው፡፡

5ኛ. የግርዶሹ መንገድ 3 የሰሜን አሜሪካ ሀገራትን የሚያቋርጥ ሲኾን ይኸውን ሰሜን ምዕራብ ሜክሲኮ፣ ከዚያም ወደ ዩ ኤስ ኤ፤ ከዚያም ካናዳን ጭምር ያካልላል፡፡

6ኛ. ቪነስ እና ጁፒተር በሙሉ የፀሐይ ግርዶሹ ጊዜ የመታየት ዕድል ያላቸው ሲሆን ፕላኔቶች ሰልፍ ሠርተው ከታችና ከላይ ይገኛሉ።

7ኛ. ኮሜት 12p/ pont Brooks የተባለ ጅራታማ ኮከብ በዕለቱ መታየቱ ተጠባቂ አድርጎታል።

8ኛ. ኦገስት 21/ 2017 ላይ አንድ አግድሞሽ ግርዶሹ ሲሠራ በመጋቢት 30 ደግሞ አንድ ታላቅ አግድሞሽ ይሠራል፡፡ በደቡብ ኢሊኖይ እና ምዕራብ ኪንታኪ መገናኛ አላቸው፤ እነዚኽ በ2ቱም ሙሉ ግርዶሾች የሚሠራው ቅርጽ ተ ወይም የመስቀል ቅርጽ ነው፡፡ በተጨማሪም ኦክቶበር 14 ቀለበታማ የፀሐይ ግርዶሽ ነበረ፡፡ ግርዶሹ የተጓዘበት መሥመር የኦገስት 21/ 2017 አሌፍ አ ፊደልን ሲሠራ የአሁኑ ደግሞ ተ ሠርቷልና የአሌፍ እና ታው ግርዶሽ ተብሏል፡፡

9ኛ. መጋቢት 16 ወይም ማርች 25 በሰሜን አሜሪካ ፔኑምብራል የጨረቃ ግርዶሽ (ድብዝዝ የጨረቃ ግርዶሽ) የተከሠተ ሲኾን በወሩ ውስጥ ኹለት ታላላቅ ክስተቶች መኾናቸው ነው፡፡

10ኛ. እንደ ኢትዮጵያ የሥነ ፍጥረት ሊቃውንት ዘመነ ዮሐንስ - መጋቢት 29 - እሑድ የምጽአት መታሰቢያ ሲኾን በተለይ በነጋታው ይኽ ታላቅ ጨለማ መከሠቱ ብዙ ምልክቶችን በሚገባ የሚያሳይ ሲኾን ለእስራኤል ይኽ የዘንድሮው ሙሉ የፀሓይ ግርዶሽ የወራት መጀመሪያቸው ኔሣን 1 ነው፡፡

11ኛ. 4.75 በሊየን ደላር የፈጀው በጄኔቫ ሲዊዘርላንድ ያላው 10,000 ሳይንቲስቶች፤ 100ዎች ዩኒቨርሲቲዎች የተሳተፉበት የሰርን “አጽናፈ ዓለማችንን በስውር የሚገዛውን የማይታይ ነገር ፍለጋ በሚል የዓለማችን ኃይለኛ እኑሶች አክስራሌተር ሙከራዬን በፀሐይ ግርዶሹ ዕለት መጋቢት 30 አደርጋለሁ ማለቱ መላውን የዓለም ሕዝብ እያነጋገረ ይገኛል፡፡
ብዙዎች በማኅበራዊ ሚዲያ ሰርን በዕለቱ የተሰወረ መተላለፊያ ሆን ብሎ ሊከፍት ነው እያሉ ሲገኙ ሰርን በበኩሉ አላደርገው ይህን እያስተባበለ ይገኛል፡፡ ቢሆንም ክርክሮቹ ከፍ ብለው የዓለምን ማኅበራዊ ሚዲያ ይዘውታል፡፡ እኛም በዓለም ላይ የሚመጣው አዎንታዊ ይሁን አሉታዊ ነገርን እንደ አንድ የምድሪቱ አካልነታችን መድረስ አይቀርምና ከፍ ብሎ ጉዳዩን ማየቱ አይጎዳም፡፡

12ኛ. በጉጉት ይህን ድንቅ ክስተት ለማየት የጓጉ እንዳሉ ሁሉ አብዛኞቹ የመጋቢት 30 ይህንን ክስተት በእጅጉ የፈሩት ሲሆን ከግርዶሹ በኋላ በምድራችን ላይ ታይተው የማይታወቁ ይልቁኑ በተፈጥሮ ላይ ታላላቅ ለውጦች ይመጣሉ እያሉ ሰፊ ዘገባን እየሠሩ ይገኛሉ፡፡

በዚያም ሆነ በዚህ በእኔ ምልክታም ፀሓይ ጨረቃ ዘመንን ከመሥፈር ባለፈ ለታላቅ ምልክት መፈጠራቸው የታመነ ነውና ሁኔታውን በአትኩሮት ማየት መልካም ነው፡፡

እኔም ይህን ታላቅ የተፈጥሮ ክስተት አስመልክቶ እሑድ መጋቢት 29 ከፊዚክስ ሊቁ ከዶክተር አበበ ጋር ሰፊ ጥናታዊ ጽሑፍ እጅግ ብዙ ሰዎች በተገኙበት ሙሉ ግርዶሹ በሚታይበት በቴክሳስ ዳላስ ያቀረብን ሲሆን፤ በተለይ የሕፃናቱ መገኘትና ተሳትፎ አስገራሚ ነበር። ይህም በመጪው ተረካቢ ትውልደ ላይ ያለንን ተስፋ ያለመለመ ነው። ነገም በቴክሳስ ዩኒቨርሰቲ ዪቱዲ ሰፊ የጥናታዊ ምርምር መርሐ ግብር እና ከሺዎች ጋር ግርዶሹን የመመልከት መርሐ ግብር ይኖረናል፡፡
(ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ)
13.9K views07:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 00:11:20
13.2K views21:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-05 03:24:14
13.0K views00:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-05 00:56:05
12.9K views21:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 18:37:34

12.8K views15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 14:25:50 የአምላክ እናት በዘይቱን ማርያም ከመጋቢት 24 ጀምሮ ለ3 ዓመታት የተገለጠችበት የበረከት በዓል
ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
❖ በእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን በእኛ አቈጣጠር ከ1960 ዓ.ም. ላይ ከመጋቢት 24 ጀምሮ በካይሮ ባለችው በዘይቱን ማርያም የብርሃን እናቱ የቅድስት ድንግል ማርያም መገለጥ ይታሰባል። የአምላክ እናት በዘይቱን ማርያም የመጀመሪያው መገለጧ የተደረገው መጋቢት 24 ሲኾን ብርሃንን ለብሳ በጉልላቱ ላይ ተገልጣ በታየች ጊዜ ወደ 250,000 የሚጠጉ የሚያምኑም የማያምኑም ሕዝቦች ተሰብስበው በታላቅ ደስታና ምስጋና ያን አስደናቂ መገለጥ ይመለከቱ ነበር፡፡

❖ ከአንድ ሳምንት በኋላ ሚያዝያ 1 በድጋሚ በታላቅ ብርሃን ታጅባ በታላቅ ግርማ ተገለጠች፤ ከዚያም በኹለት ሳምንት በሦስት ሳምንት ልዩነት በታላቅ ብርሃን እየታጀበች በመገለጥ እስከ 1963 ዓ.ም. ድረስ ለሦስት ዓመታት ታይታለች፡፡

አስደናቂው የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን በዚህ ሊንክ ይመልከቱ



❖ ንግሥታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቤተ ክርስቲያኑ ጉልላት ላይ ስትገለጥም ለ2 ሰዓታት ከዚያ የበለጠ ሰዓትም ትታያቸው ነበር፤ መላእክትም በአርአያ ብሩሃን አርጋብ ዙሪያዋን ክንፋቸውን ዘርግተው ሲመላለሱ ይታዩ ነበር፤ ሌላው አስደናቂ የነበረው ክስተት እንደ ዕንቊ ፈርጥ የመሰሉ አስደናቂ ብርሃናት በዙሪያዋ ይፈስሱ ነበር።

❖ ይልቁኑ እጅግ አስደናቂ ቀይ ሕብረ ብርሃናማ ደመና በዙሪያዋ ከብቧ ነበር፤ ልዩ መዐዛ ያለው ዕጣንም በእጅጉ ይሸት ነበር፤ የታመሙትም በእንዲኽ ባለ ክብር በምትገለጥ ጊዜ ከሕመማቸው ይፈወሱ ስለነበር ኹሉም የታመመ ይመጣ ነበር፡፡ ይኽ የተገለጸችበት የዘይቱን ማርያም ቤተ ክርስቲያን እመቤታችን ጌታን ይዛ በተሰደደች ጊዜ ያረፈችበት የተቀደሰ ቦታ እንደነበር የኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን አባቶች ያስተምራሉ፡፡

❖ በዚያን ጊዜ የነበሩት የግብጽ ፓትርያርክ በቅድስና ሕይወታቸው በጣም የታወቁት አቡነ ቄርሎስ ነበሩና ከብፁዓን አባቶች ጋር የእመቤታችን መገለጽ አማናዊ መኾኑን በዐይናቸው በማየት በጸሎት በሱባዔ በመታገዝ አረጋግጠው ሚያዝያ 26 በይፋ መገለጧን የሚያረጋግጥ ጽሑፍን ጽፈዋል፡፡ ይኽ መገለጧ በመላው ዓለም በመሰማቱ የሮም ቤተ ክርስቲያን ልዑካንን በዚኽ ጉዳይ ወደ እስክንድርያ በመላክ አረጋግጣለች፡፡

❖ ይኽነን በግብጽ በዘይቱን ማርያም የመገለጧን ነገር ምስክርነት በጊዜው የግብጽ ፕሬዝዳንት የነበሩት ጀማል አብደል ናስር ጭምር ያረጋገጡ ሲኾን በግብጽ ቴሌቭዥን በዜና አውታሮች ኹሉ ሲተላለፍ ነበር፡፡ ይኽነን መገለጧን በሚሊየን የሚቈጠሩ የኮፕቲክ ክርስቲያኖችና ሌሎች የእምነት ተከታዮችና ኢአማንያን ጭምር አይተው ምስክርነታቸው ሰጥተዋል።

❖ የመገለጧን 50ኛ ዓመት ግንቦት 4 2010 ዓ.ም. ላይ የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓልን ፓፕ ታዎድሮስ 2ኛ ሥርዐተ ቅዳሴውን ራሳቸው በመምራት ያከበሩ ሲኾን እጅግ ብዙዎች ካህናትና የግብጽ ክርስቲያኖች በዓሉን አድምቀውት ነበር፡፡

በመገለጧ ጊዜ የነበረውን ክስተት በዚኽ የ YouTube ሊንክ ይመልከቱ



❖ ጥንት የነበሩት የኢትዮጵያ ሊቃውንት የእመቤታችንን መገለጥ ይጽፉ ነበር፤ አባ ጽጌ ድንግልም አስቀድማ በደብረ ምጥማቅ በታላቅ ክብር ተገልጻ ለምእመናን የታየችው የአምላክ እናት ለርሱም ትገለጽለት ዘንድ በማሕሌተ ጽጌ መጽሐፉ ላይ፡-

“አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኀምሰ ዕለታተ
ትእምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ
ሚ መጠነ ማርያም ታሥተፌሥሒ ትፍሥሕተ
ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሑ መዓልተ
ብፁዕ ዘርእየኪ በሕልሙ ሌሊተ”
(የፊትሽን መልክ ያይ ዘንድ የሞተ ሰው እስኪነሣ ድረስ በደብረ ምጥማቅ ለዐምስት ቀናት ያኽል በተገለጽሽ ጊዜ ማርያም ምን ያኽል ደስ ታሰኚ ኖሯል! በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ምስጉን ነው) በማለት ተማፅኗታል፡፡

❖ የእመቤታችን ታማኝ ወዳጅ አባ ጽጌ ድንግል በተመስጦ በመኾን እጅግ ድንቅ የኾነችውን የአምላክን እናት ሥዕል ካየ በኋላ ይኽነን የምስጋና ቃላት ለርሷ ያቀርባል፡-

“ሥዕልኪ ጽግይተ ላሕይ ዘከመዝ ትኤድም በዓለም
እፎ ይሤኒ በሰማይ ላሕየ ገጽኪ ማርያም
ሐሤተ ትእምርትኪ እጽገብ አስተርእዪኒ በሕልም
እስመ አውዐየኒ ነደ ፍቅርኪ ፍሕም
አጥፍኦቶ ዘኢይክል ዝናም”
(ማርያም ሥዕልሽ በዓለም እንዲኽ የምታበራ ከኾነ በሰማይ የፊትሽ መልክ ምን ያምር! አንቺን ከማየት የሚገኘውን ደስታ እጠግብ ዘንድ በሕልም ተገለጪልኝ፤ ዝናብ ሊያጠፋው የማይቻለው የፍቅርሽ እሳት አንድዶኛልና) ብሏል፡፡

❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም ይኽነን መገለጧን በእንዚራ ስብሐት መጽሐፉ ላይ፡-
“ኦ ንግሥት ይገንዩ ለኪ ነገሥት ወለኪ ንግሥታት ይትቀነያ
ወኪያኪ የአኲታ ወለስምኪ ይገንያ
ወለኪ ይሰግዳ ወለክብርኪ የሐልያ
ጢሮስ ወሲዶና ሰብአ ግብጽ ወኢትዮጵያ
ፊንቂ ወሮምያ ማሮን ወአርማንያ
በሥነ ጸዳልኪ ይትፌሥሓ ወበላሕይኪ ይትሐሠያ”

(ንግሥት ሆይ ነገሥታት ለአንቺ ያገለግላሉ፤ ንግሥታትም አንቺን ያመሰግናሉ፤ አንቺንም ያሞግሳሉ፤ ለስምሽም ያጐነብሳሉ፤ ለአንቺ የጸጋ ስግደትን ይሰግዳሉ፤ ለክብርሽም ምስጋናን ያቀርባሉ፡፡ ጢሮስና ሲዶና የግብጽና የኢትዮጵያ ሰዎች፣ ፊንቄና ሮምያ፣ ማሮንና አርማንያ በወጋገንሽ ውበት ደስ ይሰኛሉ፤ በደም ግባትሽም እሰይ ይላሉ) በማለት ገልጦታል፡፡

❖ የመልክአ ማርያም ደራሲም የአምላኩን እናት ቅድስት ድንግል ማርያምን ፊቷን ለማየት ሽቶ በናፍቆት ኾኖ፡-
“ሰላም ለመልክእኪ ዘተሠርገወ አሜረ
ዘያበርህ ወትረ
ፍቅርትየ አንቲ እንተ ታበድሪ ፍቅረ
አርእዪኒ ገጸ ዚኣኪ ማርያም ምዕረ
ዘኢይሰምዖ ካልእ እንግርኪ ነገረ”
(ኹልጊዜ (ዘወትር) የሚያበራ ፀሓይን ጌጥ ላደረገ መልክሽ ሰላምታ ይገባል፤ ፍቅርን የምትመርጪ (የምታስቀድሚ) አንቺ ፍቅረኛዬ ማርያም ሌላ የማይሰማው ነገርን እነግርሽ ዘንድ አንድ ጊዜ ያንቺን ፊት ግለጪልኝ) በማለት ተማፅኗታል፡፡

❖ የአምላክ እናት ሆይ አስቀድመሽ በደብረ ምጥማቅ በኋላም በዘይቱን ማርያም ተገልጠሽ በረከትን እንዳትረፈረፍሽላቸው ዛሬም ለእኛ ለምንወድሽ ለልጆችሽ ትገለጪልን ዘንድ እንማፀንሻለን፡፡ በዓለም ላይ የመጣውን መቅሠፍት ከልጅሽ አማልደሽ አርቂልን እኛ ልጆችሽንም በቃል ኪዳንሽ ጥላ ከጥፋት ሠውሪን።
[ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ]
12.7K views11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ