Get Mystery Box with random crypto!

አገልግል

የቴሌግራም ቻናል አርማ ourmereja — አገልግል
የቴሌግራም ቻናል አርማ ourmereja — አገልግል
የሰርጥ አድራሻ: @ourmereja
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.21K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-03-23 13:42:36
#ትግራይ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ፕሬዝደንት አድርገው ሾሙ
በትግራይ በተቋቋመው ግዚያዊ አስተዳደር በእጩነት ዶ/ር ደብረጽዮን በቅድሚያ ቀርበው ውድቅ ያደረገው የፌደራል መንግስቱ የጌታቸው ረዳን እጩ ፕሬዝዳንትነት መቀበሉን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አሳውቋል።
318 viewsedited  10:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 06:41:30
#ሰበር ቀልድ (ቀንድ)
አዲሱ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር አቶ ጌታቸው ረዳን የሽግግር መሪ (ፕሬዚዳንት) አድርጎ ሾሙዋል። ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በፌደራል መንግሥቱ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል። ጌታቸው ረዳ በአብላጫ ድምፅ ተመርጧል።
290 views03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 06:31:10 በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ለሰራተኞቻቸው ደመወዝ መክፈል ሊጀምሩ ነው ተብሏል
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ለሰራተኞቻቸው ደመወዝ ለመክፈል በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ አስታወቁ።የገንዘብ ሚኒስቴር ለሰራተኞች ውዝፍ ደመወዝ መክፈያ እና የአንድ ወር የስራ ማስኬጃ በጀት፤ ባለፈው አርብ መጋቢት 1፤ 2015 እንደፈቀደላቸው ዩኒቨርሲቲዎቹ ተናግረዋል።

ተጠሪነታቸው ለፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር የሆኑ አራት ዩኒቨርስቲዎች በትግራይ ክልል ይገኛሉ። በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ምክንያት የመማር ማስተማር አገልግሎታቸውን አቋርጠው የሚገኙት እነኚህ አራት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፤ የመቐለ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርስቲዎች ናቸው።

የመቐለ፣ አክሱም እና ራያ እና ዩኒቨርሲቲ አመራሮች፤ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ምክንያት ላላፉት 20 ወራት በዩኒቨርሲቲዎቹ ለሚሰሩ ሰራተኞች ደመወዝ አለመከፈሉን ገልጸዋል። ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራር፤ የሰራተኞችን ውዝፍ ደመወዝ ጉዳይ ከገንዘብ ሚኒስቴር አመራሮች ጋር በነበራቸው ስብሰባ ወቅት ገልጸዋል።

በዚሁ ስብሰባ ላይ የሚኒስቴሩ ኃላፊዎች፤ “ ‘ሌላውን የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኛም ግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ መንግስት ውሳኔ የሚሰጥበት ይሆናል’ የሚል ምላሽ መስጠታቸውንም አስታውሰዋል። የዚሁ ስብሰባ ተሳታፊ የነበሩት የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕ/ር ገብረየሱስ ብርሃነ በበኩላቸው፤ “መንግስት በልዩ ሁኔታ የሚወስነው ውሳኔ እንዳለ ነው የተነገረን” ሲሉ የሰራተኞች ውዝፍ ደመወዝን በተመለከተ ጉዳዩ ከሚመለከተው የፌደራል ተቋም የቀረበውን መልስ ጠቅሰዋል።

የገንዘብ ሚኒስቴር ይህ ስብሰባ በተካሄደ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ባሳለፈው ውሳኔ፤ የዩኒቨርስቲዎቹ ሰራተኞች ደመወዝ እንዲከፈል በጀት መልቀቁ ታውቋል። የፌደራል ተቋማት ለሆኑት አራቱ ዩኒቨርስቲዎች ሰራተኞች የደመወዝ ክፍያ የሚሆን ገንዘብ መተላለፉን የገንዘብ ሚኒስቴር ምንጮች አረጋግጠዋል። “የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ገና ስላልተመሰረተ፤ ለክልሉ የተላከ ገንዘብ የለም” ሲሉም የሚኒስቴሩ ምንጮች አክለዋል።
375 views03:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 14:30:30
#መቐለ_ዩኒቨርሲቲ

" ተማሪዎቻችንን እንደገና ለመቀበል ዝግጁ ስንሆን ይፋዊ መግለጫ እንሰጣለን " - ዶ/ር ፋና ሀጎስ (የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት)

ከትላንት ምሽት አንስቶ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች መቐለ ዩኒቨርሲቲን የሚመለከቱ መረጃዎች እየተሰራጩ ይገኛሉ።

እነዚህ መረጃዎች ፦
- ዩኒቨርሲቲው ወደ መማር ማስተማር ስራው እዲመለስ መወሰኑ፣
- በጦርነቱ አቋርጦ የነበረውን ስራ ከመጪው ሳምንት አንስቶ እንደሚጀምር፣
- በመንግስት በኩል አስፈላጊው #በጀት እንደተለቀቀለት፣
- 24 ሺህ ነባር ተማሪዎችን በቀጣይ 4 ወር ትምህርት እንዲያጠናቅቁ እንደሚያደርግ
- ከመስከረም 2016 ጀምሮ አዲስ ተማሪዎችን እንደሚቀበል የሚገልፁ ናቸው።

ነገር ግን ይህ የተሳሳተ መረጃ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ገልጸዋል።

መቐለ ዩኒቨርሲቲም ቢሆን በይፋዊ የፌስቡክ እና የትዊተር አካውንቱ ላይ ምንም አይነት መረጃ አልለጠፈም።

የተሰራጨውን መረጃ በተመለከተ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋና ሀጎስ ለ" ኢትዮጵያ ቼክ " መረጃ ማጣሪያ ድረገፅ በሰጡት ቃል ፥ ዩኒቨርሲቲው ስራ ለመጀመር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እየሰራ ቢሆንም በዩኒቨርሲቲው ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን የራሱን ጊዜና ሂደት እንደሚወስድ ተናግረዋል።

ዶ/ር ፋና " ዩኒቨርሲቲው ሥራውን ይጀምራል ነገር ግን በሚቀጥለው ሳምንት አይደለም ፤ በእርግጥ ይህን ለማድረግ ወራትን ይወስዳል " ሲሉ ተናግረዋል።

ዶ/ር ፋና እስካሁን መቐለ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ጥሪ እንዳላደረገ ገልፀው " እኛ (ዩኒቨርሲቲው ወይም የትምህርት ሚኒስቴር) ተማሪዎቻችንን እንደገና ለመቀበል ዝግጁ ስንሆን ይፋዊ መግለጫ እንሰጣለን " ሲሉ አሳውቀዋል።

Credit : ethiopiacheck.org
618 viewsedited  11:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 09:49:13
መቀሌ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዛሬው ዕለት በመቐለ ከተማ በሚገኙ ሁሉም ቅርጫፎቹ አገልግሎት መሰጠት ጀመረ
262 views06:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 18:14:31 12ኛ ክፍል ፈተናውን በትክክል ከወሰዱት 896,520 ተማሪዎች ውስጥ ከግማሽ በላይ ያመጡት፤ 29,909 ናቸው።

ትምህርት ሚንትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
266 views15:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 21:36:03 ለ2014 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ተፈታኞች በሙሉ
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት የተለቀቀ በመሆኑ ተፈታኞች ከዛሬ ጥር18 2015 ዓ.ም ከሌሊቱ 5፡30 ጀምሮ፡-
• በዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ወይም
• በ6284 አጭር የጽሑፍ መልዕክት መላኪያ ላይ የምዝግባ ቁጥራቸውን (Registration Number) ብቻ በመላክ ወይም
• በቴሌግራም ላይ  https://t.me/eaesbot
ማየት የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-
• ማንኛውም ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በአካል መምጣት ሳያስፈልግ እስከ ጥር 26/2015 ዓ.ም ድረስ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ላይ Compliant የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማቅረብ ይችላሉ፡፡
• የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አድራሻ ላይ ብቻ ይጠቀሙ፡፡ ከተመሳሳይ እና የተዛባ መረጃ ለማሰራጫት ከሚሞክሩ አካላት ራስዎን ይጠብቁ፡፡
388 views18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 21:23:28 ከ2014 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የማለፊያ ውጤት ያመጡት ሦስት በመቶ ብቻ ናቸው
ኩረጃን ለማስቀረትና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚል፣ በልዩ ሁኔታ ከተሰጠው የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ የመልቀቂያ ፈተና ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት (የማለፊያ ነጥብ) ያገኙ ተማሪዎች 28 ሺሕ ብቻ መሆናቸውን ታውቋል፡፡

ለመጀመሪያ ጊዜ በዩኒቨርስቲ በተሰጠው ፈተና ከ980 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን፣ ወደ ዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጡት ተማሪዎች 28 ሺሕ ገደማ መሆናቸው ከትምህርት ሚኒስቴር ምንጮች ለማወቅ ተችሏል።፡

ከፍተኛ ጥያቄ የሚነሳበትን የትምህርት ጥራት ለማሻሻል እና የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ላይ የሚስተዋለውን ኩረጃ ለማስቀረት ወሳኝ ነው የተባለለት ፈተና በጥብቅ ቁጥጠር ከ50 በሚበልጡ የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች መሰጠቱ ይታወቃል፡፡

የፈተና ውጤቱ ከዛሬ እኩለ ሌሊት ጀምሮ በበይነመረብ ይፋ እንደሚደረግ፣ ተማሪዎችም በተሰጣቸው የመለያ ቁጥር ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ የአዲስ ማለዳ ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡ በውጤቱ ላይ ትምህርት ሚኒስቴር በነገው ዕለት መግለጫ እንደሚሰጥም ይጠበቃል፡፡

የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ቁጥር፣ ዩኒቨርስቲዎች ካላቸው የመቀበል አቅም ጋር በፍፁም እንደማይጣጣም መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች 130 ሺሕ በላይ ተማሪዎችን የመቀበል አቅም እንዳላቸው የትምህርት ሚኒስቴር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ይህም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ካላቸው የቅበላ አቅም የ2014 ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ያስመዘገቡት ከዩኒቨርሲቲዎቹ የመቀበል አቅም ከ20 በመቶ የማይበልጥ ነው ማለት ነው፡፡

ከፍተኛ የተማሪዎች ውጤት ማሽቆልቆል ማጋጠሙን የመንግሥት ከፍተኛ ኃላፊዎች የሰሙ ሲሆን፣ ያጋጠመውን የተማሪዎች ውጤት ማሽቆልቆል ምን ይደረግ በሚለው ላይ ምክክር እየተደረገበት ነው፡፡ በውይይቱ የዩኒቨርስቲዎች መቀበል የሚችሉት አቅም ጋር የሚጣጣም ተማሪ፣ ወደ ዩኒቨርስቲ ሊገባ የሚችልበት ሁኔታ ላይ ውሳኔ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡

የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ቁጥር አነስተኛ መሆኑንን ተከትሎ፣ ዩኒቨርስቲዎች በመቀበል አቅማቸው ልክ ተማሪዎችን እንዲቀበሉ አማራጭ እየተፈለገ ነው፡፡ በዚህም በልዩ ሁኔታ ለማለፊያ የቀረበ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን የማጠናከሪያ ትምህርት ወስደው ወደ ዩኒቨርስቲ እንዲገቡ ይደረግ የሚለው አንዱ አማራጭ ሆኖ በመንግሥት በኩል እየታዬ መሆኑ ታውቋል፡፡ በተማሪዎቹ ውጤት ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት እንዲያውቁት የተደረገ እንደሆነ ማወቅ ተችሏል፡፡

የ2014 የ12ኛ ክፍል ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች መሰጠቱ፣ በትምህርት ስርዓቱ ላይ ያለውን ስብራት ለማከም እንደ አንድ የመፍትሔ አቅጣጫ ተወስዷል፡፡ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግበራዊ የተደረገው የፈተና ስርዓት፣ በዩኒቨርስቲ መምሀራን አማካኝነት፣ ተማሪዎችም ከተማሩበት አካባቢ ርቀው በዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢዎች ውስጥ የተሰጠ ነበር፡፡
423 views18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 18:10:03 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤት በዚህ ሳምንት እንደሚገለፅ ተሰምቷል።ተማሪዎች ውጤታቸውን በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።ከዛሬ ሰኞ እስከ መጭው ቅዳሜ ባለው ጊዜ ውስጥ ይፋ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ጥር 15/2015 ዓ.ም
586 views15:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 17:47:11
መቀሌ

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የፌደዴል ተቋማትን ለመጠበቅ መቀሌ ገባ

በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት መሠረት በኢፌዴሪ መንግስት የሚተዳደሩ ተቋማትን ለመጠበቅ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በዛሬው ዕለት ትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ገብቶ ሥራ መጀመሩን አስታወቀ፡፡

መንግስትና ህወሓት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የደረሱባቸውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በትግራይ ክልል የሚገኙ በኢፌ ፌዴሪ መንግስት የሚተዳደሩ አውሮፕላን ማረፊያዎች፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የቴሌኮም አገልግሎት፣ የባንክና ሌሎች ለህብረተሰቡ አገልግሎት የሚሰጡ የፌደራል ተቋማት አስተማማኝ ጥበቃ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ቀደም ብሎም በትግራይ ክልል አካባቢዎች በመግባት ህብረተሰቡን በማረጋጋት ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ በማድረግ የፀጥታና ደህንነት የማስከበር ስራዎችን እየሰራ መቆየቱ ይታወቃል።
360 views14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ