Get Mystery Box with random crypto!

ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ

የቴሌግራም ቻናል አርማ nikuyebetekerstiandemtsi — ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ
የቴሌግራም ቻናል አርማ nikuyebetekerstiandemtsi — ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ
የሰርጥ አድራሻ: @nikuyebetekerstiandemtsi
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.87K
የሰርጥ መግለጫ

ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ
የዩቲዩብ ቻናሉን ምዕመናን ሰብስክራይብ ያድርጉ የበለጠ ጠንክረን እንድሰራ ይረደናል
https://www.youtube.com/channel/UCYc6W7aFPzYIkK0F1a4VSlQ
ማንኛውንም መረጃ በዚህ ማድረስ  ትችላላችሁ
@Nikutewahedo
@Niku_tewahedo

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-02-20 17:41:41
የዛሬ 61 ዓመት የጀርመን ፍራንክፈርት ዩኒቨርስቲ በጋሞ ዞን ብርብር ማርያም ገዳም ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በስርዓተ ቅዳሴ ላይ ሲያገለግሉ ለታሪክ ያስቀረው ፎቶ ግራፍ ነው
***

በ1954 ዓ. ም የዛሬ 61 ዓመት ወደ ኃላ ስትጓዝ ጋሞ ዞን የሊቃውንተ ቤተክርስቲያን መፍለቂያ ነበር።

ብርብር የምትባለው ስፍራ ደግሞ የእነዚህ ሊቃውንት መፍለቂያ ምንጭ ነበረች።

ደገኛው የጋሞ ገበሬ ደግሞ በእውቀት እና በፍቅሩ "ሊቃውንት" ተብሎ የሚጠራበት ወርቃማው ዘመን ነበር።

የዛሬን አያድርገው እና...

በነገራችን ላይ እዚህ የቴሌግራም ቻናል ላይ

ስለብርብር ማርያምን   ሙሉ ታሪኩን  እያቀረብ ነው ማንበብ ትችላላችሁ


https://t.me/Orthodox_sibket/244
1.8K views14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 17:28:42
ባለሣር ክዳኗ ቤቴልሔምና ባለቆርቆሮዋ መቅደስ እንዲህ ወዳማረበት ህንጻ መቅደስ የተሸጋገረው የጉምጉምታ ልደታ ለማርያም መቅደስ
***

እግዚአብሔር ይመስገን !!!

የዛሬ አንድ ዓመት ገደማ ....ባለሣር ክዳኗን ቤቴልሄም እና ከጎርፍ ጋር ከምትታገለው ባለቆርቆሮዋን መቅደስ የሆነችውን በቦረዳ ወረዳ ቤተክህነት ውስጥ የምትገኘውን ጉምጉምታ ለማርያም እንታደግ ዘንድ በእንተ ማርያም ብለን ተማጽነንን ነበር።

በሁለት ዙር የልመና መርኃግብርም ከ400ሺ ብር በላይ አሰባስበን ። ብርቱው የህንጻ አሰሪ ኮሚቴ ተጨማሪ ገንዘብ በማሰባሰብ እንዲህ ያማረ የልደታ ለማርያም መታሰቢያ ህንጻ መቅደስ አንጸው በቀን 27/05/15 ዓ.ም አስመርቀዋል።

ለሰጪዎች እግዚአብሔር ይስጥልን ፣ ለለፉትም ልፋታቸውን የነፍስ ዋጋ አድርጎ ይቀበልልን

ለሰጪዎችም ቅዱስ እግዚአብሄር ቸርነትን ያድርግልን !!!
1.6K views14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 07:51:10
2.2K views04:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 20:53:11
የአቡነ እስጢፋኖስ ሀገረስብከት የሆነችው ኮንታ በአከባቢ ቋንቋ አገልግሎት 33 ነፍሳት ወደ ቅድስት ቤተክርስትያን በረት ተቀላቀሉ።
***

ከጅማ በኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፓሊስ እንዲሰደዱ የተደረጉት አረጋዊው ጳጳስ ብጽኡ አቡነ እስጢፋኖስ በአባትነት እረኝነት እየመሩት የሚገኘው የኮንታ ወረዳ ቤተክህነት

በኮንተኛ ቋንቋ ባደረገው ሐዋርያዊ አገልግሎት እነሆ 33 ነፍሳት ወደ ቅድስት መቅደሳችን ተቀላቅለዋል።

በወረዳው ባለፉት 3 ሳምንታት ተከታታይ የጥምቀት ድል የተገኘበት ነው።

እግዚአብሔር ይመስገን
2.6K views17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 15:19:51
በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የቅድስት ሥላሴ ልጆች ማኅበር በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ከተማ በሕገ ወጥ መልኩ የተተሾሙ ግለሰቦች ባስነሱት ብጥብጥ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች እርዳታ አደረገ ።
ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ተጎጂዎችን በማጽናናት ላይ ይገኛሉ።
ሰናይት ባንተ
(ኢኦተቤ ቴቪ የካቲት ፲፪ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ሻሸመኔ)
በሻሸመኔ ከተማ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን ምዕመናን ላይ በሕገ ወጥ መልኩ የተተሾሙ ግለሰቦች ባስነሱት ብጥብጥ እና በእነርሱ አቀነባባሪነት በተወሰደው የግፍ እርምጃ ለተጎዱ ወገኖች በሀዋሳ ከተማ በአላቲዎን እና ያኔት ሆስፒታል በመገኘት የጉዳት መጠናቸውን ተመልክቶ የአንድ ሚሊየን ብር (1,000,000 ) ድጋፍ አድርጓል ።
በሀገረ ስብከቱ በኩል ለተዋቀረው የእርዳታ ኮሚቴም 450,000 ብር ድጋፍ አድርጓል ።
በጸጥታ ኃይሎች እና ወረበሎች በግፍ በአጣና ተቀጥቀጠዉ በሰማዕትነት ላለፉት ለቄስ ሐረገወይን ባለቤት የሁለት መንታ ልጆች እናት ምንም እንኳን በቂ ባይሆንም ለጊዜዉ ለችግር መሸፈኛ የሚሆን የ 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ) ብር ድጋፍ አድርገዋል። በድምሩ ለ25 ሰዎች የ 350,000 ( ሶስት መቶ ሀምሳ ሺህ ብር) ገቢ አድርገዋል። የእርዳታው አስተባባሪዎች ይህ ገንዘብ ለሰዉነት መጠገኛ የምግብ እና የመሳሰሉትን ጥቃቅን ነገር ይሸፍንላቸዉል ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ ክልል ጌዴኦ አማሮና ቡርጂ እና የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሆስፒታል ተኝተው ህክምና የሚከታተሉ ወገኖችን ጎብኝተው አጽናንተዋቸዋል ።
ጉዳቱ ከደረሰበት ጀምሮ ምግብ በማቅረብና የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ለተባበሩ ለሀዋሳ ከተማ ኦርቶዶክሳውያንም ምዕመናንም ብፁዕነታቸው ታላቅ ምስጋና አቅርበዋል።
EOTC TV
817 views12:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 09:45:18 “ጾምን አውጁ” (ኢዩ.፪፥፲፭)

እንኳን ለዐቢይ ጾም አደረሰን!

በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ከሚታወጁት ሰባት አጽዋማት መካከል ታላቅ ለሆነው ለዐቢይ ጾም ስላደረሰን አምላካችን እግዚአብሔር ምስጋና ይድረሰው!

ዐቢይ ጾም ማለት ምን ማለት ነው?

በመጀመሪያ ‹‹ዐቢይ›› የሚለው ቃል ‹‹አበየ›› ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው፡፡ ትርጓሜውም ‹‹ከፍ አለ›› ማለት ነው፡፡ ጾሙም ዐቢይ የተባለበት ሦስት ዓበይት ምክንያቶች አሉት። የመጀመሪያው ጌታቸን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ የጾመው ስለሆነ ነው፡፡ (ማቴ.፬፥፫-፫) በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት ስለ ሚበልጥና የቀኑ ብዛትም ፶፭ ቀንም ነው፡፡ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች እንዲሁም ደግሞ ሦስቱ ርእሰ ኃጢአት (ትዕቢት፣ ስስት ፍቅረ ነዋይ) በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ድል የተመቱበት በመሆኑ ዐቢይ (ታላቅ) ጾም ተብሏል፡፡ (ማቴ.፬፥፫-፲፩)፡፡

የዐቢይ ጾም ስያሜዎች

ዐቢይ ጾም ከቀኑ ርዝማኔ በተጨማሪ የተለያዩ ስያሜዎች አሉት፡፡
ጾመ ሁዳዴ፡- ሁዳድ ማለት ሰፊ (ትልቅ) የእርሻ ቦታ ማለት ነው፡፡ በሰፊ እርሻ የተመሰለበት ምክንያት የቀኑ ብዛት ከሌሎች አጽዋማት ስለሚበዛ ነው፡፡

የካሣ ጾም፡- አዳምና ሔዋን በዲያቢሎስ ግዞት እያሉ ክርስቶስ ደሙን በመክፈል (በመካስ) ነጻ ስላውጣቸው የካሣ እየተባለ ይጠራል፡፡

የድል ጾም፡- ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ጾም ሰይጣንን ድል ያደረገበት በመሆኑ የድል ጾም ተብሏል፡፡

ጾም አስተምህሮ፡- ዐቢይ ጾም ‹‹ጾም አስተምህሮ›› የተባለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማስተማር የጾመው በመሆኑ ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር የተለያዩ ስያሜዎች አሉት፡፡

የዐቢይ ጾም ሳምንታት

ዐቢይ ጾም በያዘው በ፶፭ ቀኑ ውስጥ ሰባት ቅዳሜና ስምንት እሑዶቸን ይዟል፤ የእነዚህ የስምንቱ እሑዶች የተለያየ ስያሜ አላቸው፡፡ ስያሜአቸውንም የሰጣቸው የቤተ ክርስቲያናችን የዜማው ሊቅ የሆነው ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ ዘወረደ፣ ቅድስት፣ ምኩራብ፣ ደብረዘይት፣ ገብረ ኄር፣ ኒቆዲሞስ ፣ መፃጉዕ፣ ሆሣዕና ናቸው፡፡

፩ኛ. ዘወረደ፡- በመጀመርያው ሳምንት ዘወረደ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት መውረዱን፣ ከአመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን እና እኛን ማዳኑን በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሚወሳበትና የሚዘከርበት ወቅት ሲሆን ይህንንም የሚዘክሩ መዝሙሮች ይቀርባሉ፤ ትምህርቶች ይሰጣሉ፤ ይህንንም እያሰብን ጾሙን እንጾማለን፡፡
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ለሐዋርያት እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን በሥርዓቱ ጹመን እንዲንጠቀም እርዳን፤ አሜን!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
1.6K views06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 23:50:53 ዕለት ዕለት የሚያስጨንቀኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሐሳብ ነው።
፪ ቆሮንቶስ ፲፩ ፣ ፳፰


እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን
637 views20:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 23:46:52
ውግዘቱ ይነሳልን ልመና
...
EX ኤዎስጣቴዎስ በትምህርት ከሁለቱ አማጺ ጳጳሳት የተሻሉ ናቸው። የአብነት ትምህርትም አላቸው ቴዎሎጂም ተምረዋል። እና ውግዘት Excommunication ምን እንደሆነ በሚገባ ያውቁታል። በእርግና እድሚያቸው ተወግዘው ከቤተክርስቲያን ህብረት መለየት ጾኑ ህመም ነው። ያውም በቅዱስ ሲኖዶስ መገዘት ትርጉሙን ይረዱታል።
ሁለቱ እንኳን እንዲሁ የኦሮሞ ጳጳስ ኮታ ይሙላ በሚል ነው የተሾሙ የረባ ትምህርት ሳይኖራቸው። በተለይ ሳዊሮስ ከዲያቆንነት በዓመት ልዩነት ውስጥ ነው አመንኩሰው ያጰጰሷቸው 97 ዓ.ም ላይ።

ኤዎስጣቴዎስ እንደዛ አይደሉም ተምረወል። ተግባራቸውን ብኮንንም እውቀታቸውንና ትምህርታቸውን አልክድም። ለዛም ነው ውግዘቱ ይነሳልን ልመና ላይ ያሉት።
...
ከጠ/ሚ አብይ ጋር በነበረው ውይይት ቅድሚያ ውግዘት ይነሳል ልመናው። ከዛም በዃላ በመጥፎ ተግባራቸው ላይ ሆነውም እንኳ ውግዘቱ ይነሳል ልመና ላይ ያሉ። በቅዱስ ሲኖዶስ ተገዝተዋል ታስረዋል። ማለትም በሰማይም በምድርም የታሰሩና የተረገሙ ሆነዋል። ይህ በሃዋሪያዊ ጽኑ ስልጣን የሆነ ነው።
675 views20:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 23:44:55
614 views20:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 23:44:51 ዝም ትልና ከእውነት ጋር ለመቆም መረጃ ትሰበስባለህ ከዛም እንደዚህም አለ ትልህ እና ለህዝብ ታወራለህ


የኦሮሞን ገበሬ ንቀው አሜሪካ 17 ዓመት ያሉት ሰው፤

Ex ኤዎስጣቴዎስ 1997 ዓ.ም ለኦሮሞ ኦርቶዶክሳዊያን እንዲያገለግሉ ከተሾሙት 9 ኦሮሞ ጳጳሳት መካከል አንዱ የነበሩ ሲሆን። የተመደቡትም ኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ነበር፡፡

የተመደቡበትን ሀገረ ስብከት (ኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሐረርጌ) ላይ 1 ዓመት እንኳን ሳይቆዩ ትምህርት ልማር ይፈቀድልኝ በሚል ምክንያት በ1998 ምዕራብ ሐረርጌን ጥለው አሜሪካ ሄዱ ። ቅዱስ ሲኖዶስ ለ4ዓመት ብቻ ፈቅዶላቸው ከ4 ዓመት በዃላ ተመልሰው እዛው ኦሮሚያ ክልል እንደሚያገለግሉ በቃልም በደብዳቤም ገልጾላቸው ከሀገር ወጡ፡፡

አሜሪካ እስከ ጥቅምት ወር 2004 ዓ.ም ቆይተው ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ ስለታወቀ፥ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኖ ኦሮሚያ ክልል ጉጂ ሊበን ቦረና ሀገረ ስብከት እንዲመሩ፣ የAfaan oromoo ቋንቋ ተናጋሪ ናቸውና የኦሮሞ ብሄር ተወላጅ ኦርቶዶክሳዊያንን በቋንቋቸው እንዲያገለግሉ መድቧቸው ነበር፡፡

Exአባ ኤዎስጣቴዎስ ግን ትምህርቴን ሳጠናቅቅ እመለሳለሁ ያሉትን ቃላቸው ሳይጠብቁ ወደ ሀገር ቤት (ኦሮሚያ ክልል ጉጂ ሊበን ቦረና ሀገረ ስብከት) አልመለስም ብለው ቀሩ። የተመደቡበት የኦሮሚያ ክልል ጉጂ ሊበን ቦረና ሀገረ ስብከት ያለ ሊቀጳጳስ ቀረ፡፡

ሊቀ ጳጳሱ ተመልሰው ኦሮሚያ ክልል ጉጂ ሊበን ቦረና እንዲያገለገሉ ከተወሰነበት ጥቅምት ወር 2004 ዓ.ም. ጀምሮ፣ በስልክና በደብዳቤ ተደጋጋሚ መልእክት ሲያደርሳቸው ቢቆይም ከአሜሪካ ተመልሰው ኦሮሚያ ክልል ገጠራማው ጉጂ ሊበን ቦረና ሀገረ ስብከት መስራት ሳይፈልጉ በእንቢታቸው ጸንተው እዛው አሜሪካ እስከ ዛሬ ድረስ ቀርተዋል።

ማለትም ላለፉት 17 ዓመታት ኑሯቸው አሜሪካ ነው።

ቅዱስ ሲኖዶስ ሊያነጋግርዎ ስለሚፈልግ ወደ ሀገርዎ እንዲገቡ” በሚል፦ ጥቅምት 30 ቀን 2004 ዓ.ም.፣ ኅዳር 8 ቀን 2004 ዓ.ም.፣ ታኅሣሥ 18 ቀን 2005 ዓ.ም.፣ ግንቦት 21 ቀን 2009 ዓ.ም. እና ኅዳር 3 ቀን 2007 ዓ.ም. በጻፈላቸው አምስት ደብዳቤዎችና በስልክም ተደጋጋሚ መልእክት ቢያደርሳቸውም የቅዱስ ሲኖዶሱን ጥሪ ችላ ብለው ቀርተዋል። ቅዱስ ሲኖዶሱ፣ ለስድስተኛና ለመጨረሻ ጊዜ ለሊቀ ጳጳሱ ባስተላለፈላቸው ጥሪ፣ ሐምሌ 30 ቀን 2009 ዓ.ም. ወደ ሀገር ገብተው ለጽ/ቤቱ እንዲያሳውቁ ደብዳቤ ለኮለቸው ነበር፡፡ “ካልመጡ ግን ቅዱስ ሲኖዶስ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት የሚገደድ መኾኑን ጉባኤው ወስኗል፤” በማለት አስጠንቅቆ ነበር - በቁጥር 245/699/2009 በቀን 18/09/2009 ዓ.ም.፣

ከቅዱስ ሲኖዶሱና ከፓትርያርኩ ተደጋጋሚ ጥሪ በተጨማሪ፣ በሚቀርቧቸው ካህናትና መምህራንም ተደጋጋሚ ምክር ቢሰጣቸውም፣ “ሰዉ በአውሬ እየተበላና በባሕር እየሰጠመ ብዙ መከራ አይቶና ብዙ ገንዘብ ከፍሎ የሚገባባትን ርስት ምድር አሜሪካንን ጥዬ አልወጣም፤ እንዲህ ያለ ሐሳብ ወደ እኔ ይዛችሁ አትምጡ፤” በሚል ወደ ሀገር ቤት ወደተመደቡበት ጉጂ ሊበን ሀገረ ስብከት እንደማይመለሱ ውሳኔያቸውን አሳውቀው በዚያው ቀርተወል። በዃላም በላኩት ሽምግልና አቡነ ኤዎስጣቴዎስ መኖር በፈለጉበት አሜሪካ እንዲጸኑ ቀሩ።
....
እንግዲህ ቤተክርስቲያን ላይ ለፈጸሙት በደል እንደምክንያት ያቀረቡት፦ ''የኦሮሚያ ክልል ያሉ ኦርቶዶክሳዊያንን በቋንቋቸው የሚባርክ ጳጳስ ተገቢው ሁኔታ የለም'' የሚል ነበር።

በተቃራኒው ህገወጡን ተግባር ከፈጸሙት መካከል አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የተመደቡበትን የኦሮሚያ ክልል መጀመሪያ ምዕራብ ሐረርጌ ጥለው ወደ አሜረካ የኮበለሉ። በዃላም ቅዱስ ሲኖዶስ ጉጂ ሊበን ቦረና ሀገረ ስብከት እንዲመሩ የወሰነውን ውሳኔ በመጣስ ገጠራማውን የኦሮሚያ ክልል ያሉ ሀገረ ስብከቶችን ንቀው አሜሪካንን ባዕታቸው አድርገው ላለፉት 17 ዓመታት በእንቢታ የቆዩት አንዱ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ነበሩ።

ለ17 ዓመት ለማገልገል የናቁትና የጠሉትን የኦሮሞ ኦርቶዶክስ ጥያቄ ሳይመልሱ ፤ ከአሜሪካ በዓመት አንዴ ወይም ሁለቴ እሱንም ለቅዱስ ሲኖዶስ ስበሰባ ብቅ ለሚሉባት ሀገርና የረሱትን ህዝብ ጥያቄ የዘነጉት ሰው። ዛሬ ተቆርቋሪ መስለው የሚታዩት ዓላማቸው ቤተክርስቲያንን ማፍረስ ለሶስተኛ ወገን መሸጥ ስለሆነ ብቻ ነው።

ለኦሮሞ ኦርቶዶክስ የሚያስብ አባት ገጠር ከተማ ሳይመርጥ በሚችለው ቋንቋ ያገለግል ይመራቸዋል እንጂ የወጣበትን ህዝብ ሸሽቶ አሜሪካ የተቀመጠ አባት በምን ሞራሉ ተቆርቋሪ መስሎ ይቀርባል?
...
ሳጠቃልል፤ Ex አባ ኤዎስጣቴዎስ
ቤተክርስቲያን ውስጥ 40 ዓመት አገልግለዋል ነገርግን አንድም ቀን በAfaan Oromoo ሰብከው ፣ ቀድሰው አያውቁም
18 ዓመት በጵጵስና ቆይተዋል አሜሪካንን ጥለው መጥተው የኦሮሞ ኦርቶዶክስን ለማገልገል ፍቃደኛ አልሆኑም
አንድም የAfaan Oromoo መጽሃፍት ጽፈው ወይንም ተርጉመው አያውቁም
633 views20:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ