2023-02-25 09:59:36
ሼር ማድረግ ደሞ የእናንተ ሥራ ነውቤተክርስቲያን ያወጀችውን አዋጅ ተከትሎ ሃይማኖታዊ
ተልእኳቸውን በመፈጸማቸው ከሥራ የተባረሩ፣የታሰሩና የተንገላቱ ኦርቶዶክሳዊያን ሪፖርት እንዲያደርጉ የተላለፈ ጥሪ፤
*****
የካቲት ፲፰ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
"""""""""""""""""""""""""""
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
**
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅደስ አሐደ አምላክ
አሜን
በኢትዮጵያ ኦርቶድክስ ተዋሕድ ቤተ ክርስቲያን በተፈጸመው ሃይማኖታዊ፤ ቀኖናዊ እና አስተዲዯራዊ ሕገ ወጥ የኤጴስ ቆጰሳት ሢመት ጋር በተያያዘ በተፈጠሩት ችግሮች እንዱሁም ችግሮቹን መነሻ በማዴረግ ቅዱስ ሲኖድስ ጾመ ነነዌን ምክንያት በማዴረግ የጾም እና የምህላ አዋጁ መነሻነት ምእመናን ሰማእትነትን ከፍለዋል፤ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዲት ደርሶባቸዋል፤ ያለአግባብም ታስረዋል፤ በሕገወጥ መንገድ ተንከራተዋል፤ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ከፍለዋል፤ አሁን አሁንም ከደመወዝ እና ከሥራ ገበታም ጭምር ታግደዋል፤ ተሰናብተዋልም፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ ቅደስ ሲኖዶስ በቤተ ክርስቲያናችን እና በምእመናን ላይ እየደረሱ ላሉ ጥቃቶች እና ጉዳቶች እንዱሁም ሕገ ወጥ ተግባራትን በመከታተል ተገቢውን ሕጋዊ ምላሽ መስጠት የሚችል የሕግ ባለሙያዎች አማካሪ እና ድጋፍ ሰጭ ኮሚቴ በማዋቀር ወደ ሥራ ገብቶ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ስሆነም የደረሱትን እና እየደረሱ ያለትን ጉዳቶች በተመለከተ ተጨባጭ መረጃ እና ማስረጃ ማሰቤሰቡ ለነገ የማይባል ተግባር በመሆኑ እናአሁንም የሕግ ክፍሉ በተለያነ መንገድ በሚደርሰው መረጃ ላይ ብቻ ተመስርቶ በውስንነት ድጋፍ እየሰጠ የሚገኝ መሆኑን ጠቅሶ መረጃ እና ማስረጃ ያላቸው ማናቸውም ምእመናን እና ምእመናት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እጆቻችሁ ላይ ያለ የሰነድ፤የድምጽ፤ እና የምስል ማስረጃዎቻችሁን በሙሉ ከዚህ በታች በተቀመጡት አማራጭ የመረጃ መንገዶች ታሳውቁን ዘንድ የሕግ ክፍሉ ያሳስባል፡፡
በመሆኑም ፦
፩. በማናቸውም የፌዳራል፤ የክልል እና የከተማ መስተዳደር ውስጥ ተቀጥራችሁ ስትሠሩ የነበራችሁ እና ከሃይማኖት ጋር በተያያዘ ከሥራ እና ከደመወዝ የታገዳችሁ እንዱሁም የተሰናበታችሁ በሙሉ ዝርዝር መረጃውን በመላክ እንድታሳውቁን፤
፪. በማናቸውም የፌዳራል፤ የክልል እና የከተማ መስተዳደር ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ በእስር ላይ የሚገኙ ካህናት፤ አገልጋዮች እና ምእመናን ሙለ መረጃ በመላክ እንድታሳውቁን፤
፫. በማናቸውም የፌዳራል፤ የክልል እና የከተማ መስተዳደር ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ የሞት እና የአካል ጉዳት የደረሰባቸውን ካህናት፤ አገልጋዮች እና ምእመናን ሙለ መረጃ በመላክ እንድታሳውቁን፤ እያሳሰብን ያላችሁን ማናቸውም መረጃ እና ማስረጃዎች ይህ ማስታወቂያ ከተነገረበት ከዛሬ የካቲት ፲፰ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ጀምሮ በስልክ ቁጥር +251985585858 በዋትስአፕ፤ በቴሌግራም ወይም በኢሜይል አዴራሻችን፡-eotcer@gmail.com የሞቱትን፤ የተጎደትን፤ የታሠሩትን እና የተሰወሩትን ሰዎች ስም እና የድርጊቱን ውጤት የሚያሳይ ዝርዝር መረጃ ታጋሩን ዘንዴ በቤተ ክርስቲያን ስም ጥሪያችንን
እናስተላፋሇን፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶድክስ ተዋሕዶ
ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
በውጪ ሀገር እና በሀገር ውስጥ ለምትገኙ ውድ ኦርቶዶክሳዊያን በዚህ በፆም ወቅት ሙሉ ቅዳሴ በዜማ ከጽሑፍ ጋር በንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ የዩቲዩብ ቻናል ያገኙታል ያዳምጡ ተሰጥኦውን ይመልሱ
2.0K viewsedited 06:59