2023-02-15 16:59:24
ሆኖም ግን የ2015 ዓ.ም የጾመ ነነዌ ሳምንት ቤተ ክርስቲያን በውስጥ ጠላቶች የተፈተነችበት ወቅት በመሆኑ የእምነቱ ተከታዮች የደረሰውና እየደረሰ ያለው ፈተና ከባድ ቢሆንም ልጆቿ በእምነት ጸንተው፣ በያሉበት ጥቁር ልብስ በመልበስ፣ በእንባ እና በጸሎት ከኃያሉ ከእግዚአብሔር ፊት የቆሙበት ወቅት መሆኑን ታሪክና ትውልድ የማይረሳው ነው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ በደረሰው ልብ በሚሰብር ፈተና ተስፋ ሳንቆርጥ በእምነት በሚደረግ ጸሎት የበለጠ በእግዚአብሔር ፊት እንድንቆም እንድንበረታ ያስተምረናልና ልንበረታ ይገባናል ብለዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ አክለው በመካከለኛው ካሊፎርኒያ በተተኪ ትውልድ ላይ ትኩረት በመስጠት ልዩ ልዩ እቅዶችን በማዘጋጀት ሀገራችን ኢትዮጵያ በሰሜን አሜሪካ ለትውልድ የሚተላለፍ ርስትና ቅርስ እንዲኖራት ለማድረግ በኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ስም ታሪካዊ፣ ታላቅና ሰፊ ቦታ ለመግዛት እንደታሰበና በግዢ ስምምነት ውስጥ እንደነበረ ከ3 ወራት በፊት ገንዘብ በማሰባሰብ እርዳታ መጠየቁ የሚታወስ ነው፡፡
በዚህም የገዳሙ ግዢ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅና ቁልፉን እና አስፈላጊ የሆኑ የግዢ ሰነዶችን መረከብ መቻላቸውን በታላቅ ደስታ ብፁዕነታቸው ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን ግዢውን ለመፈጸም 3.5 ሚሊየን ዶራል ከግል ድርጅቶች በወለድ እንዲሁም ከግለሰቦች ያለወለድ 1.9 ሚሊየን ያለወለድ በመበደር የተፈጸመ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
ስለገዳሙ በተለያዩ የማኅበራዊ ድረ ገጾች በተደረገው ጥሪ መሠረት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በገንዘብ፣ በጸሎት፣ በእውቀት፣ በሙያና ውድ ጊዜያችሁን በመስጠት ላደረጋችሁት እርዳታ በእግዚአብሔር ስም ምስጋናችንን እናቀርባለን ብለዋል፡፡
ብፁዕነታቸው አክለው በዚህ ታላቅ የገዳም ቦታ ላይ የተሟላ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት መስጠት እንዲቻልና በጥናት የተዘጋጁ እቅዶችን በአጫር ጊዜ ማሟላት እንድንችል የሁላችሁም አስተዋፆ አስፈላጊ በመሆኑ በጸሎት፣ በእውቀት፣ በገንዘብ፣ በቁሳቁስ አስፈላጊውን እርዳታ በማድረግ እንድትተባበሩን ሲሉ መንፈሳዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በተጨማሪም ይህንን ታሪካዊ ገዳም ለማስመረቅና ለማስጎብኘት ይቻል ዘንድ ሚያዚያ 14 ቀን 2025 ዓ.ም /April 22, 2013 G.C/ የቅዳሴ ቤቱ የምርቃት መርሐ ግብር እንዲከናወን መወሰኑን በመግለጽ በዓለም ዙሪያ የሚትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በበዓሉ ላይ በመገኘት ከቅዱሳን በረከት እንዲሳተፉና ገዳሙን እንዲጎበኙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
መጨረሻም አሁን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከገጠማት ችግር አንፃር ስለገዳሙ ሰፊ ገለጻ ማድረግ አግባብ ባለመሆኑ ወደፊት የግዢ አፈጻጸሙን በተመለከተ ሰፋ ያለ መረጃ እንደሚሰጡ ብፁዕነታቸው ገልጸዋል፡፡
2.0K views13:59