Get Mystery Box with random crypto!

ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ

የቴሌግራም ቻናል አርማ nikuyebetekerstiandemtsi — ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ
የቴሌግራም ቻናል አርማ nikuyebetekerstiandemtsi — ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ
የሰርጥ አድራሻ: @nikuyebetekerstiandemtsi
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.87K
የሰርጥ መግለጫ

ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ
የዩቲዩብ ቻናሉን ምዕመናን ሰብስክራይብ ያድርጉ የበለጠ ጠንክረን እንድሰራ ይረደናል
https://www.youtube.com/channel/UCYc6W7aFPzYIkK0F1a4VSlQ
ማንኛውንም መረጃ በዚህ ማድረስ  ትችላላችሁ
@Nikutewahedo
@Niku_tewahedo

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-02-22 15:51:18
በኮንታ 38 አዳዲስ አማንያን ሥርዓተ ጥምቀት ተፈጽሞላቸው የሥላሴን ልጅነት አገኙ!!
++++++++++++++++

(የካቲት 15 ቀን 2015 ዓ.ም

አዲስ የተሠራችው የቁታ ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ምርቃት የካቲት 12 ቀን 2015 ዓ.ም የኮንታ ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ገነት ቆሞስ አባ መዓዛ ቅዱሳን አዳነ በተገኙበት ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል፡፡

በዕለቱም 38 አዳዲስ አማንያን ሥርዓተ ጥምቀት ተፈጽሞላቸው የሥላሴን ልጅነት አግኝተዋል ሲል የማኅበረ ቅዱሳን ዘግቧል።

የጅማ ሀገረ ስብከት መገናኛ ብዙኃን

ወይ እግዚአብሔር ይገርማል ብቻ እግዚአብሔር ይመስገን
1.6K views12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 15:47:19
ጅማ ያሰረቻቸውን ካህናት አባቶች እና ምዕመናንን በሙብከእስር በዋስ ፈታለች
***

እግዚአብሔር ይመስገን

ለሁሉም በአንዴሄ መድረስ አይቻልም ቢሆንም ሁሉም ይፈታሉ ከእግዚአብሔር ጋር

በጸሎት አስብን የቀረቱንም በህግ እናስፈታለን
1.4K views12:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 15:16:09 ደስ  የሚል መንፈሳዊ ትምህርትነው  አዳምጡ









1.4K views12:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 09:34:26
አብ የተከላት፣ወልድ የመረጣት፣መንፈስቅዱስ የታተመባት ነፍስ
***

እህታችን ሐያት አህመድ እንኳን አለም ወደሚጠላት ቤት በሠላም መጣሽ

በዚህ ነብስ ደስ ያለው

እግዚአብሔር ይመስገን
1.9K views06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 08:09:20
የሩሲያ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በ12 ርእሰ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ማድረጋቸው ተገለጸ።

በሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መካከል ለሁለተኛ ጊዜ የሁለትዮሽ ውይይት ከየካቲት 4 ቀን እስከ የካቲት 9 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በሩሲያ ሞስኮ መደረጉ ይታወሳል።
በጉባኤው በኢትዮጵያ በኩል በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንትና የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መሪነት በሩሲያ በኩል በብፁዕ አቡነ ሊዮኒድ በአፍሪካ የሩሲያ ቤተ ክርስቲያን የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ እየተመራ ተከናውኗል።
በውይይቱ ላይ ከአራት ዓመታት በፊት በተካሔደው በመጀመሪያው የሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ወቅት በጋራ ይተገበራሉ ተብለው በተስማሙባቸው ፕሮጀክቶች ዙሪያ ግምገማ ተደርጓል።

እንዲሁም ሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ክርስትና እና ክርስቲያኖችን መከላከል፣ በዘመናዊው ዓለም ክርስቲያናዊ ዕሴቶች እንዳይጠፉ መጠበቅ፣ በሚዲያ አማካኝነት የልምድ ልውውጥ ማድረግ፣ በትምህርት ዘርፍ መደጋገፍን ጨምሮ በ12 ርእሰ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ፈጽመዋል።
የመነኮሳት ልዑካን ወደ ሁለቱም አብያተ ክርስቲያናት እንዲሔዱና በሁለቱም በኩል ያለውን የገዳማውያን ሕይወት እንዲመለከቱም ዕቅድ ይዘዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የሞስኮ የነገረ መለኮት አካዳሚ እና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ በትብብር እንዲሠሩ ስምምነት ላይ የተደረሰ ሲሆን የሩሲያ ቤተ ክርስቲያን ልዑክ ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲንና ሌሎች የኢትዮጵያ ቦታዎችን እንደሚጎበኝም ተጠቅሷል።
በተጨማሪም የሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ምእመናን በሩሲያ እና በኢትዮጵያ ያሉ ቅዱሳን ቦታዎችን መጎብኘት እንዲችሉ ለማድረግ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በትብብር ለመሥራት ተስማምተዋል። መረጃው የተሚማ ነው።
2.0K views05:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 09:48:32
የሰንበት ትምህርት ቤት ጉዞ እናበረታታ

የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ውሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን፣ ወቅታዊ ሁኔታዎችን የሚገልፁ መረጃዎችን እንዲሁም ማስታወቂያዎችን የምንለቅ ስለሆነ እንድትከታተሉን እንጠይቃለን።


መልእክት ካሎት በዚህ ሊንክ ይላኩልን


ለበለጠ በቴሌግራም አድራሻ ያግኙው


https://t.me/weludebirhan
https://t.me/weludebirhan
https://t.me/weludebirhan
821 viewsedited  06:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 23:37:58
በጣም ብዙ ሰዎች ስማችንን ስላነሳችሁን አንድ ላይ መልስ ለመስጠት ያህል... የወገናቸውን ሞት ተከትሎ ጥቁር ልብስ በመልበሳቸው ከስራ የታገዱትን ግለሰብ ጉዳይ...

ዜናው የመጣልን ዛሬ ከጊዜያዊ የህግ ኮሚቴው ስብሰባ ስንበተን ነበር። ..ከሰሞኑ የታሰሩት ሰዎች ብዛት :የፖሊስ የእምቢተኝነት አካሄድ በጣም አስቸጋሪ እየሆነብን ስለመጣ ዛሬ ከ9:00 እስከ ምሽት 1:00 ድረስ የዘለቀ አስቸኳይ ስብሰባ እና በድጋሚ የስራ ክፍፍል ማድረግ ነበረብን!
ተለቅ ያለ ቲም አዋቅረን የነገ እና የቀጣይ ቀናት የስራ ክፍፍል አድርገን ተለያይተናል። እኔ በበኩሌ መኪና ውስጥ ደርሼ ስልኬን ሳበራ ነው ይሄኛውን ዜና የሰማሁት።ለቡድኑ አባላት አሳውቄአለሁ። በአስቸኳይ ተሰብስበን ምላሻችንን ነገ እናሳውቃለን!ማንም የስራ ሃላፊ እንዳሻው የሚሆንበት ጊዜ ማብቃት አለበት!!
አይዞሽ እህታችን!!

ነገ የሚሆነው እናያለን በጰ
ጸሎት አስብን
189 views20:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 23:19:43
የሌላ ቤተ እምነት ሰዎች አጅበዋት የሚያከብሯት ጥንታዊቷ የዘይሴ ቅድስት ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን
***

አጼ ምኒልክን በአንበሳ ደቦል ፈንታ ለአከባቢው ገዢ(ካዖ) ስለፍቅራቸው ልኬት ስጦታ አድርገው የሰጡት ጽላት ናት።

ንጉሱ የትኛውንም የጦር ዘመቻ ከማድረጋቸው በፊት መባ እና የአስቡኝ ጸሎት በእዚህች አጥቢያ ያሲዙ ነበር።

ስሟም ዘይሴ ቅድስት ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን ይባላል። የምትገኘውም በጋሞ ጎፋ ሀገረ ስብከት አርባ ምንጭ ዙርያ ወረዳ ቤተክህነት ውስጥ ነው።

አሁን ላይ በአከባቢው ያለው ምዕመናንን ተመናምነው በጣም ጥቂት ብቻ ቀርተዋል ።

ነገር ግን በአከባቢው ያሉት የፕሮቴስታንት ቤተ እምነት ተከታዮች ስሟን ሲጠሩ " ኪዳኒኪ" ይላሉ።

ጽላቷ ከአከባቢው በአንድ ወቅት ተሰዳ በሄደችበት ወቅት በብዙ መከራ ነዋሪው ተፈትኖ እንደነበር ይነገራል።

ለምድራቸው የበረከት ምልክት አድርገው ስለሚያምኗት ሃይማኖታቸው ኦርቶዶክስ ባይሆንም እንዲህ ግን አጅበው ያከብሯታል።

ወዳጄ .... ገጠር በሚባለው ስፍራ ላይ እልፍ ድህነት የተራበ ነፍሳት እንዳሉ ስነግርህ በደስታ ነው።
331 views20:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 21:44:53
ብዙ ልብ የሚሰብር ነገር እየተመለከትን

ብቻ ምረጫ ይደረስ በድምፅ የምንጥልበት ቀን ይመጣል
958 views18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 18:49:24
በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሥር በደጀን ወረዳ ውስጥ የሚገኘው የሰብሸንጎ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በውል ባልታወቀ የእሳት አደጋ የወደመ ሲሆን አንድ ሰውም በአደጋው ምክንያት ሕይወቱ ሊያልፍ ችሏል።

የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል
1.8K views15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ