Get Mystery Box with random crypto!

ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ

የቴሌግራም ቻናል አርማ nikuyebetekerstiandemtsi — ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ
የቴሌግራም ቻናል አርማ nikuyebetekerstiandemtsi — ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ
የሰርጥ አድራሻ: @nikuyebetekerstiandemtsi
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.87K
የሰርጥ መግለጫ

ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ
የዩቲዩብ ቻናሉን ምዕመናን ሰብስክራይብ ያድርጉ የበለጠ ጠንክረን እንድሰራ ይረደናል
https://www.youtube.com/channel/UCYc6W7aFPzYIkK0F1a4VSlQ
ማንኛውንም መረጃ በዚህ ማድረስ  ትችላላችሁ
@Nikutewahedo
@Niku_tewahedo

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-02-24 02:18:38
ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቦረና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ አቀረቡ።

ብፁዕነታቸው በማኅበራዊ የትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት በቦረና እና አካባቢው በተከሰተው ድርቅ በርካታ ኢትዮጵያውያን በችግር ውስጥ እንደሚገኙ ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ ያሉ ሲሆን የተከሰተው ድርቅ ወደ ረሀብ ተለውጦ ከዚህ በላይ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ሕይወት እንዳያልፍ መላው ኢትዮጵያውያን ድጋፋቸውን ሊያደርጉ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

መንግስትም በአካባቢው ላሉ ወገኖች የሚያደርገውን ድጋፍ በማጠናከር የተቀናጀ የነፍስ አድን ተግባራትን በማከናወን ሊደግፋቸው ይገባል ሲሉም አክለዋል።

በመጨረሻም መላው ኢትዮጵያውያን በአካባቢው ለተከሰተው ድርቅ ትኩረት በመስጠት የወገኖቻችንን ሕይወት ለመታደግ ከጸሎት ጎን ለጎን የተቻላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ አባታዊ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
1.4K views23:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 02:17:35 በውጪ ሀገር እና በሀገር ውስጥ ለምትገኙ ውድ ኦርቶዶክሳዊያን በዚህ በፆም ወቅት ሙሉ ቅዳሴ በዜማ ከጽሑፍ ጋር በንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ የዩቲዩብ ቻናል ያገኙታል ያዳምጡ ተሰጥኦውን ይመልሱ
             








1.2K views23:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 20:40:05
የሰንበት ትምህርት ቤት አልባስ በተውሶ በመውሰድ እና መንበር በማጣት ለአገልግሎት ለተቸገረችው የቅድስት ኪዳነምህረት መቅደስ ከማህበራዊ ሚዲያ ያስተባብረነውን አድርሰናል።
***

ይህቺን መቅደስ አስታወሳችዋት?

የበዓለ ጥምቀት ወቅት ጥቂት ምዕመናንን ብቻ በዳስ ጥግ እና ጥግ ቆመው በዓሉን በሚያሳዝን ሁኔታ ያከበሩበት በጋሞ ጎፋ ፍርድ ወረዳ የምትገኘው የገጠሪቷ ቤተክርስቲያን

እነሆ በአገልጋይ ካህናት ጥያቄ መሰረት የአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ለአገልግሎት በተውሶ ከሌላ አጥቢያ አልባስ እየተዋሱ ያገለግሉ ነበር።

መንበሩም ለአገልግሎት አዳጋች ነበረ።

እነሆ እግዚአብሔር ቸርነትን ባደረገላቸው አካላት ቸርነት ህንጻ መቅደሷን ቀለም በመቀባት በማሳደስ፣ትልቅ መንበር እና 40 የሰንበት ትምህርት ቤት አልባስ በማስተባበር በአጠቃላይ ከ110ሺ ብር በላይ በሆነ ወጪ እንዲህ በደማቅ እና በደስታ ያከብሩ ዘንድ ፍቃደ እግዚአብሔር ሆኗል።

እግዚአብሔር ይመስገን

ቸርነት ላደረጋችሁልን ቅዱስ እግዚእብሔር የነፍስ ዋጋ አድርጎ ይቀበልልን !!!
1.7K views17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 20:35:25 በውጪ ሀገር እና በሀገር ውስጥ ለምትገኙ ውድ ኦርቶዶክሳዊያን በዚህ በፆም ወቅት ሙሉ ቅዳሴ በዜማ ከጽሑፍ ጋር በንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ የዩቲዩብ ቻናል ያገኙታል ያዳምጡ ተሰጥኦውን ይመልሱ
             








1.5K views17:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 17:15:54 ከዚህ ልጅ ምን እንማር ይሆን

ቤተ ክርስቲያን ስትቃጠል ቆሜ አላያትም ብሎ መስቀሉን ጨብጦ የተቃጠለዉ የጎጃም ወጣት የህይወት ታሪክ


+++++++#የቻለ_ለሌሎች_ያጋራ+++++++
ጉዳዩ እንዲህ ነዉ፤ በምስራቅ ጎጃም ዞን በደጀን ወረዳ የሚገኘው ደብረ መድኃኒት ሰብሸንጎ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተው በ1267 ዓ.ም መሆኑ ይነገርለታል።

ታቦቱ ተአምረኛ፣ ጠበሉ ፈዋሽ ነው። የደብሩ ነዋሪዎች ከሆኑት መካከልአቶ ጌታቸው እጅጉና እናቱ ወ/ሮ ውዳላት ያየህይራድ የተባሉ ክርስቲያን ባልና ሚስቶች በ1981 ዓ.ም የሚያምር ወንድ ልጅ ሲወልዱ ይርመዴ በማለት ስም አወጡለት።

ዓይኑ ቀለም መለየት፣ አንደበቱ ፊደል መጥራት ሲጀምር የትመን አቦ በሚገኘው አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ እስከ 6ኛ ክፍል ተማረ። ከዚያም አራት ዓይናው ሊቅ አለቃ ውብሸት ወንበር ዘርግተው ባስተማሩበት አጠገብ በተሠራው ብቸና ከተማ በሚገኘው በላይ ዘለቀ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እስከ ዐሥራ አንደኛ ክፍል ቢማርም ትምህርቱን ለመቀጠል የማያስችል ችግር ገጠመው። ተምሮ እስከምጨርስ የቤተሰቦቹ ችግር ጊዜ የማይሰጥ ሆነበት።

ትምህርቱን አቋርጦ ቤተሰቦቹን በመደገፍ ሕይወታቸውን ለመቀየር የወሰነው በደብሩ አጠገብ የሚያልፈውን ሙጋ የተባለውን ወንዝ በመጥለፍ ለልማት ነበር። ለአምስት ዓመታት ቀን ከሌት በመሥራት አትክልትና ፍራፍሬ በማልማት የቤተሰቦቹ ሕይወት ከቀየረ በኋላ ዓይኑ ያረፈባትን ሐና አየለ የተባለችውን ወጣት አግብቶ አንዲት ሴት ልጅ ወለደ። ትዳሩ ባይዘልቅም እርሱ ግን ልብስ ስፌት ሠልጥኖ በዚያ መተዳደር ጀመረ።

ልብስ ሰፍቶ ከሚያገኘውን ገንዘብ የዕለት ጉርሱን፣ የዓመት ልብሱን በማስቀረት ለቤተ ክርስቲያንና ለችግረኞች መርዳቱን ገንዘቡ አደረገ። ርኅራኄው አምሳያ እንዳልነበረው የሚያውቁት የሚመሰክሩለት ምነው እንደ እርሱ በመሆን የሚል መንፈሳዊ ቅንዓት እያደረባቸው ነው። ለቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለተቸገረ በማይሰስተው እጁ መመጽወት የሚወደው ይርመዴ ዐመታዊ የታቦት ንግሥ የማያመልጠው ሲሆን ሲሔድም ባዶውን የማይሔድ አንድ ጊዜ ከሦስት ሺህ ብር በላይ ሰጥቶ የሚመለስ ክርስቲያን ነበር።

ይርመዴ “አልባሳት የምሰፋው ትርፍ ለማግበስበስ አይደለም” የሚል ፈሊጥ ነበረው። ገዝቶ በሣጥን ያስቀመጠውን ልብስ ለታረዘ ሰጥቶ ሲጨርስ ብትን ጨርቅ ገዝቶ ሰፍቶ ያለብስ ነበር። የማስቀድመው መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ምክንያት የሚሆኑኝን ነው በማለት ንሰሓን አባቱ ሁለት ጊዜ ሰፍቶ አልብሷል። የተቸገረ ሰው አይቶ ማለፍ የማይሆንለት ይርመዴ ስንቅና የትራንስፖርት ላለቀባቸው ጠበልተኞች ገንዘብ በመስጠት ሀገራቸው እንዲገቡ ያደርግ ነበር።

ገንዘብ መመጽወቱና የተቸገረ መርዳቱ አላረካው ያለው ይርመዴ የካቲት 12 ቀን 2015 ዓ.ም ክርስትና የተነሣበት ደብረ መድኃኒት ሰብ ሸንጐ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን እየተቃጠለ መሆኑን ሲሰማ ቤተ ክርስቲያኑ ከተቃጠለማ አብሬ እቃጠላለሁ እንጂ ሲቃጠል በፍጹም ቆሜ አይሆንልኝም በማለት በፍጥነት ወደ እሳቱ ሄደ። ለቃሉ ታማኝ፣ ለእምነቱ ሟች የነበረው ይርመዴ ጌታቸው ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር መቃጠንል መርጦ እሳቱ ከተነሣበት ጉልላት ላይ ሊወጣ ሲሞክር ጓደኞቹ ሊከለክሉት ቢሞክሩም አልቻሉም።

በፍጥነት ወጥቶ አማትቦ ወደ እሳት የተቀየረውን የቤተ ክርስቲያን ጉልላት ያቀፈው ተነፋፍቆ የከረመ ወዳጁን ያገኘ ያህል ነበር። ይርመዴና የቤተ ክርስቲያኑ ጉልላት እንደ ተቃቀፉ ከምሥራቅ ወደ ምዕራብ ተያይዘው ጣራው ላይ ወደቁ።

ላለመላቀቅ ቃለ ማሐላ የፈጸሙ የሚመስሉት ይርመዴና የቤተ ክርስቲያኑ ጉልላት ጣራው ሲደረመስ ተያይዘው ወደ ቤተ ልሔም ወረዱ። በቦታው የደረሱ ክርስቲያኖች ይርመዴን በውስጥ፣ መስቀሉን በላይ ተናንቀው አገኟቸው።

ቤተ ክርስቲያንን ከራሱ አስበልጦ የሚወደው ወጣቱ ክርስቲያን ራሱን እንደ ሻማ በማቅለጥ ሰማዕትን የተቀበለው በእንዲህ ያለ ጥብዓት ነው። በዚህ ዘመን ለምንኖር ክርስቲያኖች አምላካችን እንዲህ ያለውን ጥብዓት ያድለን።
2.9K views14:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 17:00:00
ጋሞ ዞን በከምባ ዙርያ ወረዳ 109 ኢ አማያን በዛሬ ዕለት ተጠምቀው ሐብተ ወልድ ስመ ክርስትናንን ተቀብለዋል።
***

እግዚአብሔር ይመስገን
1.7K views14:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 06:58:21
እንኳን አደረሻቹው
875 views03:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 22:41:22
ትንታጉ ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው ከእስር ተፈቷል ! ከእግዚአብሔር እየሰራን ነው
305 viewsedited  19:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 19:06:24
የዛሬ 50 ዓመት የመስቀል በዓል በጋሞ ገጠራማ ስፍራ
***

ጋሞዎች የዛሬ 50 ዓመት ወደ ኃላ ተጉዘው የሚመለከቱን ዘመን "ቤኒ ክርስቲያን ላይታ" ይሉታል።

"ያኔ የክርስትና ዘመን" እንደማለት ነው።

በእዚህ ዘመን ኦርቶዶክሳዊት በጋሞዎች መንደር ሃይማኖት ብቻ ሳይሆን ባህልም ጭምር ነው።

እግዚአብሔር ሆይ ታሪክ ተናጋሪ ብቻ አታድረገን
1.3K views16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 17:54:10
ዲያቆን አማኑኤል ከእስር ተፈቷል::

እየሰራን ነው በጸሎት እያገዛቹን
1.4K views14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ