Get Mystery Box with random crypto!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ National Election Board of Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ nationalelectionboardnebe — የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ National Election Board of Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @nationalelectionboardnebe
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.27K
የሰርጥ መግለጫ

NEBE

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-01-25 12:02:43
የህዝበ ውሳኔ #ድምፅ መስጫ ቀን ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም
7.5K viewsedited  09:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 18:11:00 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ዎላይታ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት የውጤት ማመሳከር፣ የማዳመርና ይፋ የማድረግ ሂደትን አስመልክቶ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የሕዝበ ውሣኔው ምርጫ አስፈጻሚዎችን ለሚያሠለጥኑ ባለሞያዎች ሥልጠና መሰጠት ጀመረ።

በዚህ መሠረት እስካሁን የሚከተሉት ሥልጠናዎች ተሰጥተዋል፦

- በሕዝበ ውሣኔ የድምፅ መስጫ ቀን የውጤት ማመሳከርና የማዳመር ሥልጠና ለመሪ አሠልጣኞች እና ለተወሠኑ የቦርዱ ኦፕሬሽን ክፍል ባልደረባዎች ጥር 4 እና ጥር 5 ቀን 2015 ዓ.ም. እንዲሁም ጥር 8 እና ጥር 9 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።

- በሕዝበ ውሣኔው ድምፅ መስጫ ቀን፤ የውጤት ማመሳከር ሂደት ላይ ከ26 የማስተባበሪያ ማዕከላት ለተውጣጡ 121 አስፈጻሚዎች ጥር 13 ቀን 2015 ዓ.ም. የአንድ ቀን ሥልጠና በአርባ ምንጭ ከተማ ተሰጥቷል።

- በሕዝበ ውሣኔ ድምፅ መስጫ ቀን፤ በውጤት ማዳመር ሂደት ላይ ከዞን እና ከልዩ ወረዳዎች የሕዝበ ውሣኔው ማስተባባሪያ ጽ/ቤት እንዲሁም ከተመረጡ የማስተባበሪያ ማዕከሎች ለተውጣጡ 51 አስፈጻሚዎች ጥር 14 እና ጥር 15 ቀን 2015 ዓ.ም. የሁለት ቀን ሥልጠና በአርባ ምንጭ ከተማ ተሰጥቷል።

- በሕዝበ ውሣኔ ድምፅ መስጫ ቀን፣ ድምፅ ቆጠራ እና ውጤት በጣቢያ ደረጃ ይፋ የማድረግ ሂደት የተመለከተ ሥልጠና ለ250 የመሥክ አሠልጣኞች “የአሠልጣኞች ሥልጠና” የሚሰጥ ሲሆን፤ ለ135 የመሥክ አሠልጣኖች በመጀመሪያ ዙር ጥር 14 እና ጥር 15 ቀን 2015 ዓ.ም. በአርባ ምንጭ የአሠልጣኞች ሥልጠና ተሰጥቷል። የሁለተኛው ዙር የአሠልጣኞች ሥልጠና ለ117 ሠልጣኖች ጥር 17 እና 18 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚሰጥ ይሆናል።

- የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች የምርጫ ቀን ሥልጠና ከጥር 19 እስከ ጥር 24 ቀን 2015 ዓ.ም. በሦስት ዙር በ31 ማዕከሎች የሚሰጥ ይሆናል።
9.2K viewsedited  15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-20 12:12:23
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ታኅሣሥ 19 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢ. ብ. አ. ፓ) ነሐሴ 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በሚመለከት ፓርቲው ከሪፖርት ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉ፣ ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ እና የቦርዱ ታዛቢዎች ካቀረቡት ሪፖርት አንጻር መርምሮ ውሣኔ አሣልፏል።

ቦርዱ ባደረገው ምርመራ ፓርቲው ያካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ ያሻሻለው የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ግልጽ ያልሆኑ፣ መካተት ኖሮባቸው ያልተካተቱ አንቀጾችን የለየ ሲሆን፣ ከዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 ጋር የሚቃረኑ አንቀጾች ተፈጻሚ እንዳይሆኑና ጠቅላላ ጉባዔው በቀጣይ ስብሰባው አስፈላጊውን ማስተካከያ አድርጎባቸው ሪፖርት እንዲያቀርብ ቦርዱ ወሥኗል። ከላይ የተጠየቁ ማስተካከያዎች እንደተጠበቁ ሆነው ፓርቲው ነሐሴ 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ እና የተላለፉ ውሣኔዎችን ቦርዱ የመዘገበ መሆኑን ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ አሳውቋል።

የውሣኔውን ሙሉ ዝርዝር ከላይ በተያያዘው ደብዳቤ ላይ ያገኙታል።
2.8K views09:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 13:06:49
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ዎላይታ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ የተለያዩ የዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል።

የቦርዱ የሎጅስቲክ ሥራ ክፍል ለሕዝበ ዉሣኔው ድምፅ መስጫ ቀን የሚያገለግሉ የተለያዩ ሠነዶችና ቁሳቁሶችን (መጠባበቂያን ጨምሮ) ለ3,769 ምርጫ ጣቢያዎች ለሥርጭት ዝግጁ በሆነ መልኩ የማሸግ ሥራውን አጠናቋል። በእሽጉ ውስጥ ከተካተቱ ሠነዶች እና ቁሳቁሶች መካከል የድምፅ መስጫ ወረቀቶች፣ የሕዝበ ዉሣኔው ውጤት ማመሳከሪያ እና ማሳወቂያ እንዲሁም በድምፅ መስጫ ቀን ጥቅም ላይ የሚውሉ ሌሎች አስፈላጊ ሠነዶች ይገኙበታል።

በቀጣይም ቦርዱ ከላይ የተጠቀሱትን ሠነዶችና ቁሳቁሶች ወደ’ተመረጡ የሕዝበ ዉሣኔው ማስተባበርያ ማዕከላት የሚያሠራጨ ሲሆን፤ በተዋረድም ወደ ምርጫ ጣቢያዎች የሚያሠራጭ ይሆናል።
1.8K views10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 16:00:13
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የኢትዮጵያ ነጻነት ፓርቲ (ኢ. ነ. ፓ) ሚያዝያ 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በሚመለከት ፓርቲው ከሪፖርት ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉ፣ ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ እና የቦርዱ ታዛቢዎች ካቀረቡት ሪፖርት አንጻር መርምሮ ውሣኔ አሣልፏል።

ቦርዱ ባደረገው ምርመራ ፓርቲው ባካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ የፓርቲ አባላት ያልሆኑ በልመና ተግባር የተሠማሩ በአበል ክፍያ በጉባዔው ላይ እንዲሣተፉ ማድረጉንና የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ለጉባዔው ቀርቦ ሳይፀድቅ ፓርቲው ደንቡ ቀርቦ እንደፀደቀ በማስመሰል ለቦርዱ የሰጠውን የተሣሣተ መረጃ መሠረት በማድረግ ፓርቲው ከሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ መታገዱን በመግለጽ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 98/3/ መሠረት መከላከያውን እንዲያቀርብ ቦርዱ በሐምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም. በቁጥር አ1162/11/641 በተጻፈ ደብዳቤ ለፓርቲው አሳውቋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ፓርቲው በሐምሌ 21 ቀን 2014 ዓ.ም. በጽሑፍ ያቀረበው መከራከሪያ አሳማኝ ባለመሆኑ ቦርዱ አልተቀበለውም።

በዐዋጁ አንቀጽ 98/1(ሠ)/ የፖለቲካ ፓርቲው በማጭበርበር ወይም ዕያወቀ ወይም ማወቅ የተገባው ሆኖ ሳለ አሣሣች መረጃ በማቅረብ የተመዘገበ ከሆነ ወይም በዐዋጁ መሠረት መረጃ ሲጠየቅ የሐሰት መረጃ ለቦርዱ የሰጠ እንደሆነ ቦርዱ ፓርቲውን ከምዝገባ ሊሠርዝ እንደሚችል በግልጽ ተደንግጓል፡፡ በዚህ መሠረት ቦርዱ ፓርቲው በፈጸማቸው ጥፋቶች ምክንያት ከምዝገባ እንዲሠረዝ መወሠኑን ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ አሳውቋል።

የውሣኔውን ሙሉ ዝርዝርና ፓርቲው ያቀረበውን መከራከሪያ ከላይ በተያያዘው ደብዳቤ ላይ ያገኙታል።
2.1K views13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 11:43:49 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተለያዩ ምክንያቶች ምርጫ እንዲደገም ውሳኔ በተላለፈባቸው ምርጫ ክልሎች ላይ በዚህ ዓመት ምርጫውን ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እያከናወነ ነው።

በዚሁ መሠረት በአማራ ክልል በአዴት፣ አምባሰል፣ ባቲ፣ እስቴ 3፣ መርጦ ለማርያም፣ ራያ ቆቦ ምርጫ ክልሎች ላይ ለሚያካሄደው የድጋሚ ምርጫ፤ ምርጫ የሚያስፈጽሙ ሠራተኞችን በጊዚያዊነት ለመቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም በተጠቁሱት አካባቢዎች ውስጥ የምትኖሩ በምርጫ አስፈጻሚነት በገለልተኝነት ማገልገል የምትፈልጉ እና ከፓርቲ አባልነት ነፃ የሆናችሁ አመልካቾች ከጥር 9 እስከ ጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም. እንድታመለከቱ ቦርዱ ያሳውቃል።
የምልመላ መሥፈርት፡-

• ዕድሜው/ዋ ከ18 ዓመት በላይ የሆነ/ች፣
• የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፣
• መኖሪያ አድራሻ፦ በምርጫ ክልሉ ውስጥ በሚገኙ ቀበሌ ውስጥ የሆነ/ች፣
• የትምህርት ዝግጅት፦12ኛ ክፍል ያጠናቀቀ/ች እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች፣
• የሥራ ቦታ፦ በተጠቀሱት የምርጫ ክልል ውስጥ በሚገኙ ቀበሌ እና ምርጫ ጣቢያዎች፣
• የክፍያ ሁኔታ፡- በቀን በድምሩ 250 ብር፣
• የክልሉን የሥራ ቋንቋዎች መግባባት የሚችል/የምትችል ቢሆኑ ይመረጣል፤ ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ።
በመሆኑም ከዚህ በላይ የተጠቀሱን መሥፈርቶች የምታሟሉ አስፈጻሚዎች ከታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ አማካኝነት ከጥር 9 እስከ ጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም. ባሉት ስምንት ተከታታይ ቀናት እንዲመዘገቡ ቦርዱ ጥሪውን ያስተላልፋል።
ማሳሰቢያ፡ በእነዚህ ምርጫ ክልሎች የሚካሄደው የድጋሚ ምርጫ በመሆኑ በስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ የተሣተፋችሁ ምርጫ አስፈጻሚዎች ማመልከቻ የማንቀበል መሆኑን እናሳስባለን።

https://pollworkers.nebe-elections.org/recruitment

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ጥር 9 ቀን 2015 ዓ.ም.
2.8K views08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 10:43:44
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተለያዩ ምክንያቶች ምርጫ ባልተካሄደባቸው የተወሠኑ የምርጫ ክልሎች ላይ በተያዘው ዓመት ምርጫውን ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ተግባራት በማድረግ ላይ መሆኑ ይታወቃል።

በዚህም መሠረት በአማራ ክልል አንኮበር፣ ሰቆጣ፣ ተሁለደሬ 1፣ ተሁለደሬ 2፣ ላይ አርማጭሆ፣ ጭልጋ 1፣ ጭልጋ 2፣ ደምቢያ 2፣ ሞላሌ ምርጫ ክልሎች ላይ በምርጫ አስፈጻሚነት ለነበራችሁ ተሣትፎ በቅድሚያ እያመሰገንን፤ በቀጣይ በእነዚህ አካባቢዎች ለሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ በምርጫ አስፈጻሚነት በድጋሚ ለመሣተፍ ፍቃደኛ መሆንዎን እንዲያረጋግጡልን እንጠይቃለን። ፍቃደኛነትዎን ለመግለጽ ከላይ የተጻፈው መልዕክት (text message) በእጅ ስልክዎ ሲደርስዎ አንድን ተጭነው ይመልሱ።
2.9K views07:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 17:02:00
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ታኅሣሥ 20 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ የወለኔ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ወ. ህ. ዴ. ፓ) ጥር 9 ቀን 2013 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በሚመለከት ፓርቲው ከሪፖርት ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉ፣ ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ እና የቦርዱ ታዛቢዎች ካቀረቡት ሪፖርት አንጻር መርምሮ ውሣኔ አሣልፏል።

ቦርዱ ባደረገው ምርመራ በፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ የተካሄደው የማዕከላዊ ኮሚቴ፣ የቁጥጥር ኮሚሽን እና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ በግልጽ በዐዋጁ አንቀጽ 74(3) መሠረት ሚሥጥራዊ በሆነ መልኩ ያልተደረገና የሕጉን አስገዳጅ ድንጋጌ የተቃረነ በመሆኑ፤ ፓርቲው ሕጉን መሠረት በማድረግ በድጋሚ ጠቅላላ ጉባዔ ሊካሄድ እንደሚገባ ቦርዱ ወሥኗል።

በተጨማሪም በጠቅላላ ጉባዔው የተመረጡ አመራሮች ሙሉ አድራሻ እና በኃላፊነት ለመሥራት የተስማሙ መሆናቸውን የሚገልጽ በፊርማቸው የተረጋገጠ ሠነድ ያልቀረበ መሆኑ፣ የጠቅላላ ጉባዔው ቃለ ጉባዔ በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት በየገጹ ያልተፈረመ መሆኑ፣ የተሻሻለው የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ መካተት ያለባቸው አንቀጾች በተሟላ መልኩ አለመካተታቸው ቦርዱ ጠቅላላ ጉባዔው እንዲደገም የመወሠኑ ምክንያት ከሆኑት ውስጥ ይጠቀሳሉ።

ስለዚህም ይህ ውሣኔ ከተገለጸበት ከታኅሣሥ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት የአራት ወራት ጊዜ ውስጥ ማለትም እስከ ሚያዚያ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ ፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔውን እንዲያካሂድ፤ ይህም ሲሆን በድጋሜ የሚደረገው ጠቅላላ ጉባዔ ሕጉንና የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ የተቀመጡትን ድንጋጌዎች በተከተለ መልኩ መሆን እንዳለበት ቦርዱ ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ አሳውቋል።

የውሣኔውን ሙሉ ዝርዝር ከላይ በተያያዘው ደብዳቤ ላይ ያገኙታል።
2.3K views14:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 15:26:38
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ዎላይታ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ፤ ከተጠቀሱት ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ለተውጣጡ የፖሊስ ኮሚሽንና የፖሊስ ክፍል አባላት ጥር 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ሥልጠና ሰጠ።

ይህን በአርባ ምንጭ የተሰጠው በምርጫ ማስፈጸሚያ አደረጃጀቶችና ተግባራት ሰላምና ደኅንነትን ለመጠበቅ ለሚመደቡ የፀጥታ አስከባሪዎች የሚሰጥ ሥልጠና ላይ 29 ከፍተኛ ኮማንደሮች የተሣተፉበት ሲሆን፤ ከነዚህም ውስጥ 22 ከስድስቱ ዞኖችና አምስቱ ልዩ ወረዳዎች የተውጣጡ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ሰባት ተሣታፊዎች ደ’ሞ ከደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን ናቸው።

በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ የፖሊስ ኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ሥልጠናውን በምን አግባብ ወደታች ለማውረድ እንደታሰበ የተያዘውን ዕቅድና የእያንዳንዱን ፖሊስ ክፍል ኃላፊነት በተመለከተ ማብራሪያ አቅርበዋል። በምርጫ ማስፈጸሚያ አደረጃጀቶችና በምርጫ ተግባራት ላይ ሰላምና ፀጥታ የሚያስከብሩ የፀጥታ አስከባሪ አካላት የአሠራር ሥርዓት እና የሥነ-ምግባር መመሪያ ቁጥር 12/2013 በኪስ ለመያዝ በሚያመች መልኩ ተዘጋጅቶ ለፀጥታ አካላቱ እንዲደርሳቸው ተደርጓል።
2.6K views12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 14:09:33
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ታኅሣሥ 19 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ሰኔ 3 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በሚመለከት ፓርቲው ከሪፖርት ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉ፣ ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ እና የቦርዱ ታዛቢዎች ካቀረቡት ሪፖርት አንጻር መርምሮ ውሣኔ አሣልፏል።

ቦርዱ ባደረገው ምርመራ ፓርቲው ባካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ በተሻሻለው የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ሕጉን የሚጻረሩ፣ ወጥነት የሌላቸውና አሻሚ ትርጉም የሚሰጡ፤ እንዲሁም በዐዋጁ መሠረት ተሻሽለው መቅረብ ያለባቸውን አንቀጾች የለየ ሲሆን፤ በዚህም መሠረት ይህ ውሣኔ ከተገለጸበት ከታኅሣሥ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት አራት ወራት ጊዜ ውስጥ ማለትም እስከ ሚያዚያ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ጠቅላላ ጉባዔውን በድጋሚ እንዲያካሂድ፤ ይህም ሲሆን በድጋሚ የሚደረገው ጠቅላላ ጉባዔ ሕጉንና የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ የተቀመጡትን ድንጋጌዎች በተከተለ መልኩ መሆን እንዳለበት ቦርዱ ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ አሳውቋል።

የውሣኔውን ሙሉ ዝርዝር ከላይ በተያያዘው ደብዳቤ ላይ ያገኙታል።
271 views11:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ