Get Mystery Box with random crypto!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ National Election Board of Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ nationalelectionboardnebe — የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ National Election Board of Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @nationalelectionboardnebe
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.27K
የሰርጥ መግለጫ

NEBE

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 20

2022-07-27 18:41:24
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ ካፋ አረንጓዴ ፓርቲ (ካአፓ) ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ አስመልክቶ ተከታዩን ውሣኔ አሣልፏል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ ካፋ አረንጓዴ ፓርቲ (ካአፓ) መጋቢት 03 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ አስመልክቶ ፓርቲው ከሪፖርቱ ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉ፣ ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ እና የቦርዱ ታዛቢዎች ካቀረቡት ሪፖርት አንጻር መርምሯል። በዚህም መሠረት ቦርዱ የሕግ አፈጻጸም መሠረታዊ ጉድለቶች ያገኘ ሲሆን፤ ፓርቲው የሕጉን እና መተዳደሪያ ደንብ መርኆችን በተከተለ ሁኔታ በድጋሚ ጠቅላላ ጉባዔ ሊካሄድ እንደሚገባ ወሥኗል፡፡

ቦርዱ ጠቅላላ ጉባዔው ድጋሜ እንዲደረግ ከወሠነባቸው ምክንያቶች በዋናነት የፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ የተካሄደው የማዕከላዊ ኮሚቴ፤ የቁጥጥር ኮሚሽንና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ እጅ በማውጣት በመደረጉ በዐዋጁ አንቀጽ 74(3) መሠረት ሚሥጥራዊ በሆነ መልኩ ያልተደረገ፤ የሕጉን አስገዳጅ ድንጋጌ የተቃረነ በመሆኑ ሲሆን፤ ፓርቲው ሕጉን መሠረት በማድረግ በድጋሚ ጠቅላላ ጉባዔ ሊያካሄድ እንደሚገባ ቦርዱ ወሥኗል፡፡

የውሣኔውን ዝርዝር ለማንበብ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ
https://nebe.org.et/am/node/753
8.7K views15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 12:17:08
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የኢትዮጵያ ሶሻል-ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ አስመልክቶ ተከታዩን ውሣኔ አሣልፏል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ የኢትዮጵያ ሶሻል-ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) መጋቢት 24 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ አስመልክቶ ፓርቲው ከሪፖርቱ ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉ፣ ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ እና የቦርዱ ታዛቢዎች ካቀረቡት ሪፖርት አንጻር መርምሯል። በዚህም መሠረት ቦርዱ የሕግ አፈጻጸም መሠረታዊ ጉድለቶች ያገኘ ሲሆን፤ ፓርቲው የሕጉን እና መተዳደሪያ ደንብ መርኆችን በተከተለ ሁኔታ በድጋሚ ጠቅላላ ጉባዔ ሊካሄድ እንደሚገባ ወሥኗል፡፡

ቦርዱ ጠቅላላ ጉባዔው ድጋሜ እንዲደረግ ከወሠነባቸው ምክንያቶች በዋናነት የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫ በሚካሄድበት ጊዜ ዕጩዎች ያገኙት ድምፅ አቆጣጠርን በሚመለከት ከቦርዱ የተላኩት ታዛቢዎች ባቀረቡት ሪፖርት ግልጽ ባልሆነ መንገድ እየተቆጠረ እንደነበር በማረጋገጣቸው፤ የጉባዔ አዘጋጆቹን ቆጠራው በትክክል ለምን እንደማይካሄድ ሲጠይቁም ጉባዔተኞቹ ከሩቅ የመጡ እንደሆኑ እና ሌሊቱን እስኪቆጠር መጠበቅ እንደማይችሉ የተገለጸላቸው በመሆኑ፤ እንዲሁም በአጭር ጊዜ ውስጥ “አልፈዋል/ ተመርጠዋል” የተባሉ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ዝርዝርም በአስመራጭ ኮሚቴ ሰብሳቢ እንዲነበብ መደረጉ ይጠቀሳሉ።

የውሣኔውን ዝርዝር ለማንበብ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ
https://nebe.org.et/am/node/752
7.4K views09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 09:26:50 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ ፓርቲዎች ያቀረቡትን የምዝገባ ፍቃድ አስመልክቶ ተከታዩን ውሣኔ አሣልፏል፡፡
https://nebe.org.et/am/node/751
9.0K views06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 18:02:31
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ዎሕዴግ) ኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴ ጠቅላላ ጉባዔ ለማድረግ ለቦርዱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ቦርዱ ከላይ የተያያዘውን ውሣኔ አሣልፏል።
9.3K views15:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 15:59:59
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሚያዝያ 2 ቀን 2014 ዓ. ም. የኢትዮጵያ ነፃነት ፓርቲ (ኢነፓ) ያደረገውን ጠቅላላ ጉባዔ በተመለከተ ፓርቲው ያቀረባቸውን ሠነዶችና ሪፖርቶች እንዲሁም የቦርዱ ታዛቢዎችን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ ከላይ የተያያዘውን ውሣኔ አሣልፏል።
9.5K views12:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 16:12:58 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አመራር እና የጽ/ቤት ሃላፊዎች ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. ከተባበሩት መንግሥታት የፍላጎት ግምገማ ልዑክ የምርጫ ድጋፍ አስተባባሪዎች ጋር ገንቢ ውይይት አካሄደ።

ልዑኩ አላማውን የፖለቲካና የምርጫ ምኅዳሩን፣ የምርጫ ዑደቱ የሚተዳደርበት የሕግ እና ተቋማዊ ማዕቀፍን፣ እንዲሁም የባለድርሻ አካላትን ዐቅምና ፍላጎት በመገምገም ምርጫ ቦርዱ በጠየቀው መሠረት የተሻሉ አማራጮችን ማሳየትና ድጋፉ የሚያስፈልገው ምን ላይ ነው የሚለውን መለየት ሲሆን፤ ከምርጫ ቦርድ በተጨማሪ ልዑኩ ፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ የሲቭል ማኅበረሰብ ተቋማትን፣ ብዙኃን መገናኛ አካላትን ጨምሮ የምርጫ ባለድርሻ አካላትን አግኝቷል።

The National Election Board of Ethiopia (NEBE) and its secretariat had a constructive meeting with the United Nations Needs Assessment Mission (NAM) for electoral assistance yesterday, July 14, 2022.

The purpose of the Needs Assessment Mission (NAM) is to evaluate the political and electoral environment in the country, the legal and institutional framework governing the electoral process, the capacity and needs of the various election stakeholders as well as to develop recommendations on the possibilities of electoral assistance in accordance with the request of NEBE.
The mission met with electoral stakeholders including political parties, Civil Society Organizations, and media representatives.
3.5K viewsedited  13:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 17:53:01
4.5K views14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 14:25:57 ማስታወቂያ

በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በመሥክ አሠልጣኝነት ለተሣተፉ ባለሞያዎች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በመሥክ አሠልጣኝነት ለተሣተፉ ባለሞያዎች ለነበራቸው የላቀ ተሣትፎ እያመሰገነ፤ በምርጫው ላይ በአሠልጣኝነት የነበራቸውን ተሣትፎ የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት በቀላሉ ለመውሰድ የሚያስችል የምስክር ወረቀት መውሰጃ ፖርታል አዘጋጅቶ አቅርቧል።

የምስክር ወረቀቱ የሚመለከታቸው ባለሞያዎች ከሥር የሚገኘውን ሊንክ በመጫንና የምስክር ወረቀት ፖርታሉ ላይ የሚጠየቁትን የማንነት ማረጋገጫ መረጃ በማስገባት የምስክር ወረቀታቸውን መውሰድ የሚችሉ መሆኑን ቦርዱ ይገልጻል።


http://nebecertificate.org.et/trainers
9.8K viewsedited  11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 13:14:08 በኦሮሚያ ክልል ለምትገኙ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለተሣተፋቹ ምርጫ አስፈጻሚዎች ሁሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባሳለፍነው ሣምንት በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለተሣተፉ ምርጫ አስፈጻሚዎች የሰርተፍኬት መውሰጃ ፖርታል ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ነገር ግን በአንዳንድ የቴክኒክ ችግሮች ምክንያት በኦሮሚያ ክልል ለምትገኙ የምርጫ አስፈጻሚዎች ፖርታሉ እየሠራ ስላልሆነ፤ ይህንን ችግር በጥቂት ቀናት ውስጥ አስተካክለን እስከምናሳውቃችሁ ድረስ በትዕግሥት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንገልጻለን።

Raawwachiistota filannoo, filannoo biyyaalessa 6ffaa irratti naannoo Oromiyaatti hirmaattaniif

Boordiin Filannoo Biyyaalessa Itoophiyaa torban darbe rawwachiistota filannoo akka biyyaatti argamaniif poortaalii waraqaa ragaa fudhachuudhaaf isaan gargaaru ifoomsuun isaa ni beekama. Haa ta`u malee, sababa rakkoo teeknikaa gara garaatiin raawwachiistota filannoo naannoo Oromiyaatti argamtaniif poortaalichi hojjachaa waan hin jirreef, rakkoo kana guyyoota muraasa keessatti sirreessinee hanga isin beeksisnutti obsaan akka nu eegdan kabajaan isin beeksisna.
18.2K views10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-08 10:09:40 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለተሣተፉ የምርጫ አስፈጻሚዎች ሰርተፍኬት መስጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለተሣተፉ ሠራተኞች፤ ማለትም የዞን አስተባባሪዎች፣ ምክትል የዞን አስተባባሪዎች፣ የምርጫ ክልል ኃላፊዎች፣ የምርጫ ጣቢያ ምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ዳታ ኢንኮደሮችና የአይ.ሲ.ቲ ባለሞያዎች ለነበራቸው ተሣትፎ ቦርዱ እያመሰገነ፤ በምርጫው ላይ የነበራቸውን ተሣትፎ የሚያረጋግጠውን የምስክር ወረቀት በቀላሉ ለመውሰድ የሚያስችል የምስክር ወረቀት ፖርታል አዘጋጅቶ አቅርቧል። የምስክር ወረቀቱ የሚመለከታቸው ሠራተኞችም የምስክር ወረቀት ፖርታሉ ላይ የሚጠየቁትን መረጃዎች በማስገባት የምስክር ወረቀታቸውን መውስድ የሚችሉ መሆኑን ቦርዱ ይገልጻል።

ተጨማሪ መረጃ ለማግኝት እንዲሁም ሰርተፍኬትዎ እንዲደርስዎ እዚህ ላይ ይጫኑ

https://nebe.org.et/am/certificate-pw
26.6K views07:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ