Get Mystery Box with random crypto!

አዋጅ – Awaje News

የቴሌግራም ቻናል አርማ na_le_eth — አዋጅ – Awaje News
የቴሌግራም ቻናል አርማ na_le_eth — አዋጅ – Awaje News
የሰርጥ አድራሻ: @na_le_eth
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 190
የሰርጥ መግለጫ

https://t.me/awajenews

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-07-12 13:41:26
101 viewsNa le Tofek, 10:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 09:13:12
#ለጥንቃቄ

በክሮም ብሮዉዘር ላይ አደገኛ ክፍተት መገኘቱን ተከትሎ ተጠቃሚዎች ብሮዉዘሩን እንዲያዘምኑ ጉግል አሳሰበ

ግዙፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ጉግል በክሮም ብሮዉዘሩ (chrome browser) ላይ ተጠቃሚዎችን ለከፍተኛ የሳይበር ጥቃት የሚያጋልጥ ክፍተት መገኘቱን ተከትሎ አስቸኳይ የክፍተት መሙያ አቅርቧል። ኩባንያዉ ለክፍተቱ መሙያ Chrome_103.0.5060.114 የተሰኘ የክሮም እትም ያቀረበ ሲሆን ይህም ለማይክሮሶፍት ዊንዶዉስ ተጠቃሚዎች የሚሆን መሆኑ ጠቁሟል።

ይህ የደህንነት ማዘመኛ በጉግል ኩባንያ የቀረበለት ክፍተት ከዚህ በፊት ያልተለየ እና የመረጃ መንታፊዎች በተጠቃሚዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረስ የሚያስችላቸዉ መሆኑን ጉግል ይፋ አድርጓል።

ይህ ቀደሞ ያልተለየ የሳይበር ጥቃት አጋላጭ ክፍተት zero_day_vulnerability በክሮም ብሮዉዘር ላይ ሲደርሰ የፈረንጆቹ 2022 ከገባ ወዲህ ለአራተኛ ጊዜ መሆኑም ታዉቋል። በመሆኑም የክሮም ብሮዉዘር ተጠቃሚዎች የክፍተቱን አደገኛነት በመረዳት በአስቸኳይ የመረጃ ማፈላለጊያዉን እንዲያዘምኑ ጉግል መክሯል።
804 viewsNa le, 06:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 17:09:09
#ለጥንቃቄ

ቀጣይ ቀናት ከፍተኛ ጎርፍ ሊከሰት ስለሚችል በተዳፋት አካባቢዎች ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ኢንስቲትዩቱ አሳሰበ

የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ከሐምሌ 1 እስከ 10 ቀን 2014 የሚኖረውን የአየር ፀባይ ሁኔታ ትንበያ በተመለከተ በሰጠው መግለጫ በሐምሌ ወር የመጀመሪያዎች አስር ቀናት በአገሪቱ መደበኛ እና በአንዳንድ አካባቢዎች ነጎድጓዳማ እና በረዶ የቀላቀለ ዝናብ ይጠበቃል ብሏል።

በምዕራባዊ የአገሪቱ አካባቢዎች አጋማሽ እና መካከለኛው የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ100 እስከ 200 ሚሊ ሜትር፤ በተወሰኑ ቦታዎች ከ200 ሚሊ ሜትር በላይ ዝናብ እንደሚጠበቅ በመግለጫው ተመላክቷል፡፡

በሐምሌ ወር በመጀመሪያዎቹ አስር ቀናት በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በትግራይ እና በደቡብ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች መደበኛ እና ከመደበኛ በላይ ዝናብ ይጠበቃል ብሏል። በአብዛኛው የአባይ፣ ባሮ-አኮቦ፣ ተከዜ፣ አዋሽ፣ ስምጥ ሸለቆ፣ ኦሞጊቤ፣ አፋር-ዳናከል፣ የላይኛውና መካከለኛው ዋቢ-ሸበሌ እንዲሁም ገናሌ-ዳዋ ተፋሰሶች ከፍተኛ እርጥበት ይኖራቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።

በታችኛው ገናሌ-ዳዋ፣ ስምጥ ሸለቆ እና ኦሞ-ጊቤ ተፋሰሶችም መጠነኛ እርጥበት ይኖራቸዋል ተብሏል። ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች እንዲሁም ሌሎች አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎች ለጎርፍ አደጋ ሊጋለጡ ስለሚችሉ ከወዲሁ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ኢንስቲቲዩቱ ማሳሰቡን ኢዜአ ዘግቧል። የዝናቡ ሁኔታ በመኸር አብቃይ እና ዘር መዝራት ባልተጀመረባቸው አካባቢዎች የተሻለ እርጥበት ስለሚኖር አርሶ አደሮች አጋጣሚውን እንዲጠቀሙበት አስገንዝቧል።
80 viewsNa le, 14:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 07:19:47
Looking into our own death:
How much is the flame,
how hard will get tragedic;
How heavy is the load?
How far it will sink?
How deep the suffering will be?
How louder it will get?
Being victim of the blade,
Is it sadness? Is it rage? Is it regret? How does it feels? What are we gonna name it?
Is any words of languages capable of expressing these extent of plague?
Will Mother and Country handle the burden of this pain and misery?
76 viewsNa le, 04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 22:40:25
705 viewsNa le, 19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 13:41:36
82 viewsNa le, 10:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 19:52:15
ጥቂት የመልካምነት ጠብታዎች ተጠራቅመው ትልቁን የሰብአዊነት ባህር ይሰራሉ፡፡ መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ታፈራለች የሰው ልብም የመልካም ቡቃያ አውድ ናት፡፡ እኛም ከፈጣሪ የተሰጠንን ብዙ መልካም ነገሮች ውስጥ ጥቂቷን መልካምነት አጠገባችን ላሉት ሰዎች እናካፍል የሰው ልጅ መልካም ነገር ቢያደርግ ብዙ ነገሮችን ያተርፋል መልካም ስራ የክፉ ቀን ስንቅ ናትና፡፡

ስለዚህ ጥሩ ነገር በመስራት ለህሊናችን ሀሴትን እናቀብል፡፡ እኛም በመልካምነትና በጥሩነት ትልቅ ልንሆን ይገባል ትልቅነት የሚመጣው ከትልልቅ ሀሳቦች ነው፡፡ ሀገርም የአስተሳሰብና የመልካም ሀሳብ ውጤት ናት፡፡ ነገሮች በመልካም አስተሳሰቦችና ሀሳቦች ይደራጃሉ፡፡ ሀገርም የሚገነባው በጥሩ ሀሳብ ነውና፡፡ ሀሳብና አመለካከታችንን ወደ ጥሩና መልካም ነገር ከቀየርን የማንለውጠው ነገር የለም፡፡ አሁንም ካለንበት ችግር ለመውጣት መፍትሄው ያለው በእያንዳንዳችን መዳፍ ላይ ነው፡፡ ነገሮችን ለመቀየር እያንዳንዳችን የመፍትሄ ሀሳብ ልናዋጣ ይገባል፡፡
81 viewsNa le, 16:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 22:42:21
#Let's_work _together_for_unity !!

Gondar City Administration's fundraising program designed to support individuals and institutions who have been affected by the crisis under the guise of religion,

The Fundraising for parts of the society that have suffered life, physical, psychological and property damage which is a reassurance of our hope that we can rebuild damaged individuals and institutions and show that our culture of solidarity and solidarity will not be eroded by extremists.

The fundraise will be collected through, Commercial Bank of Ethiopia, Amhara Bank, Dashen Bank and Hibret Bank.

CBE Account Number :
1000484634509

Amhara Bank Account Number:
9900000685759

Dashen Bank Account Number:
5024893493011

Hibret Bank Account Number:
2030412149295011
202 viewsNa le, 19:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 14:54:52 #የኛ_ዘመን_ወጣት_ሚና

በጎንደር አዘዞ ጠዳ ክፍለከተማ "የኛ ዘመን ወጣት ሚና" በሚል መሪ ቃል ወጣቶች ጋር በአገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ ተካሄደ።

ፕሮግራሙ ከመጀመሩ በፊት በቅርቡ በኦነግ ሸኔ እና በተለያዩ ጊዜያት የሂወት መስዋዕትነት እና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ንፁሀን ዜጎች የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ ተጀምሯል።

መድረኩን የመሩት የጎንደር ከተማ ወጣቶች ሊግ ስራ አስፈፃሚ ወጣት ቶፊቅ እስማኤልሀኪም ሲሆኑ በመድረኩ ላይ የከተማ፣ የክፍለ ከተማና የቀበሌ አመራሮች ተገኝተዋል። ፕሮግራሙን በእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት የከፈቱት የአዘዞ ጠዳ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት አቶ ይሁን ዳምጤ ናቸው።

የመወያያ ሰነዱን ያቀረቡት የአዘዞ ጠዳ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ሊግ ኃላፊ የሆኑት ወጣት ሀይለ ማሪያም ፋሲል ሲሆኑ በሰነዱም በዚህ ዘመን ያለን ወጣቶች በሀገራችን የዜጎችን ሰላምና ደህንነት የማረጋገጥ ስራ ላይ ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆን፣ የተሰሩ የልማትና የዲሞክራሲ ማጎልበት ስራዎችን ማወቅና ማበረታታት እና ሚዲያውን የሰላምና የልማት መሳሪያ እንዲሆን በመቅረፅ በጉልህ መንቀሳቀስና ሀገራችንን ወደ ቀደመ ክብሯ መመለስ እንደሚጠበቅብን ተገልጿል።

በተጨማሪም በሰነዱ ወጣቱ በክረምት ወራት በበጎ ፍቃድ ተግባራት ላይ በመሠማራት ሀገሩን ብሎም ራሱን መጥቀም እንዳለበት እና በያዝነው አመት ለታቀዱት የክረምት በጎፈቃድ ተግባራት አጋዥ እንዲሆኑ ለውይይቱ ተሳታፊዎች ጥሪ ተላልፎል።

የኛ ዘመን ወጣቶች ህብር ብሔራዊ ወንድማማችነት በመገንባት ለሃገራችን አንድነትና ዘላቂ ሰላም ላይ በመትጋት ለሚያጋጥሙ ችግሮች የመፍትሔ አካል መሆን አለብን ሲሉ ወጣት ቶፊቅ ገልፀዋል።

በመጨረሻም የወጣቱን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ፣ ከህግ ማስከበር አንፃር፣ ሀገራችን ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ በመረዳት ከወጣቱ ምን ይጠበቃል፣ ከኑሮ ውድነት አኳያ እንዲሁም ከክረምት በጎፈቃድ ተግባሮች አንፃር በርካታ ጥያቄዎች ከውይይቱ ተሳታፊዎች ተነስተው በመድረኩ መሪዎች ምላሽ በመሰጠትና ወጣቱ የኢትዮጵያን መከላከያ ሰራዊት በመቀላቀል የሀገሩን ዳር ድንበር ማስጠበቅ እንዳለበት መልዕክት በማስተላለፍ ውይይቱ ተጠናቋል።
68 views𝐓𝐚𝐦𝐢𝐫𝐚𝐭 𝐘𝐢𝐫𝐝𝐚𝐰, 11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 14:54:52
61 views𝐓𝐚𝐦𝐢𝐫𝐚𝐭 𝐘𝐢𝐫𝐝𝐚𝐰, 11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ