Get Mystery Box with random crypto!

አዋጅ – Awaje News

የቴሌግራም ቻናል አርማ na_le_eth — አዋጅ – Awaje News
የቴሌግራም ቻናል አርማ na_le_eth — አዋጅ – Awaje News
የሰርጥ አድራሻ: @na_le_eth
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 190
የሰርጥ መግለጫ

https://t.me/awajenews

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-02-26 12:08:37 hi
63 viewsNa le Tofek, 09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 23:29:36 https://youtube.com/@yemarbetemengist
11 viewsNa le Tofek, 20:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 21:35:50 “ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል”
           ከዲያቆን ሔኖክ ኃይሌ
   …ንጉስ ህዝቅያስ በጠና ታሞ ተኝቷል ነብዩ ይሳያስ ሊጠይቀው መጣ ሆኖም እደ ልማዱ “እግዚአብሔር ይማርህ” አላለውም ለጆሮ የሚከብድ ቃል ጥሎበት ወጣ “ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል” ነብዩ ይህንን ብሎት ከወጣ በኃላ ህዝቅያስ ወደ ግድግዳው ዞሮ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ አምላኩ በንግግር ብዛት የሚሰማ አምላክ አይደለምና ፊቱን ወደ መቅደሱ አቅጣጫ አዙሮ አለቀሰ..

  …ከጥቂት ደቂቃ  በኃላ ነብዩ ኢሳያስ ሌላ መልዕክት ይዞ ተመለሰ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል “ፀሎትህን ሰምቻለሁ እንባህን አይቻለሁ በእድሜህ ላይ አስራ አምስት አመት እጨምርልሀለሁ”  ትንቢተ ኢሳያስ ምዕ38፡5

  ህዝቅያስ "ቤትህን አስተካክል" ከተባለ በኃላ ፊቱን አዙሮ ከማልቀስ በቀር ምንም አላደረገም “ህዝቅያስ ሆይ ካልጋህ ሳትዎርድ ያስተካከልከው ቤት ምን አይነት  ቤት ነው? ለባሪያዎችህ መመሪያ ሳትሠጥ የምታስተካክለው ቤትስ  እንዴት ያለ ቤት ነው? በደቂቃዎች ውስጥ ትሞታለህ ከተባልክ በኃላ አስራ አምስት አመት ያስጨመረልህ ምን አይነት ማስተካከያ አድርገህ ነው? ለኛም ንገረንና እድሜ እናስጨምር”

ህዝቅያስ ካልጋው ሳይነሳ ያስተካከለው ቤቱ ልቡ ነበር ልብህን ካስተካከልክ ቤትህ ይስተካከላል “እግዚአብሔር እንደሆነ ትሞታለህ ቢልህም መሞትህን አይፈልግም እርሱ ከሀጥያትህ እንጂ ካንተ ጋር ፀብ የለውም”  “በውኑ ኃጥያተኛ ይሞት ዘንድ እፈቅዳለሁ” ይላል ጌታ እግዚአብሔር “ከመንገዱ ይመለስና በህይወትም ይኖር ዘንድ አይደለምን” ይላል መሀሪው ትንቢተ ህዝቅየል ምዕ18፡23
እሱ ትሞታለህ የሚልህ መኖርህን ፈልጎ ነው አንዴ ብያለሁ ብሎ አይጨክንብህም በንሰሀ ተመለስ እንጂ ምሬሀለሁ ለማለት ይቸኩላል አሁን ትሞታለህ ብየው አሁን ትድናለህ ብለው ይንቀኛል ሳይል ተመልሶ ይምርሀል ሀጥያትህንም ወደ ጥልቁ ይጥለዋል በጎ እንድትሰራም እድሜ ይጨምርልሀል አንተ ብቻ ተመለስና አሁኑኑ ንሰሀ ግባ

  ከበደል አልጋ ጋር ያጣበቀህ ፈተናም ድል መንሻው ጊዜው አሁን ነው ህዝቅያስ በደቂቃ እምባ ምህረት አግኝቶ እድሜ ካስጨመረ በዐብይ ፆም ሙሉ የሚያለቅስ ምን ያህል እድሜ ያገኝ ይሆን

#ወዳጄ

አንተም ተነሳና በዚህ ወር ቤትህን አስተካክል እንደ ህዝቅያስ ፈጣሪ ይጠብቅሃል የተቀየምከውን ይቅር በል የበደልከውን ካስ የሚበቀልህን የማይተኛ ጠላትህን ዲያብሎስን ተበቀለው ጾም ዲያብሎስ ድል የተደረገበት የጦር አውድማ ነው፡፡

በዚህ ወራት ድል ያላደረግነውን ፈተና በሌላ ጊዜ አናደርገውም

“ሰነፍ ገበሬ በሰኔ ይሞታል” የሚባለው በፆም የተኛ ክርስቲያን መቸም አይነቃም በጾም ያልተገራ አንደበት መቸም አይገራም በጾም ያልተፈወሰ ቂም መቸም አይፈወስም

ጌታችን በወንጌል አንዴ ወደ እሳት አንዴ ወደ ውሃ የሚጥል ጋኔን ያለበትን ልጅ ሲፈውስ እንዲህ አይነቱ ጋኔን ያለጾምና ያለ ፀሎት አይወጣም ብሎ ነበር

ሀገራችንን አንዴ ወደ እሳት አንዴ ውሃ የሚጥላት የጥላቻ ጋኔንም ያለፆምና ያለ ፀሎት አይወጣም

#ወዳጄ

ከቁስልህ የምትፈወስበት ወራት እንደሆነ እወቅ አንተስ ብትሆን ልትላቀቀው እየፈለክ ያቃተህ ክፉ ልማድ የለብህም እንደ ቅዱስ ጳውሎስ “የምፈልገውን መልካም ነገር አላደርግም የማልፈልገውን ክፉ ነገር አደርጋለሁ ምንኛ ጎስቋላ ለዚህ ለሞት ከተሰጠው ሰውነት ማን ያድነኛል” ብለህ ምርር እንድትል ያደረገህ ኃጥያት የለም

እንግዲያውስ እወቀው ይህ አይነቱ ወገን ያለ ፆምና ያለ ፀሎት አይወጣም ይህ ጾም ቁስል የሚሽርበት ጾም ነው ይህ ፆም እከክን ማራገፊያ ጾም ነው እንደ ህዝቅያስ በዚህ ወር ቤትህን በንሰሃ አስተካክል፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የካቲት 15/2012 ዓ.ም
22 viewsNa le Tofek, 18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 21:35:48
20 viewsNa le Tofek, 18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 21:44:37 http://yetibibgojo.net/2023/02/15/
25 viewsNa le Tofek, edited  18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 08:17:47 ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሰጠ መግለጫ

በረዥሙ የሀገረ መንግሥትነት ታሪካችን ውስጥ ኢትዮጵያ ያለፈችባቸው ወሳኝ የታሪክ አንጓዎችና ውጣውረዶች ብዙ ናቸው። ቢሆንም ግን በታሪካችን ሂደት በገጠሙን ፈተናዎች ወድቀን ሳንቀር ፈተናዎችን በአኩሪ ገድል እየተሻገርን አኩሪ አገራዊ የጋራ እሴቶችን አፍርተን ከዚህ ደርሰናል።

ስለሆነም ይኸኛው ትውልድ የተረከባቸው በከፍተኛ ውጣውረዶች መካከል ተፈትነው ያለፉ፣ የነጠሩና በጋርዮሽ መስተጋብሮቻችን የተሳለጡ እጅግ የምንኮራባቸው የባሕል፣ የትውፊትና የታሪክ ሀብቶቻችን ዘርፈ ብዙ ናቸው።

በውልና በገሃድ እንደሚታወቀው በዘመናችን ሁሉ ላካበትናቸው አገራዊ እሴቶች እንደ ሌሎች ቀደምት ሃይማኖቶች ሁሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተጫወተችው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡

በታሪክ ሂደታችን ውስጥ እያጋጠሙን ከምናልፋቸው እንደ አንዱ የሚቆጠር ችግር ሰሞኑን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተፈጥሯል፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰውን ይህንን ፈተና በትኩረት ሲከታተለው ቆይቷል፡፡

በመሆኑም መንግሥት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በውስጧ የተፈጠረውን ችግር በቤተ ክርሰቲያኗ ሕግ እና ሥርዓት መሰረት መፈታት አለበት የሚል እምነት በመያዝ ጉዳዩን ሕገ ቤተ ክርስቲያን እና ቀኖናው በሚፈቅደው የአሠራር ስርዓት እንዲፈታ የበኩሉን አስተዋጽኦ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

ይሁን እንጅ የተፈጠረው ችግር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕግጋት መሰረት መፈታት ሲገባው ባለመፈታቱ ምክንያት ችግሮች በመባባሳቸው በሃገራችን አንዳንድ አካባቢዎች ለሰው ልጆች ሕይወት መጥፋት፤ አካል ጉዳት እና የምዕመናን እንግልት መድረስ የክልሉ መንግሥት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለጸ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን እረፍተ ነፍስ እንዲሰጥልን ቤተሰቦቻቸውን እና ወዳጅ ዘመዶቻቸውንም ፈጣሪ መጽናናትን እንዲያድልልን እንመኛለን፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መግሥት የጉዳዩን አሳሳቢነት እና አደጋውን በመገንዘብ እጅግ በበሰለ መንገድ በመጓዝ ታላቋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድነቷ ጸንቶ እና ተጠብቆ እንዲቀጥል እና የተፈጠረው ችግር በውይይት እንዲፈታ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል።

በሌላ በኩል ደግሞ ከውይይቱ የሚያፈነግጥ አካል ካለ በሀገሪቱ ሕግ እና ስርዓት መሰረት እንዲፈታ ቤተ ክርስቲያኗ አቅጣጫ አስቀምጣ ሲሠራ የነበረበትን መንገድ እና የተሄደበት ርቀት የሰከነ እና ጥበብ የተሞላበት ትክከለኛ አካሄድ መሆኑን ይገነዘባል፡፡

ስለሆነም የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማስጠበቅ የተሄደበትን ርቀት እያደነቀ በዛሬው እለት በፌደራል መንግሥት እና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል በተካሄደው ውይይት መግባባት ላይ በመደረሱ የተሰማውን ደስታ ይገልጻል፡፡

በቀጣይም ለረጅም ዘመናት ጸንታ የቆየችው ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድ መንበር፣ አንድ ሲኖዶስ እና አንድ ፓትርያርክ የሚለውን የቤተ ክርስቲያኗን ሕግና ቀኖና ተፈጻሚነት እንዲኖረው ሁልጊዜም ድጋፉን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ያስገነዝባል፡፡

የሃይማኖት አባቶችም ችግሩ ካጋጠመበት ጊዜ ጀምሮ የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ ለማድረግ ጉዳዩ በሕግ እና ስርዓት እንዲፈታ ያሳዩት ትእግስት እና አስተውሎት የተሞላበት ተግባር ትምህርት የሚወሰድበት እና በቀጣይ ለሚያጋጥሙ ችግሮች አርዓያ የሚሆን ነው፡፡

መላው የክልላችን ሕዝብ እና የቤተ ክርስቲያኗ ምዕመናንም ችግሩን ከሰማንበት ጊዜ ጀምሮ ሃይማኖታዊ ስርዓቱ በሚፈቅደው እና ቅዱስ ሲኖዶስ በወሰነው መሰረት ችግሩ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ በጾም፣ በጸሎት እና ምህላ ላበረከታችሁት ፍጹም ሰላማዊ፣ የሰከነ እና በአስተምህሮት የጸና አካሄድ መንግሥት ላቅ ያለ ምስጋናውን ያቀርባል።

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
26 viewsNa le Tofek, 05:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 22:34:52 ለመጀመሪያ ጊዜ ቡርቧክሶች ቀየ ዘለኩ ….

ሙዚቃ ሳይንስ ነው፡፡ ሙዚቃ ሀይማኖት ነው፡፡ ሙዚቃ ፖለቲካ ነው፡፡ በቃ ሙዚቃ የሁለንታ (Universe) ወኪል ነው፡፡

“ዳዊት በበገናው፣እዝራም በማሲንቆው የእግዚአብሔርን እናት ቅድስት
ድንግል ማሪያምን አመስግነው ሞትን ሳይቀር እንደ እንቅልፍ
አቅለውታል፡፡

የመፅሃፍ ቅዱሱን እዝራ የመሰንቆ ውርስ ለማግኘት ጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት ከተማ ቡርቧክስ መንደር ላይ በመሰንቆ ድምፅ ከትመናል፡፡ ቡርቧክስ የአዝማሪዎች መንደር ናት፡፡ እነ ኤሊያስ ተባባል፣ እነ የሺ እመቤት ዱባለ--- ርቄ ሳልጓዝ ወንድሜ ወረታው እህቴ ሀረግም ሰፈራቸው እዚሁ ነው፡፡ ቡርቧክስ!!!

አበው ስለብርቧክስ ሲናገሩ መነሻቸው ነገስታቱ ናቸው ጎንደርን አፄ ፋሲለደስ በዝግ ፖሊሲ አረጋግተው እስከ ተከታዮቻቸው ለሁለት መቶ ዓመታት በሰላማዊ ሁኔታ መርተዋል፡፡ ሌላው ጊዜ የደርቡሽ ፣የመሳፍንቱ እና የሌላው የጦርነት ጊዜ ነበር፡፡ በደርቡሽ( በሱዳን)ጦርነቱ ጎንደር ማክሰኝት አካባቢ ከብቶች አለቁ፡፡ የጦር መሳሪያዎች ወደሙ፡፡ የትሬዛ ብር ወደመ፡፡ ብር እንደኳስ ተጠለዘ፡፡ ብር ኳስ ሆነ፡፡ ቡርቧክስ መነሻው ይሄው ነው፡፡ በተኮላተፈ አማርኛ ብር እንደ ኳስ ማለት ነው፡፡

ቡርቧክስ የአዝማሪዎች መንደር ነው፡፡ የቡርቧክስ ተወላጅ ከወላጁ የሚወርሰው ከፈረስ ጭራ እና ከወይራ እንጨት የተሰራ መሰንቆ እና የሰም ለበስ ቅኔ ግጥምን ነው፡፡ መሰንቆ በአንድ ክር የትኛውንም የሙዚቃ ምት የሚያወጣ ነባር የሙዚቃ መሳሪያ ነው፡፡ አዝማሪም፣ መሰንቆን ከመዘወር ጀምሮ ሰም ለበስ ግጥምን እስከ መቀኘት የመጠቀ ምናብ ያለው የጥበብ ሸራ ነው፡፡

መቸሞ በኛ ሀገር ታሪክ ፈረስ ና መሰንቆ የተጫወቱት ሚና ቀላል አይደለም፡፡ አዝማሪ ጣዲቋን ብቻ እናስታውስ፡፡ ፡በአድዋ ጦርነት ብዛት ያለው መሰንቆ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡አዝማሪ ጣዲቋም በመሰንቆዋ ቅኝት ወታደሩን በወኔ በማጋል፣ጠላትን በማደናበር የአድዋ ተራሮችን ተቀኝታባቸዋለች፡፡

አዝማሪ ከግዕዝ ወደ አማርኛ ሲተረጎም አመሰገነ ማለት ነው፡፡ እዝራ በመሰንቆ አምላኩን አመስግኗል፡፡ የኛ ሀገር አዝማሪዎች ጀግናን አመስግነው፣ፈሪን ነቅፈዋል፡፡ ተችተዋል፡፡

አዝማሪ፣ፊት ለፊት ተናጋሪ ብቻ ሳይሆን፣የህዝብ ብሶት መተንፈሻ አባሪ እስትንፋስ ነው፡፡ለዚህም ነው ጃንሆይ ( ቀኃስ) በአዝማሪዎች አጥኝ እየላኩ የማህበረሰባቸውን ስሜት ያዳምጡ
የነበረው፡፡ህዝብን እስከ ፍላጎቱ ከአዝማሪዎች አንደበት ይገኝ ነበርና፡፡

በኃላ ግን ከደርግ ዘመነ መንግስት ጀምሮ መንግስትን አዝማሪዎች እንዳይተቹ ሲባል አዝማሪነትን ማናናቅ፣ማዋረድ፣ማንቋሸሽ ተጀመረ-የደርግ ጠቅላይ ሚኒስትር ፍቅረ ስላሴ ወግደረስ በኛ ና አብዮቱ በተሰኘው መፅሃፋቸው እንደመሰከሩት፡፡

የጎንደር የቡርቧክስ አዝማሪዎች ግን መሰንቆቸውን ከትክሻቸው ሳያወርዱ ያባቶቻቸውን የጥበብ ገፀ በረከት አስከትለዋል፡፡ ዛሬም በዚህ ሰፈር ፖለቲካ፣ሃይማኖት፣ ፍቅር...... በመሰንቆ
ይወራል፡፡ ይመሰጠራል፡፡ ባህል ና ስነ ልቦና በቡርቧክስ አዝማሪዎች አንደበት ይተነተናል፡፡ከዚህች ሰፈር የጎንደር ስሜት፣የአማራ ስነልቦና ፣የኢትዮጲያዊነት መዳረሻ. .......በመሰንቆ ይገለፃል፡፡ እነሆ መሰንቆ እና ግጥም በአዝማሪዎች ደጃፍ፣
"""" ""''
አዝማሪው ይዘፍናል ማሲንቆ በዜማ እየከረከረ
የፈረስን ጭራ የፍየልን ቆዳ ባንድ እያናገረ
ግጥሙ ግን ከንቱ ነው ፍፁም ሀሳብ የለሽ
‹‹አልማዝ እንደምን ነሽ እናናየ እንዴት ነሽ››
ኤዲያልኝ አዝማሪ ኤዲያልኝ ማሲንቆ
ድምፅ ብቻ መስማት ሀሳብ ተደብቆ
ተቀበል አዝማሪ ተቀበለኝ ግጥም
ህይወቴን ዝፈነው ቅኝትህ እንዲጥም

‹‹እህህን እህህ…ዋሆየ ዋሆየ››
‹‹ጭራ ሆኜ ቀረሁ አንቺን ከፊት ብየ››
ተቀበል አዝማሪ ኑሮየን ተቀኘው
የመንከራተቴን ውሎየን ዝፈነው
ሀያ አመታት ሙሉ አገር ለጠበቀ
ላገሩ ዳር ድንበር የትም ለወደቀ
አስር አለቃ ነው የተሰጠው ማረግ
እያየህ ዝምያልከው እንዳይሆን ሲደረግ
ኧረ ተው ፈጣሪ ኧረ ተው ኧረ ተው
ግፌን ደበቁህ ወይ አንተንም እንደሰው
******
ተቀበል አዝማሪ ብሶቴን አዚመው
የማሲንቆህ ዜማ ጩኸቴን ይልቀቀው
‹‹እትብቴ ከወዲያ መቃብሬ ወዲህ››
‹‹በተወለድኩበት አልኖርኩም ከንግዲህ››
ሞኝነት ነበር ወይ ምሽግ ላይ ማርጀቴ
ሰው ኪሱን ሲሞላ ሀገሬን ማለቴ
ጅልነት ነበር ወይ ላገር መዘመሬ
ጦቢያ በሚሉት ቃል ሌት ተቀን መስከሬ
በጨርቅ ሱሪ ላይ ከስክስ ጫማ አድርጌ
ጉራማይሌ መልኬን ከሰዎች ሸሽጌ
ስራ ማስታወቂያ ከሚለጠፍበት
አየሁ ለኔ ሚሆን ግሩም የስራ አይነት
የስራ መደቡ የስራው መጠሪያ
ዘበኝነት ይላል የጥበቃ ሙያ
የስራ ልምዱ ላይ እዛ ሚፈለገው
በውትድርና የስራ ልምድ ያለው
እይልኝ እጣዮን ያገሬን ብሽቅነት
የሹመቴን ቦታ ርስትና ጉልት
እይልኝ አገሬን የገልቱነቷን ጥግ
ቀርፍታ ስትጥለው ህይወቴን እንደምርግ
******
እንዲህ ብለህ ዝፈን እንባየን ተውሰህ
እናናየ እንዴት ነሽ ስትል እንዳልሰማህ የኔን እምባ ትተህ
‹‹ምንድን ነው ውዳሴ ከንግዲህ ለጠላ››
‹‹የደረቡት ሁሉ ከሆነ ነጠላ››
‹‹ጠበቃሽ ማን ይሆን ዋስሽስ ማን ይሆን››
‹‹ነበረኝ ያልሽው ሰው እንዳልነበር ሲሆን››
አድሮ ጥጃ ነው ወይ ከቶ የኔ ሹመት
ካደባባይ ጓዳ ከእልፍኝ ወደ ማጀት
******
እንዲህ ብለህ ዝፈን ተቀበል አዝማሪ
ለዚች መናኛ አገር በቁሜ ቀባሪ
ወጥቶ ላደረ ሰው እድሜውን በሙሉ ጋራ ሲሰነጥቅ
አይጠብበትም ወይ ስርቻ መንደር ውስጥ ደጃፍን መጠበቅ፡፡

….. አቤት የግጥማቸው ለዛ የስንኝ አጣጣሉ ዛሬ እኔ ብያለሁ

የገጣሚው ግጥም ሀረጉ ስንኙ
ዘንድሮስ ያስብላል አይ ገጣሚ ሞኙ

ብቻ የሆነ ሆነና ዛሬ ስጓጓላት የነበረችውን የብርቧክሶችን የዋርካ ዛፍ አገኘኃት ብዙ ጥያቄዎችን ጠየኳት ምን ትሺ ይሆን አልኳት መልሳ ብዙ ጥያቄ ጠየቀችኝ በጣም ብዙ ጥያቄ ብቻ ብዙ ብዙ የቤት ስራ አለብን ክብር ለመሰንቆ እመለስበታለሁ

ቅዳሜ በጎንደር ከተማ ታላቅ የአዝማሪዎች ፌስቲባል በክብር ተጋብዛችኃል፡፡
90 viewsNa le Tofek, 19:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 22:34:50
82 viewsNa le Tofek, 19:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 18:39:21 9ኙ የጎንደር ሴቶች የእስክስታ ዓይነቶች

#ጉች_ጉች

በውዝዋዜ ወቅት ከሚያሳዩት የእስክስታ ትዕይንት አንዱ ጉች ጉች ይባላል። ይህ እስክስታ አንዲት ሴት ጥበበኛና ባለሙያ ከሚያሰኟት ነገሮች ውስጥ አንዱ እንጀራ መጋገር በመሆኑ ይህ ውዝዋዜ ሲጨፈር ሴቷ በእግሯ መዳፍ ቁጢጥ በማለት እየተሽከረከረችና ክብ በመስራት ዙሪያውን በመዞር የሴት ወይዘሮ መሆኗን እና የእንጀራ መጋገር ሙያ እንዳላት የምትገልጽበት የእስክስታ አይነት ነው።

#ዶሮ ውሃ ሲጠጣ

ሁለተኛው የእስክስታ አይነት ዶሮ ውሃ ሲጠጣ ይባላል። ይህ አይነት ውዝዋዜ ዶሮ ውሃ ሊጠጣ ከሚያደርገው የዶሮ ተፈጥሮ የተወሰደ የእንቅስቃሴ አይነት ሲሆን በታዳሚው አዕምሮ ውስጥ እንዲቀረጽ የተፈለገው ዋና ቁም ነገር የሴቷን የዶሮ ወጥ ሙያ ለመግለጽ ነው። ሲጨፈርም ሴቷ የመቀነቷን ጫፍና ጫፍ በመያዝ እጆቿን ወደ ጎን በመዘርጋት ቀስ በቀስ ከወገቧ ዘንበል እያለች ወደ ታች በመውረድ ልክ ዶሮ ውሃ ሊጠጣ ሲል እንደሚያደርገው ተወዛዋዧም አንገቷን ዝቅ ከፍ እያደረገች የምትወዛወዘው ውዝዋዜ አይነት ነው።

#ሰክስክ

ሦስተኛው የእስክስታ አይነት ሰክስክ የሚባለው ሲሆን በዚህ የእስክስታ አይነት ሊተላለፍ የተፈለገው መልዕክት የሴቷን አሳ የመስራት ሞያ ነው። አንድ አሞራ ወደ ወንዝ አሳ ለመያዝ ሂዶ ከያዘ በኋላ አንገቱን ዝቅ ያደርግና ከወደ አፉ ቀና በማለት አሳውን ለመዋጥ የሚያደርገውን ትግልና ትዕይንት መሰረት ተደርጎ የተቀዳ የውዝዋዜ አይነት ነው። አጨፋፈሩም የመቀነቷን ጫፍ እና ጫፍ በመያዝ ከአንገቷ ሰበር ከወገቧ ዘንበል በማለት ልክ አሞራ አሳ በማንቁሩ እንደሚያነሳው አንገቷን ወደላይ ቀና በማድረግ በአንገትዋና በትከሻዋ ወደ ላይና ወደ ታች እየወዘወዘች ትጨፍራለች።

#ድስቅ

ጌጣጌጦችን አሳምረው መስራት እንደሚችሉ ለማሳየት ደግሞ ድስቅ የሚባለውን የውዝዋዜ አይነት ይጠቀማሉ። ውዝዋዜው የሚጨፈረው በደረትና በትከሻ ሲሆን በሰርግ እና በተለያዩ ሃይማኖታዊ በአላቶች ላይ ሴቶች ለመልካቸው ውበት የሚያላብሳቸውን የሞያ እና የእመቤትነት ማዕረግ የሚያጎናጽፋቸውን ጌጣጌጦች በጸጉራቸው፣ በእጃቸው እና በ አንገታቸው አድርገው ይሄዳሉ።
እነዚህን ጌጣጌጦች የሚያዘጋጁዋቸው ራሳቸው መሆናቸውን ለማሳየት ድስቅ የተሰኘውን ውዝዋዜ ይጨፍራሉ። ይህ እስክስታ ሲመታ በደረታቸውና በትከሻቸው በሃይል ስለሚመታ አንገታቸው ላይ ያለው ጌጣጌጥ ዕርስ በእራሱ እየተላተመ ድምጽ ያሰማል። የብዙ ሰዎችን ቀልብም ይገዛል። የሰሯቸው ማጌጫዎች ጥራትና ውበት ይታያል። የሞያ ደረጃቸውን ከፍ አድርጎ ያሳያል።

#ቅቤ መናጥ

አምስተኛው የውዝዋዜ አይነት ቅቤ መናጥ ይባላል። ይህ ውዝዋዜ ሴቷ ስትወዛወዝ በርከክ ብላ የመቀነቷን ጫፍና ጫፍ በእጆቿ በመያዝ እጆቿን ወደፊት እና ወደኋላ እየዘረጋችና እያጠፈች የምትወዛወዘው ሲሆን ሊተላለፍ የተፈለገው ጉረና (ወተት የሚያዝበት እቃ) እየገፋች እና እየናጠች ቅቤ ለማውጣት የሚደረገውን ትዕይንት ለመግለጽ ነው። እንዲሁም የነጠላዋን ጫፍና ጫፍ በትከሻዋ እንዲወርድ አድርጋ በሁለት እጆቿ ጫፍና ጫፉን ከያዘች በኋላ ረጋ ብላ በቀስታ በመነቅነቅ አይነት ትወዛወዛላች። ይህም የወተት መናጫውን ማሰሪያ ገመድ ይዛ ወተቱ እንዳይደፋባት (እንዳይሸፍትባት) ቅቤው እንዲወጣ የመሰብሰብ አይነት ውዝዋዜ ነው።

#እንዝርት

ፈትል፣ ጥልፍና የተለያዩ አልባሳት አስጊጠውና አሳምረው መስራት እንደሚችሉ ለማሳየት ደግሞ እንዝርት የሚባለውን የእስክስታ ትዕይንት ሴቶች ይከውናሉ። የእንዝርት አሿሿርን መሰረት አድርገው በእጆቻቸው ቀሚሳቸውን ከጎንና ከጎን በመለጠጥ ልክ እንደ እንዝርት እየሾሩና እየተሽከረከሩ ይጨፍራሉ። እንዲሁም ቀጭን ፈታይ ባለሙያ ስለመሆናቸው ለመግለጽም ይጠቀሙበታል።
አቀራረቡም ልክ እንዝርት እንደያዙ በማስመሰል በጣቶቻቸው የመቀነታቸውን ጫፍ ይዘው እጃቸውን ወደ ላይ በመዘርጋት የላይኛውን መቀነታቸውን ጫፍ በጣቶቻቸው ጥጥ እንደያዙ በማስመሰል በመፍተል አይነት እንቅስቃሴ ይወዛወዛሉ። ቁጭ ብለው ሲወዛወዙ በ አንደኛው እግራቸው በኩል ያለውን ቀሚሳቸውን ሰብሰብ አድርገው እንዝርት እያሾሩ የሚፈትሉ በማስመሰል ይወዛወዛሉ። እንዝርትና ጥጥ ይዘው እየፈተሉ ሊወዛወዙም ይችላሉ።

#ዋንጫ ልቅለቃ

ሰባተኛው ዋንጫ ልቅለቃ የተባለው የውዝዋዜ አይነት ነው። የሴቷን የወይን አዘገጃጀት የጠጅ አጣጣል የጠላ አጠማመቅና ልዩ ልዩ መጠጥ ማዘጋጀት እንደምትችል እና ባለሙያ መሆኗን ለማሳየት ዋንጫ ልቅለቃ የውዝዋዜ አይነትን ይጠቀማሉ።

በዚህ ውዝዋዜ እሷ ያዘጋጀችውን ወይን፣ የጠመቀችውን ጠላ ፣ የጣለችውን ጠጅ ማንም ቀምሶ አይተወውም። የተሰጠውን መጠጥ ከመጣፈጡ የተነሳ ልቅልቅ (ጭልጥ) አድርገው እንጠፍጣፊ ሳያስቀሩ እንደሚጠጡት ማሳያ ነው። በሌላ ጎን ደግሞ ከላይ በተጠቀሰው ሃሳብ በተቃራኒ የጠላ ወይም የጠጅ መጠጫውን ሌላ ቃና እንዳይኖረው በጠጅ ወይም በጠላ ያለቀልቁ ስለነበር ነው ዋንጫ ልቅለቃ የተባለው የሚሉም አሉ።

ይህ የእስክስታ አይነት ሴቷ የመቀነቷን ጫፍና ጫፍ ከቀሚሷ ጋር ደርባ በመያዝና ወገቧ ላይ እጆቿን አድርጋ አንገቷን በእርጋታ ከግራ ወደ ቀኝ ፣ ከቀኝ ወደ ግራ ልክ ዋንጫ እንደሚለቀለቅ ተደርጎ በመነቅነቅ በማሽከርከር የሚጨፈር የእስክስታ አይነት ነው።

#ማንጠርጠር

ስምንተኛው የጎንደር እስክስታ አይነት ማንጠርጠር ሲሆን ይሄ ውዝዋዜ ተወዛዋዧ በአንድ እጇ የአንደኛውን መቀነት ጫፍ በመያዝ የተወሰነ ከፍታ ከፍ በማድረግ፣ በሌላኛው እጇ የሌላኛውን መቀነቷን ጫፍ በመያዝ ዝቅ በማድረግ ልክ ሰፌድ ይዛ እህል እንደምታጣራ ሴት ትወዛወዛለች።

በሃገራችን በእርሻ ፣ በቤት ስራ ፣ በሰርግ ፣ በድግስ ወንፈል በመግባት መረዳዳት የተለመደ ነው። ሴቶችም በልዩ ልዩ ሞያ ለምሳሌ በጥጥ ፈተላ ፣ በጥልፍ ፣ በወቀጣ ፣ በእንጀራ ጋገራ በመሳሰሉት ይረዳዳሉ። ይሄን መረዳዳታቸውን አንድነታቸውን ለማሳየት ወገብ ለወገብ ተያይዘው የሚወዛወዙት እስክስታም ተጠቃሽ ነው።

#መንጠቅ

ከሴቶች በተጨማሪ ወንዶች የሚጨፍሯቸው የውዝዋዜ አይነቶም አሉ። ከእነዚህ አንዱ መንጠቅ ይባላል። ይህ ውዝዋዜ ከፈረስ ግልቢያ ጋር የተያያዘ እንቅስቃሴ ያለው የውዝዋዜ ዐይነት ሲሆን ውዝዋዜውም የሚቀርበው በጦር ሜዳ ጊዜ ግንባር ቀደም ጦር አብሳሪው በሆነው የፈረስ ግልቢያ ዓይነት እንቅስቃሴ ነው።
በዚህ የውዝዋዜ አይነት ሊተላለፍ የተፈለው መልዕክት ጥሩ ፈረስ ጋላቢና የጠላትን ጦር በፈረስ ሸምጥ ግልቢያ ሰብረው በመግባት ጠላትን ደምስሶና ትጥቅ ነጥቀው መውጣት የሚችሉ ልበ ሙሉዎችና ደፋሮች መሆናቸውን ማሳያ ነው።

በእስክስታ ጊዜ ሊታዩ ከሚችሉት ነገሮች ውስጥ ቀረርቶ ሽለላና ፉከራ በዋነኝነት የሚጠቀሱ ሲሆኑ ቀረርቶ በአንድ ጉልበታቸው በርከክ በማለት ጠቋሚ ጣታቸውን ጆሯቸው ላይ አድርገው አንገታቸውን በቁጭት መልክ እየነቀነቁ የሚያሳዩት ትዕይንት ነው። ይህም ሃገር ተወረረ ደንበር ተደፈረ በተባለ ጊዜ በንዴት እያቅራሩ “ያልሰማህ ተነስ ስማ” በሚል አይነት ለጦርነቱ ሌሎችን የማንቃት ምሳሌ ነው። ስለዚህ ጣታቸውን ጆሯቸው ላይ ማድረጋቸው "ስማ ተነስ" የሚል ትርጉም አለው።

ምንጭ፡- ከተለያዩ ድህረገፆች
38 viewsNa le Tofek, 15:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-06 19:04:39 ‘ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ’ (ዛሬ የዓለም ቤዛ ተወለደ)
እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሰ
36 viewsNa le Tofek, 16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ