Get Mystery Box with random crypto!

ABX

የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX A
የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX
የሰርጥ አድራሻ: @muhammedseidabx
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.70K
የሰርጥ መግለጫ

ወደ ቤታችሁ እንኳን መጣችሁ!!

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2021-12-21 12:53:10 https://twitter.com/viswoow/status/1472546426601283589?t=LipbWP1zILo6IiX2CZceWA&s=19
304 views09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-19 21:32:28 ደጋጎች ከሶላት ጋር የነበራቸው ሁኔታ
ወኪዕ እንዳለው
-        አል-አዕመሽ ለሰባ ዓመታት ያህል የሶላት መክፈቻ ተክቢራ አምልጦት አያውቅም፤ (ታሪኽ በግዳድ ፡ 5/10)
ኢብኑ ሰዕድ ሲናገር
-        “ለሰላሳ ዓመታት ያህል ቤት እያለሁ አዛን ወጥቶብኝ አያውቅም፡፡” ብሏል (ወፊያት አል-አዕያን ፡ 2/375)
ሱፍያን ኢብኑ ዑየይነህ
-        “ከኢቃማ በፊት መስጊድ መገኘት ሶላትን የማክበር ምልክት ነው፡፡” ብሏል፡፡ (ሲፈቱ ሲፍዋ ፡ 2/35)
ኢብኑ ሙዒን እንዲህ ይላል፡-
-        “ኢብራሂም ኢብኑ መይሙን ብረት ለመምታት መዶሻ አንስቶ እያለ አዛን ቢወጣ መልሶ አይመታበትም፡፡” (ተህዚህ አት-ተህዚብ ፡ 1/151)
ሱፍያን ኢብኑ ዑየይነህ እንዲህ ይላል፡-
-        “አዛን እስኪወጣ ድረስ መስጊድ እንደማይመጣ እንደ መጥፎ በርያ አትሁን ፤ አዛን ሳይወጣ በፊት መስጊድ ግባ” (አት-ተብሲረህ ፡ 1/137)
ኢብራሂም አን-ነኸዒ
-        “ከኢማሙ ጋር ሶላት ከመጀመር ችላ የሚል ሰው ካየህ የሱ ነገር ይብቃህ” ብሏል፡፡
ሙሐመድ ኢብኑ አልሙባረክ
-        “ሰዒድ ኢብኑ ዐብዱልዐዚዝ የጀመዓ ሶላት ያለቅስ ነበር” ብሏል፡፡ (ተዝኪረት አል-ሑፋዝ ፡ 1/319)
ዐዲ ኢብኑ ሓቲም
-        “ለመድረሱ የጓጓሁ ብሆን እንጂ የሶላት ሰዓት ደርሶ አያውቅም፣ ዉዱእ ላይ ሆኜ ብሆን እንጂ የሶላት ሰዓት ገብቶ አያውቅም፣” ብሏል


https://t.me/NejashiPP
848 views18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-19 14:53:12 እንዲሁ የአላህ ቀደር ሆኖ በጥልቀት ዉስጥህ የሚኖር ሰው አለ። መቼ እና የት እንዳወቅከው በትክክል ጊዜዉን አታስታውስም። በጽሑፉ እንጂ አታውቀዉም፣ አያውቅህም። አጠገብህ ሆኖ እየዳበሰህ አብሽር የሚልህ ይመስልሃል።
አብሽር ወንድሜ ሁሉ መልካም ይሆናል።
አብሽር የሚል የተላከላችሁ ሁሉ አብዝታችሁ አላህን አመስግኑ።
እሱ የተጎዱትን ለማጽናናት፣ ተስፋ የቆረጡትን ለማበርታት መልኣክን በሰው አስመስሎ ይልካልና።

በርቱ ለሌሎች መበርታት ምክንያት ሁኑ፣
ፈግጉ ለሌሎች መፍገግም ሰበብ ሁኑ፣


http://t.me/MuhammedSeidABX
139 views11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-18 06:55:54 ተገኘች …

*

ሳምንት ሆነው መሠለኝ፡፡
ከተቀጣጠርንበት ስደርስ በትንሷ ስኒ ከቀረበለት ማኪያቶ ጋር ተቀምጧል፤ ላዩ ላይ ያለዉን አረፋ በስሱ እየገፈፈ ነበር፡፡
“መርሐባ መሐመዱ!” አለኝ፡፡
አንዴ ፉት ካለለት በኋላ “አህ … ዋው.. አየህ ማኪያቶ ማለት ይህ ነው፤ …” አለና ፈጠን ያለዉን አዘዘልኝ፡፡
“እህ …” አልኩት ዉጤቱን ለመስማት፡፡
“አይቻት መጣሁ፡፡” አለኝ፡፡
“እናሳ”
“ማሜዋ አትሆንም”
“ምነው”
“እንደው ሰው የመጣም አልመሰላት፣ ሻሿ ወደኋላ ግማሽ ጭንቅላቷ ላይ ደርሷል፡፡ ዝምብላ ዉር ዉር ትላለች፡፡”
“እና”
“ልቤ አልፈቀደም፡፡” አለኝ፡፡ ወሬዉን በዚሁ ዘጋነው፡፡ ልብ ካልፈቀደ ሰው መግፋት አልወድ እኔ፡፡
ጠዋት አንድ ወዳጁ ነበር የሆነች ልጅ ላሳይህ ብሎ ይዞት የሄደው፡፡ ሲሄድ “ማሜዋ እስቲ ዱዓ አድርግበት የሆነች ልጅ ላይ ነው” ብሎኝ ነበርና፡፡

መስፈርቱ ብዙ አልነበረም “ረሕማ ያላት፣ የተረጋጋች” ይለኛል ብዙን ጊዜ፡፡

“ስንተኛህ ናት ይህች?” አልኩት ድንገት ፊት ፊቱን እያየሁኝ፡፡  “ለማየት” ማለቴ ነው፡፡
“ስድስተኛ ናት፡፡” አለኝ ቀለል አድርጎ፡፡

የሚፈልጋት ሴት ምን ዓይነት እንደሆነች በልቡ ከፃፈ ቆይቷል፤ አንዴ ጠቁሜው አትሆንም ካለኝ በኋላ እንዲህ እንዲያ አድርግ ብዬው አላውቅም፣ ይህችን ያችን አግባ ብዬም አልተጫንኩትም፡፡
አንዳንዴም ፍለጋ ጀምሮ በመሃል ያቋርጣል፡፡ ጉዳዩን ይረሳል፡፡ እንደገና ድንገት በሆነ ምክንያት ትዝ ሲለው ወይ እናቱ ስትማፀነው፣ ወይ እህቶቹ ሲጮኹበት እንደ አዲስ ይጀምራል፡፡

እኔም ልቡ በነገረው በራሱ ጊዜ ያድርገው ብዬ ከተውኩት ቆዩሁ፡፡
ባቀረበልኝ ሪፖርት መሠረት የተወሰኑትን ለምን እንደተው መለስ ብዬ ለማስታወስ ሞከርኩ፡፡

አንዷ - ዝምተኛ ናት፣ ምንም ምንም አትናገርም፣ እስቲ በዚህ ለፍላፊና በተጫዋት ባህሪዬ ከዚህች ጋር እንዴት እኖራለሁ! አለኝ፤

ሌላኛዋን ወዶ ነበር ግን አጠረችብኝ ደግሞም ልጅ እግር ናት፣ መግባባቱ የሚከብድ መሰለኝ አለኝ፡፡

ሦስተኛዋ ቀውላላም ቀልቃላም ናት፣ ሐያእ የፈጠረባት አትመስል፣ ትፈጥናለች ብዙ ታወራለች፡፡

አራተኛዋን ደግሞ ወደዳትና አነጋገራት፣ ራሷን ቆለለች፣ መስፈርቷን ደረደረች፣ ከመስፈርቶቿ ከአንዱም መውረድ አልፈለገችም፡፡ የራሷን ጥቅም አስጠባቂ ብቻ መሠለችበት፡፡ እናም ተዋት፡፡

 ስድስተኛዋ የዲኗ ጥንካሬ ነገር አጠራጠረው፣ እኔም ደካማ እሷ ደካማ እንዴት ልንዘልቀው ነው ብሎ ፈራ፡፡ ከፈሩ ደግሞ መተው ይሻላል አለኝ፡፡

አምስተኛዋን በስድስቱ መካከል እኔ ረሳሁኝ፡፡ እነኚህን ማስታወሴም ራሱ በቂ ነው፡፡

ይኸው ዛሬ በሌሊቱ ቴክስተ አደረገልኝ፣ የተላከው ቴክስት ሌሊት ስምንት ሰዓት አካባቢ፡፡ አልተኛም ማለት ነው አስቡት፡፡  
“ተገኘች” ይላል በአጭሩ፡፡
“አልሐምዱ ሊላህ!” ብዬ መለስኩለት፡፡

ዝርዝሩን ሌላ ጊዜ እናወራበታለን፡፡
ከሱ ጋር ማለቴ ነው፡፡

ግና አንድ ነገር ባስታዉስ ብዬ ወደድኩ፡፡

የደረሳችሁ ሴቶች ሆይ! ወንድማችሁ ወይም ሌላ ሰው አንድ ባዕድ ሰው ቤታችሁ ይዞ ከመጣ ሊያየኝ ነው ያመጣው ብላችሁም ጠርጥሩ እስቲ፡፡ ሆ ….
 
727 viewsedited  03:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-17 06:28:48 እጠይቃለሁ

በመንገድህ መኖር ፈልጎ ላልሆነለት፤
ፍፁም በሆነ መልኩ ሊታዘዝህ አስቦ ምኞቱ ላልተሳካለት በዚህ ባርያህ በኔ ጉዳይ ምን ወስነህ ይሆን ጌታዬ? ስለኔ ምን አልክ ያ ረብ!


ሰባሐል ኸይር


http://t.me/MuhammedSeidABX
 
 
93 views03:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-16 20:44:58 ብዙዎች ለሙሐመድ ያለን ፍቅር ከ እስከ ተብሎ ወሰን የተቀመጠለት ይመስላቸዋል፣ አይደለም፡፡
ለርሣቸው ያለን ዉዴታ ለከት የለዉም፡፡ እንኳን እኛ ሕይወት የሌላቸው ፍጡራን እንኳን ሥማቸው ሲወሳ በብርቱው ይዐሽቃሉ፣ በርሣቸው ፍቅር ድንጋይ ሊያነባ ግንድ ሊያለቅስ ይችላል፡፡

የርሣቸው ሥም ሲነሳ ከተቀመጥንበት የሚፈነቅለን አንዳች ነገር አለ፣ መላ አካላታችንን የሚቆጣጠር ልዩ የሆነ ስሜት አለ፡፡

እርሣቸው ሲወደሱ በቆምንበት ንፋስ እንደመታው ዛፍ ልንወዛወዝ እንችላለን፤ ቀልባችን ከቦታዋ ልትነቃነቅ ትቀርባለች፡፡

በርሣቸው አትምጡብን፤
ፊዳከ አቢ ወኡሚ ያ ረሱለላህ!!



http://t.me/MuhammedSeidABX
629 views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-16 17:33:22 ያለንበትን ሁኔታ አላህ ያውቃል ፣ ይህ ብቻዉን በቂ ነው።

http://t.me/MuhammedSeidABX
385 views14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-16 05:50:28 አሁን ሰዓቱ የሱብሒ ነው፡፡
፨ በዉዱእ ጊዜ ወጣት ሁን በነሻጣ ዉዱእ አድርግ፣
፨ በሶላት ጊዜ ሽማግሌ ሁን ረጋ ብለህ ስገድ፣
፨ በዱዓ ጊዜ ህፃን ሁን አልቅሰህ ጌታህን ለምን፣

፨ በሶላታችሁ በርቱ፤ ከዚህ ዓለም የበለጠ እጅግ ያማረ አገር እየጠበቃችሁ ነዉና፡፡

፨ ማን ያውቃል የዛሬ ከባድ የጠዋት ብርድ ከነገው የጀሀነም እሣት ይጠብቀን ይሆናል፡፡

አላህ ሆይ ከሶላት የማይሰንፍ፣ ከዉዱእ የማይታክት፣ ልቦና ስጠን፣ በምትወዳቸው ሰዓታት ዉስጥም ንቁ አድርገን፡፡

http://t.me/MuhammedSeidABX
909 views02:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-15 10:51:29 'ሶሻል ሚዲያ ላይ የባሌን ፖስቶች ሳይ ከምርጥነታቸው የተነሳ የሱ ሚስት በሆንኩ ብዬ እመኛለሁ ።
ምክንያቱም ቤት ዉስጥ ከማየው ባህሪው ጋር ፈጽሞ አይገናኙምና።' ትላለች አንዷ።

ዶ/ር ጃሲም ናቸው ይህን የፖሰቱት።

ሐቂቃ እንዲህ ሆነን ነው የተቸገርነው፣ ፀሐፊነትና አስተማሪነት ፍፁምነት የሚመስለው ብዙ ሰው አለ።
ሲትራከ ያ ረሕማኑ።

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.6K views07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-15 09:50:24 አረጀሁ፣ ደከመኝ፣አበቃልኝ አትበል። ዉስጥህ ካልደከመ የአካልህ መድከም ምንም ማለት አይደለም።
ዛሬም እንደትናንቱ ተስፋንና ወጣትነትን ሰንቃችሁ ኑሩ፣ በራሳችሁም ሆነ በሰው ላይ ነፍስ ዝሩ።

ዱንያ እግር ኳስ ናት እያንዳንዷን ደቂቃና ሰከንድ ተጠቀሙ፣ እስከመጨረሻዋ ደቂቃ ድረስም ተሯሩጣችሁ መልካሙን ሁሉ ተጫወቱ።

ሰው በኖረበት ነገር ላይ ይሞታል፣ በሞተበት ነገር ላይ ይቀሰቀሳል።


http://t.me/MuhammedSeidABX
1.2K views06:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ