Get Mystery Box with random crypto!

ሜርሲ እና ብዕሯ✍

የቴሌግራም ቻናል አርማ mercy_ena_berua — ሜርሲ እና ብዕሯ✍
የቴሌግራም ቻናል አርማ mercy_ena_berua — ሜርሲ እና ብዕሯ✍
የሰርጥ አድራሻ: @mercy_ena_berua
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.94K
የሰርጥ መግለጫ

ለ ሀሳብ አስተያየት t.me/mercy_bbot @Mercyabay

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-10 19:11:27 ከስሜ በፊት ሊያልቅ አንድ ክፍል ይቀረዋል።ምን ያህል ትምህርት እየሰጣችሁ እንደሆነ ባላውቅም ከብዙ እውነታዎች በጥቂቱም ቢሆን ጀባ እያልኳችሁ እገኛለሁ።በቀጣይ ደግሞ አዲስ ልብ ወለድ እጀምራለሁ።አሁንም ራማ ላይ እንደነበረው ከኢትዮጵያ ወጣ ባለ ስፍራ የሚከወንን ድርጊት አስቃኛችኋለሁ።ስለ አሸባሪዎች ስለ ስለላ ታሪክ ስንሰማና ስናነብ ነው ያደግነው።አሁን ደግሞ በእኔ ብዕር ያ ዓለም ይቃኛል።
ሃሳብ አስተያየት በ @Mercyabay እቀበላለሁ።
ብቻችሁን አታንብቡ ደግሞ ሌሎችንም ጋብዙ።
ይሄ ቤታችሁ ነው

ሰናይ ጊዜ

@Mercy_ena_berua
83 viewsMercy, edited  16:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 16:31:18 #ከስሜ_በፊት
ክፍል ዘጠኝ

"ይሀውላችሁ አንድ ጊዜ የተሳሳተ አረዳድ እንዳይኖራችሁ..."
"ዝም በል!" ከሪም ዓይኖቹን በቁጣ አፍጥጦ አቋረጠው።ወደ ፊት አንድ እርምጃ ተጠግቶት
"ከዚህ በላይ እንድትዋሸን አንፈልግም።ማብራራትም አይጠበቅብህም እኮ የፃፍከው ከበቂ በላይ አብራርተህ ነበር።"
"በእኛ ላይ ሪሰርች እየሰራህ ነበር?..በእኛ በድሃዎቹ ላይ!?"ባህሩ ነበር።
"እኛ በንፁህ ልብ ነበር የቀረብንህ።በንፁህ ልባችን አቀረብንህ።አንዳች ጥርጣሬ አልነበረንም።ህጋችንን የሻርነው ዛሬ ገና ነበር።ጥፋት እንደሆነ እየተሰማኝ ነበር ማስታወሻህን የገለጥኩት።አንድ ገፅ አንብቤ እተወዋለሁ ብዬ ነበር።ግን ስለ እኔ ስትፅፍ እንዴት ላቁም!? ስለ ጓደኞቼ ስትፈተፍት ምንም አይደሉም አያውቁም ብለህ ገመናችንን በአደባባይ ልታውጅ...ሰብአዊነት የሚባል ነገር አለ እኮ አማኑ..." ዝቅ ስትል እንባዋ ከመሬቱ ላይ ዱብ ዱብ አለ።
ዳንኤል ጥጉን ይዞ በዝምታ ይመለከታቸዋል።
ከሪም እጁን ሱሪ ኪሱ ውስጥ እየከተተ
"አሁን ወደ መጣህበት ትሄዳለህ ወይስ እኛ እንውጣለህ?" አለው።
አማኑኤል እንባው ባቀረሩ ዓይኖቹ ተመለከታቸው።
"እውነቱን ሳልነግራችሁ..." ፊቱ ላይ ያረፈበት ቡጥ ንግግሩን አቋረጠው።ዳንኤል ዘሎ ከሪምን ያዘው።አማኑኤል የተመታበትን በኩል በአንድ እጁ በመያዝ ቀና ብሎ ተመለከታቸው።
"ባንዳ... አንድ ነገር እናገራለሁ ብትል ልገድልህ ሁላ እችላለሁ።ህዲና ሳይጠፉ የጠፉትን አባትህን ፈልጋቸው።"
"አዎ አባቴ ጠፍቷል...እርሱን ለመፈለግ ስል ነው ከካናዳ ድረስ የመጣሁት።" ይሄን ሲናገር ድምፁን ከፍ አድርጎ ነበር።ዓይኖቹ ላይ የሞላው እንባ ጉንጩ ላይ ይፈስ ነበር።
"መዋሸት እንጂ መደበቅ ይቻላል ስትሉኝ አልነበር!?....እኔም ደበቅኳችሁ እንጂ አልዋሸሁም።አንድ ጊዜ ተረጋግታችሁ ስሙኝና ከዛ እሄድላችኋለሁ።አማኑኤል ከአንዱ ጥግ በሚገኘው በርኩማ ሄዶ ተቀመጠ።ቀና ብሎ ሲመለከታቸው ባህሩ ቀድሞ ፍራሹ ላይ ተቀመጠ....መዓዛም ከጫፉ ሄዳ ተቀመጠች ዳንኤል ከሪምን በእጁ እንደያዘ ወስዶ አስቀመጠው።
"ቤተሰቦቼ ከዚህ ሃገር ከወጡ አስር ዓመት ሆናቸው።እኔ ግን እዚህ መሆንን ስለምፈልግ እየተመላለስኩ በመሃል ነበርኩ።ሁሉ ነገር በሰላም እየሄደ ነበር አባቴ እስኪታመም ድረስ" ሁሉም ከጎነበሱበት ቀና ብለው ተመለከቱት።
* * *
ከስድስት ወር በፊት
ካናዳ


አማኑኤል የሆስፒታሉን በር በዝግታ በመክፈት ወደ ውስጥ ገባ።ከአልጋው ላይ አባቱን በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ሲያየው ውስጡ ክፉኛ ተሸበረ።አባቱ በመተንፈሻ(ኦክሲጅን) ነበር የሚተነፍሱት።ወደ ውስጥ በዝግታ በማምራት ከአጠገቡ ባለው ወንበር ተቀመጠ።አባቱ በፈገግታ ካዩት በኋላ ቀና በማለት ትራሱን በመደገፍ ተቀመጡ።
"አባዬ በአስቸኳይ እፈልግሃለሁ ብለሀኝ ነበር።ምንድነው በጣም አመመህ እንዴ!?"
"በጣም ልጄ በጣም አመመኝ"
አማኑኤል በመደናገጥ
"ታዲያ ሃኪሞቹን ልጥራልሃ..."ሊነሳ ሲል በእጁ ይዞ አስቀመጠው።
"እንደዛ አይደለም ልጄ።እኔን ያሳመመኝ ሌላ ጉዳይ ነው።"
"ምንድነው አባ አስጨነከኝ እኮ"
"ሁሉንም ለመናገር ህመሙ ፋታም አይሰጠኝ።እስከዛሬ አንተም እናትህም እኔን አታውቁኝም ከመጥፎ ባህሪዬ ውጭ።የምታውቁት የበግ ለምድ የለበሰውን ሰው ነው።ግን ተኩላ ነበርኩ።በበጎች ውስጥ ተመሳስዬ የገባሁ ተኩላ።ያየሁትን ሁሉ እየቀረጣጠምኩ የበላሁ ሆዳም ተኩላ።"
አማኑኤል የሚሰማው ለጆሮው ሰቀጠጠው
"አባዬ...."
"አስጨርሰኝ!....እኔና እናትህ ከመተዋወቃችን በፊት የእርዳታ ድርጅት ላይ እሰራ ነበር።ያኔ ንፁህ ነበርኩ።የበላዮቼ ግን በሰው መራብ የደለቡ ነብሰ በላዎች ነበሩ።ሳይገባኝ አነካኩኝ ከዘገየም ቢሆን ስደርስባቸው ላጋልጣቸው ብል እኔንም ሳላውቅ አነካክተውኛልና እስር ቤት እንደምበሰብስ ነገሩኝ በእናቴና አባቴም አስፈራሩኝ አማራጭ አልነበረኝምና ዝምታን መረጥኩ።እያደር ሁሉን ነገር ለመድኩት ለድሃዎች ተብሎ ከተላከው የእርዳታ ገንዘብ ወደ ኪሴ አስገባ ጀመር።ቀስ እያለ ከእነርሱ ብሼ ተገኘሁ።በመሃል እናትህን አገኘኋት እርሷ ለጌታ ልቧን የሰጠች ሴት ነበረች እኔ ደግሞ ለሌላኛው ጌታ ልቤን የሰጠሁ እና የተገዛሁ።እርሷን አግብቼ አንተን ከወለድሁ በኋላ ላቆመው ወስኜ ነበር ግን ታገልኩ ልቤንም ወደ ጌታ ልመልስ ሆንኩ የለመደው እጄ ግን አላርፍ አለ።መፅሃፉ ለሁለት ጌቶች ልትገዙ አይቻላችሁም ሲል እውነቱን ኖራል ለካ!...ለአንዱ ከልቤ ተገዛሁ ለአንዱ በማስመሰል ተገዛሁ።በድሆች እንባ የእኔን ቤት ገነባሁ።የእኔን ከርስ እየሞላሁ ከሌላቸው አጎደልኩ።ያ ስለ ሚያሰቃየኝ ነው እጠጣ የነበረው።ሰላማችሁን የነሳሁት።ጥሩ ልሆንልህ እየሞከርኩ አቃተኝ።ከገንዘብ ጋር የተፋቀረ ሰው ስለሌላው ግድ የለውም።ሰላም ካገኘሁ ብዬ ወደዚህ ሸሽቼ መጣሁ።ስራውን ብተወው እንኳ የትላንት ፀፀቴ በደሌ ቤቴን በየቀኑ ያንኳኳል።ችላ ብዬ ቆየሁ አሁን ግን በማላመልጠው እጅ ተያዝኩ።ይሄን ቀን ዘንግቼው ኖሮ ለጊዜያዊ ስል ዘላላማዊውን ገደልኩት።ትላንት በአልጋዬ ላይ ሆኜ ቢቀበለኝ ብዬ ንስሃ ገባሁ።አሁን ነብሴ ትንሽም እረፍት አገኘች።እርሷ እንዳመለጠች ይሰማኛል።እኔ ተነስቼ ስህተቴን ባርም ምንኛ ደስ ባለኝ ግን አርፍዷል።ለዛ አንተ ስህተቴን እንድታስተካክለው።ያበላሸሁትን እንድታቀናው።ያስለቀስኩትን አንባውን እንድታብሰው ወደድሁ።ወደ ኢትዮጲያ ተመለስና አባትህን ፈልገው።የጠፋውን አባትህን በድሆች ንፁህ ልብ ውሰጥ ፈልገው።ያኔ ሳይነካካ በፊት ንፁህ ልብ የነበረውን አባትህን ህዲና በንፁሃን ውስጥ ፈልገው።እነርሱን ሆነህ ህመማቸውን ታመህ ስቃያቸው እስኪገባህ ፈልገው ስታገኘው የዛሬውን ስህተቱን አርምለት።ያስለቀሳቸውን የትኛው እንደሆነ ሲገባህ እንባቸውን አብስ።ይሄኛው አባትህ የዘራውን አረም ከመሃከላቸው ንቀል።የነጠኳቸውን ሃቃቸውን መልስላቸው።አደራህን ልጄ...." ይሄን ብሎ አይኖቹን ከደነ እስከወዲያኛው።
* * *
"እኔም የጠፋውን አባቴን ፍለጋ እናንተ ጋር መጣሁ....."


ይቀጥላል......

@Mercy_ena_berua
107 viewsMercy, 13:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 20:04:04
ይቺን መልዕክት ላጋራችሁ እስኪ
ስሙትማ


@Mercy_ena_berua
213 viewsMercy, edited  17:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 19:45:09 #ከስሜ_በፊት
ክፍል ስምንት

"አማን እያበድክ ነው!?"
"አላበድኩም ቡራ" አማኑኤል በተረጋጋ ድምፅ መለሰለት።
"እያበድክ ነው እንጂ.."ብሩክ ከተቀመጠበት ወንበር እምር ብሎ ተነስቶ መንጎራደድ ጀመረ።
"እሺ ቢሮ ነው ያለነው ተረጋግተን እናውራ"
ብሩክ ወገቡን ይዞ አፍጦበት ከቆየ በኋላ ወደ ወንበሩ ተመለሰ ቁጭ አለ።
"በቃ ሁሉንም ነገር ጨረስክ አይደል...ከዛ ስፍራ ውጣ።አንተ ስትኖር እኮ ነው ሌሎችን ማኖር የምትጀምረው።ሉክ አት ዩር ቦዲይ የለህም እኮ መንምነሃል።"
"ቡራ የምልህ ግን ገብቶሃል!?እኔም እነርሱን ከመቀላቀሌ ከማወቄ በፊት እንዳንተ ነበርኩ።እንዳንተ አስብ ነበር....ካገኛኋቸው በኋላ ግን ፍፁም ሌላ ናቸው ሌላ።እነርሱ ያጡት ምግብ አይደለም ከጋንዳ ውስጥ ያገኙትን ትርፍራፊ በልተው መኖር የሚችሉ ናቸው።እነርሱ ያጡት ቤት አይደለም በየ ጎዳናው በየሸራው ውስጥ እራሳቸውን ማኖር ያስለመዱ ሰዎች ናቸው...."
"ታዲያ ምንድነው ያጡት?" ብሩክ በመገረም ጠየቀው።
* * * *
ብሩክ መኪናውን አማኑኤል ወደሚያዝበት እየነዳ ከአንድ ስፍራ ሲደርሱ እንዲያቆም ነገረው።ብሩክ ግራ ቀኙን ሲመለከት ከቆየ በኋላ
"አማን እዚህ መኪናዬን ማቆም አልችልም"
"ለምን!?"
"ይሄን ሰፈር በፊልምም ቢሆን አይቻለሁ።ገና እግርህ ከመኪናው ከመውረዱ ነው መኪናውን ፈታተው እንዳልነበር የሚያደርጉት።"
አማኑኤል ፈገግ እያለ "ለዚህ ነው አታውቃቸውም የምልህ።ፀባይ ከሌለህ አንተንም እንዳልነበረህ ወደ መጣህበት መነመንህን ይሰዱሃል።"
"ምን አልክ!?" ብሩክ በመደናገጥ ጠየቀው።አማኑኤል እየሳቀ ከመኪናው ወረደ።ብሩክ ግን ላለመውረደ አሻፈረኝ አለ።
ከጎዳናው ጥግ ድንጋይ ላይ ሰብሰብ ብለው ከተቀመጡት ውስጥ አንዱ ቀና ብሎ እንዳየ
"እንዴ አማኑ" ብሎ ሲነሳ ሁሉም ቀና ብለው አዩት።እየተንጋጉ መጥተው በየሙዳቸው ሰላም አሉት።ብሩክ ከመኪናው ውስጥ ሆኖ ሲያወሩት በመደነቅ ተመለከት።ወደ እርሱ አንዱን ይዞ ሲመጣ ብሩክ መሪውን አጥብቆ ያዘው።ልጁ የመኪናውን መስታወት ሲያንኳኳ ቀስ አድርጎ ከፈተለት።
"እእ አባቴ ፒስ ነው...ስለ መኪናህ ምንም ሃሳብ አይግባህ እኛ አለንላት።ቀና ብሎ በክፉ ዓይን የሚሾቃት እንኳ አይኖርም።...እስካሁንም አፍጥጠሻል አረ ውረጂ...." አማኑኤል እንዲወርድ በአንገቱ ምልክት ሰጠው።
* * * *
እቤቱን ዘልቃ ስትገባ ማንም አልነበረም ነበር።በእጇ የያዘችውን ፔስታል ከመሬቱ በማስቀመጥ ወደ ፍራሹ ተመለከተች።ተዝረክርኮ ነበር።ብልድልብሱን እያስተካከለች እያለ ወደ መደርደሪያው ተመለከተች።ዓይኗ ቀድሞ ያረፈው ማስታወሻው ላይ ነበር።ብልድልብሱን ወደ ቦታው መልሳ ፈራ ተባ እያለችም ቢሆን ከመደርደሪያው ማስታወሻውን አነሳች።ብዙ ካንገራገረች በኋላ ከፍራሹ ቁጭ በማለት የመጀመርያውን ገፅ ገለጠች።
* * * *
ብሩክ የሚያየውን ባለማመን ግራ ቀኝ ያማትራል።ሽታው አፍንጫውን ሲሰነፍጠው ከኪሱ ማስክ በማውጣት አደረገ።
"አማን እንሂድ በቃ"
"ገና መች አየህና..."
"ያየሁት ከበቂ በላይ ነው"
አማኑኤል ከቆሻሾቹ ክምር ጠጋ በማለት ከአንዱ ጉብታ ላይ ቆመ ብሩክም ተጠጋው።
በጣም ብዙ ወጣቶች እናቶች ህፃናት ልጅ ያዘሉ ከመኪና የሚራገፈውን ምግብ በፔስታል እያደረጉ እየተቀራመቱ ይበላሉ።ግማሹ የያዘውን ይዞ ይሄዳል።"
"ማለት አይሞቱም!?" ብሩክ የሚያየው ነገር ከአቅሙ በላይ ሆኖበት ነበር።
"እየኖሩ ነው እንግዲህ።" ከዛ ስፍራ ወጣ ብሎ በጠባብ መንገድ እየሄዱ ይመለከቱ ነበር።
ህፃናት ብርድ ያቆፈደደ ሰውነታቸውን እያከኩ በዛው ሰውነታቸው መሬት ለመሬት ከጓደኞቻቸው ጋር ሲንከባለሉ።በዛው እጃቸው እናታቸው ከጋንዳው ለቅማ ያመጣችውን ምግብ ሲቀራመቱ።እየዘገነነው ይመለከታል።ወጣቶች በሃይላንድ ለብርዱ ብለው የመኪና ቤንዚን ሲጠጡ ከወረቀት እራሳቸው እያበጁ ሲጋራ ሲሰሩና እየተቀባበሉ ሲያጨሱ ለእርሱ ከዓዕምሮው በላይ ነበር።ለሰዓታት አማኑኤል እያዞረ ከሳያው በኋላ ዝናብ መጣል ሲጀምር ወደ መኪናው አመሩ።ልጆቹ እየበሰበሱ በቦታቸው እየጠበቁለት ነበር።ብሩክ ባየው ነገር ተገረመ።አማኑኤል አመስግኗቸው ከኪሱ ገንዘብ አውጥቶ ሊሰጥ ሲል
"አረ አማኑ ባለፈው የሰጠሀን ይሀው እስካሁን አልነካነውም።ደግሞ ሁላችንም ወደየ ቤታችን ስለተመለስን ቤት ያፈራውን መብለት ጀምረናል።እማዬ ግን ያንን ልጅ ልባርከው አምጡት ስትል ነበር።"
አማኑኤል ፈገግ ብሎ
"በቃ ነገ እመጣለሁ ብሏል በልልኝ ይሄን ደግሞ ለእናትህ ቡና መግዣ ይሆናል ተቀበለኝ እኔ ስመጣ በአሪፉ ታፈላልኛለች"
"አብሽር" ብሎት ተቀብሎት ሄደ።መኪና ውስጥ እንደገቡ ብሩክ በረጅሙ ተንፍሶ
"በፊልም ላይ ሳያቸው እንደማንኛውም ሰው አሳዝነውኝ ተውኳቸው።በአካል ግን ከዓዕምሮ በላይ ነው"
አማን ፈገግ አለ የፈለገው ይሄንኑ ነበር።
* * * *
አማኑኤል ወደ ውስጥ ሲዘልቅ አራቱም ተቀምጠው አገኛቸው።እንደገባ ሲያዩ ከተቀመጡበት ብድግ አሉ።ፊታቸው ተቀያይሮ ነበር።መዓዛን ሲመለከት አልቅሳ እንደነበር ዓይኖቿን አይቶ ተረዳ።መዓዛ እጅ ላይ ማስታወሻውን ሲያየው ባለበት ደንግጦ ቆመ።ነገሮች ሁሉ እንደተበላሹ ለመረዳት ጊዜም አልፈጀበት።

ይቀጥላል.....

@Mercy_ena_berua
@Mercy_ena_berua
177 viewsMercy, edited  16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 20:52:33 መንፈሳዊ የፊልም ፅሁፍ ማለትም (Short movie scripts) የምትፈልጉ ከላችሁ በውስጥ መስመር አናግሩኝ አብረን መስራት እንችላለን።
@Mercyabay
251 viewsMercy, 17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 20:35:19 "የውስጥ ጩሀት" የሚለው ልብወለድ መንፈሳዊ ልብወለዶችን ለመፃፍ እንድደፍር ምክንያት የሆነኝ ፅሁፍ ነው።ቻናሉን የጀመርኩ ሰሞን በተከታታይ ይለቀቅ የነበረ ነው።ላላነበባችሁ ሃሳቡ ሳይጨመር ሳይቀነስ እነሆኝ።
ወደ መፅሃፍነት እቀይረዋለሁ ያልኩትም እንደተጠበቀ ሆኖ ማለት ነው
መልካም ንባብ

@Mercy_ena_berua
244 viewsMercy, edited  17:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 20:08:32 #ከስሜ_በፊት
ክፍል ሰባት

አማኑኤል የመሄድ ሃሳቡን ትቶ የእያንዳንዱን ህይወት ለማጥናት አብሯቸው ቆየ።አራቱም ያለምንም ጥርጣሬ አብረውት ይጓዙ ነበር።የእያንዳንዱ ህመም እየገባው ስሄድ የሚፅፈውም እየጨመረ አስተሳሰቡም እየተለወጠ ሄደ።ጓደኛው ብሩክ በዳንኤል ጥየቃ ሰበብ አንዳንዴ አብሯቸው ያሳልፍ ነበር።ዳንኤል መሉ ለሙሉ መንቀሳቀስ ሲጀምር ሌላ መምጫ ሰበብ ስላጣ አቤልን የሚያገኘው ብቻውን ሆነ።
* * * *
አማኑኤል ውጭ ላይ ቁጭ ብሎ በያዘው እንጨት መሬቱን እየቆፈረ በሃሳብ ሄዷል።ዳንኤል ከአጠገቡ ሄዶ በመቀመጥ አተኩሮ እያየው
"አማኑ ሰሞኑን ሃሳብ አብዝተሃል በሰላም ነው?"
አማኑኤል ቀና ብሎ ተመለከተውና በእጁ የያዘውን እንጨት ከመሬቱ እያሽከረከረ።
"ደህና ነኝ ዳኒ።የእናንተ ጉዳይ እያሳሰበኝ።"
"አንተ ደግሞ እኛ ምን እንሆንና ለእኛ የተፃፈልንን እኛው እንኖራለን።ባይሆን አባትህን ልታገኘው ከጫፍ እንደደረስክ መዓዚ ስትናገር ሰማሁ።ያኔ ስትመጣ በጣም ተረብሸህ ነበር የሃብታም ልጅ እንደሆንክ ያወኩት ወዲያው ነበር።"
አማኑኤልን ሁሉንም ነገር የደረሰበት ስለመሰለው ውስጡ ተረበሸ።
"ማለት....እንዴት አወቅክብኝ!?" ፈራ ተባ እያለ ጠየቀው።
"ድርጊትህ ይገልጥህ ነበር።አንተ ስትናገር ደግሞ አረጋገጥኩ።ባይሆን ፍፁም ሊገባኝ ያልቻለው እኛ ጋር ሆነህ ልትፈልገው መሻትህ ነው።"
"እርሱን አንድ ቀን እነግራችኋለሁ ብዬ አልነበር..."
"እኮ መች!?"
"አባቴን ሳገኘው።" ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደ ውስጥ ገባ።
* * * *
"እናትህ ደውለውልኝ ነበር"
አማኑኤል አፉ ላይ የነበረው ውሃ ትን ብሎት ከአፏ መለሰው። ብሩክ ተደናግጦ ከወንበሩ ተነስቶ አጠገቡ ደረሰ።አማኑኤል ጣቶቹን እያነሳ ደህንነቱን አረጋገጠለት።ዳዊት እየተነጫነጨ ወደ ቦታው ተመለሰ።
"ምን....ምን አለችህ?" መለስ ሲልለት ጠየቀው።
"ደህንነትህን ነው የጠየቀችኝ ደግሞ ስልክህ ብዙ ጊዜ ሞክራልህ አይሰራም።'ደውልልኝ' ብላሃለች::"
"ሌላ የነገርካት ነገር አለ!?" በስጋት ጠየቀው።
"አይዞህ ጓደኛዬ ስለምንም ነገር አልነገርኳትም።ለመዝናናት እንደመጣህ ነው የምታውቀው።እስከመቼ ነው ግን በውሸትህ የምትገፋበት?"
"አልዋሸሁም እኮ ቡራ።መልካምን ነገር ነው እያደረግኩ ያለሁት"
"አንተ አበዛሀዋ...በቀላል መንገድ እየተቻለ።አሜርካን ካከለች ሃገር መጥተህ እዚህ ያውም ጎዳና ላይ..."
"ቡራ በቃህ....ድሎት ያለው አልጋዬ ላይ አንድም ቀን በሰላም ተኝቼ አላውቅም።ይሀው ወር ሞላኝ ሰላማዊ እንቂልፍ እየተኛሁ።"
"ካልክ እሺ....እና መች ልትነግራቸው አሰብክ?"
"ከሰሞኑ...አንተ ያልኩህን ስራ አፋጥንልኝ!"

* * * *
አምስቱም ከፍራሹ ላይ ተሰይመው ምግቡን አሰፍስፈው ይጠብቃሉ።መዓዛ ትሪውን መሃከላቸው ላይ እንዳስቀመጠች ባህሩ አፏጨ።አጁን ሊሰድ ሲል መዓዛ በያዘችው ማማሰያ ቀደመችው።ሁሉም ወደ ዳንኤል ዞሩ።
"እኔ ልፀልይ?" ጆሯቸውን ባለማመን ዞረው ተመለከቱት።አማኑኤል ፈገግ ብሎ
"አታፈጡብኝ እንፀልይ...ጌታ አምላክ ሆይ ስለሰጠሀን ስለዚህ ምግብ እናመሰግንሃለን።ስለ ሰጠሀኝ ስለነዚህ ድንቅ ቤተሰቦችም ስምህ ብሩክ ይሁን።
ሁሌም አብረሀን ስላለህ እናመሰግንሃለን።አሜን።"
ዳንኤል ረዘም አድርጎ"አሜንን" አለ።ሌሎቹ ግን አይናቸውን ገልጠው እያዩት ነበር።
"አሁን መብላት ትችላለህ" ባህሩ ግን ፈዞ ነበር።አማኑኤል ፈገግ ብሎ ምግቡን ጠቅልሎ ሲያጎርሰው ነቃ አለ።
እየበሉ በዝምታ ይመለከቱታል።ዳንኤል ብቻውን ይፍለቀለቃል።ከሪም ውስጡ እያረረ:-
"አንተ ነህ አአ የከተብከው?...አንደዛ ባይሆን አትፍነከነክም ነበር።"
"መፀለይ የሃይማኖት መገለጫ አይደለም።እኔ ሁሌም እፀልያለሁ ግን በውስጤ ነው የምፀልየው።"
አለ አማኑኤል በሁለቱ በኩል የሚነሳውን ንትርክ ቀድሞ ለማርገብ።
"አፀላለይህ ግን የእነርሱን ይመስላል።" አለ በአፍንጫው ወደ ዳንኤል እየጠቆመ።
"ደግሞ የአፀላየይም ልዩነት አመጣችሁ።አቦ የማይናገረውን እንብላና የቡና ሰዓቱ ላይ ንትርካችሁን ትቀጥላላችሁ::" ባህሩ በብስጭት ተናገረ።
ተሳስቀው እየተሻሙ መመገብ ጀመሩ።
* * * *
አባቱ ከፊቱ እየቀደመ ሲራመደ አማኑኤል ባባዶ እግሩ ሆኖ ከኋላው ይከተለዋል።
"አባዬ ጠብቀኝ እንጂ!"
አባቱ ፍጥነቱን ጨምሮ ይራመዳል።አማኑኤል እርምጃው ወደ ሩጫ ተቀየረ።አባቱ ግን እጅግ እያራቀው ነበር።አማኑኤል እያለከለከ ጉልበቱን ይዞ ቆመ።
ዝቅ እንዳለ
"አ...ባ...ዬ...እ...ባ...ክ...ህ...ጠ...ብ...ቀ...ኝ"
"አጠገብህ ነኝ እኮ" አማኑኤል ቀና ሲል አባቱ አልነበረም።
"አ....ባ....ዬ"በድንጋጤ ከእንቅልፉ እየጮሀ ተነሳ።ሁሉም ከተኙበት ተደናግጠው ተነሱ።

ይቀጥላል.....

@Mercy_ena_berua
238 viewsMercy, edited  17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 17:40:07 የፀሎት ጊዜያችን
(ከ Kaltube የተወሰደ)

የግል የፀሎት ጊዜያችን ሳይስተጓጎል በቋሚነት ሲቀጥል መቼም ድንቅ ነገር ነው አንዳንድ ጊዜ ግን ጊዜውን መጠበቃችን ብቻ ሳይሆን ጊዜውን መዋጀታችንንም እርግጠኞች መሆን አለብን! (የፀሎታችንን ማለቴ ነው)

የፀሎት ጊዜን ስናስብ quantity ጥሩ ሆኖ ሳለ quality ግን አብልጦ አስፈላጊ ነው ብዬ አምናለሁ

Quality ደግሞ ልብ ይጠይቃል! በአካል ብቻ ሳይሆን በሁለንተና present መሆንን ይጠይቃል ! ፀጋው ዙፋን ስር መጥቶ አካል ብቻውን ቢደፋ ልብ ግን ክንፍ አውጥቶ ከጠፋ የፀሎት ሰዓት አልተዋጀም! አፍ ብቻ የባጥ የቆጡን ከሚያነበንብ ልባችን ከውስጠቱ ቢቃትት ነፍሳችን ገስግሳ ከአምላኳ ጋር ንክኪ ብታደርግ ፀሎታችን በርግጥ ውጤታማና effective መሆኑን እኛው ራሳችን ይታወቀናል!

ከዚሁ ጋር ተያይዞ ሌላው የፀሎት ጊዜን የሚዋጅልን ትልቁ ቁምነገር ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለን ወዳጅነት ነው! ምን መፀለይ (ፀ- ጠበቅ ብሎ) እንዳለበት የትኛው ጉዳይ ቀዳሚና አንገብጋቢ እንደሆነ መንፈሳዊው ዓለም ላይ ያለውን traffic ሁሉ መንፈስ ቅዱስ ጥንቅቅ አርጎ ስለሚያውቀው እሱ ራሱ እየመራንና ለመንፈሳችን መለኮታዊ ጉዳዮችን እያቀበለን ስንፀልይ ፀሎት አቀበት አይሆንብንም! የማያታክት የማይሰለች enjoyable experience ይሆንልናል!

ለአንዳንዶቻችን ደግሞ ስለፀሎት ያለንም መረዳት ምናልባት መቀየር ይኖርበት ይሆናል! አንዳንዴ ፀሎት ሳናውቀው የማጉረምረሚያ ቦታ የማማረሪያ አልፎ አልፎም የጭቅጭቅ ቦታ ወይ ደግሞ ማመልከቻ አስገብቶ ስሞታ አሰምቶ መሄጃም ቦታ ሆኖብን
ከሆነ የፀሎት ጊዜያችንን መልሶ ለመዋጀት መንቃት ያስፈልገናል!

"ህብረታችንም ከአባት ጋር ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው" 1ኛ ዮሐ 1:3 እንዲል ህያው ቃሉ ፀሎት በዋነኛነት አማኝ ከአምላኩ ጋር የቅርበት ህብረትና ግንኙነት የሚያደርግበት የወዳጅነት ጊዜና ቦታ ነው መሆን ያለበት!! ነፍስ አምላኳን ተጠምታ በወዳጅዋ ስር እርፍ ለማለት ናፍቃ የምትሄድበት! የአዳኝዋን ብሩህ ፊት አይታ የምትፅናናበት ፍቅር ሰጥታ ፍቅር የምትቀበልበት ቦታ!!

ከፍቶን ለምቦጫችንን ጥለን ሄደን እንኳን "ጌታ ሆይ እወድሃለሁ" ማለት ስንችል ብዙ ነገር ልባችንን አክብዶት መጥተን ስለነገሩ እንኳ በቅጡ ሳናወራ ቶሎ ሚመጣልን "አንተ እኮ ልዩ ነህ" "ስለኔ ደግሞ ታስባለህ! በኔ ላይ ያለህ ዓላማህ መልካም ነው! አምንሃለሁ! እደገፍሃለሁ እጠብቅሃለሁ! ማለት ስንችል በርግጥ ወዳጅነት መስርተናል! ህብረትም ሰምሮልናል!

ጌታ የፀሎት ጊዜያችንን የተዋጀ ያድርግልን!!

ተፃፈ በላሊ
06/28/22
ዶ/ር ላሊ -

@Mercy_ena_berua
226 viewsMercy, 14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 20:26:51 ብዕራችን የእንባችን ማበሻ ብቻ አናድርገው።
ግን ያልሆኑትንም ሆንን ብለንም መፃፍ አያስፈልገንም።ህይወትን በአንድ ገፅታ ብቻ አንገነባውም።ፀሃፊያን ቁስላችንን በብዕራቸው ሲያኩልን ብቻ የምናሞካሻቸው አይሁን።ብዕርንም የእንባ ማድረቂያ የንዴታችን መወጫ ብቻ አናድርገው።ከፈተና ወጣ ስንል ደስ የሚልም የህይወት ዘይቤ አለ።ሰይጣን ካደቀቀን በላይ እግዚአብሔር ምህረትን ያበዛልን ጊዜያቶች እጅግ ይልቃሉ።
That evil Devil በሃሳባችን "እግዚኣብሔር ከአንቺ/ተ ጋር ቢሆን ኖሮ" ብሎ የህይወታችንን መጥፎ ጠባሳዎች ውድቀቶች ከዘረዘረልን በላይ....እልፍ ብለን ማሰብ ከቻልን አንድ ጥያቄ እናነሳለን:-
"እግዚኣብሔር ከእኛ ጋር ባይሆን ኖሮስ!?" የሚል።ይሄን ጥያቄ ስናነሳ ብዙ ድንቅ መልሶችን እናገኛለን።

ሰናይ ምሽት

@Mercy_ena_berua
219 viewsMercy, edited  17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 20:25:21 #ከስሜ_በፊት

ክፍል ስድስት

"እንድታምነኝ እፈልጋለሁ ቡራ።ብዙ የቀሩኝ ነገሮች አሉ እነርሱን እስካሳካ ድረስ ሚስጥሬ ሚስጥርህ ይሁን።"
ብሩክ ካለማመን ማመኑ ስለሚሻል ብቻ ተቀበለው።
* * * *
"እንደብቃለን እንጂ አንዋሽም ነው ያልሽኝ አይደል ወደ እዚህ ህይወት ምን እንዳስገባሽ ማወቅ ፈለግኩ እና..."
"ከማንም ጎዳና ተዳዳሪ የተለየ ታሪክ የለኝም።ታሪካቸው ታሪኬ ነው አማኑ።"
"ምን አልባት ብትነግሪኝ እረዳሽ ይሆናል::"
"እንዴት?"
"ወደ ቤት ልመለስ ስለሆነ...እዛ እንደዚህ አይደለም።"
አጠገቡ ሄዳ ተቀመጠች።
"ልትሄድ?"
"የምፈልገውን እስካገኝ ነው እዚህ ያለሁት።"
"አባትህን አገኘሃቸው!?"
"እያገኘኋቸው ነው።"
* * * *
"አማኑ ይቅርብህ...እኔን የምታውቀኝ በምግብ ብቻ ይሁን።"
ፈገግ ብሎ አየው።
ባህሩ ዳቦውን እየገመጠ በዝምታ ቆየ።
"ለምንድነው የምትበላው!?"
"ለመኖር..."
"እርሱማ ሁላችንም ለመኖር ነው የምንበላው።"
"እውነቱን ንገረኝ ካልከኝ ሰለ ሚጨንቀኝ ነው የምበላው።ስጨነቅ ስጨነቅ ከምግብ ውጭ መሸሸጊያ ያለ አይመስለኝም።በቃ በዚህ ማጣት ውስጥ ሆኜ እንኳ እበላለሁ።እራሴን የምበቀለው በምግብ ውስጥ ነው።ምግብ ሚገድል ቢሆን ኖሮ ሟች ነበርኩ።"
አማኑኤል በመገረም አየው በእርሱ ውስጥ አንድም ቁም ነገር አገኛለሁ ብሎ ባለማሰቡ እራሱን ወቀሰ።
"ምንድነው ያጣሀው?"
"ያላጣሁትን ጠይቀኝ...ከሁሉ የተሻለውን ሰው ግን አጣሁ እናም ከሁሉም ወደ ተሻሉኝ ሰዎች መጣሁ።"
"ተምረሃል?"
"ወረቀቷን ነው!?.....ግቢ ጨርሼ ሰራተኛ ነበርኩ።"
አማኑኤል ተደናግጦ ተመለከተው
"ታዲያ ለምን...?"
"ሰው አጥቼ አልኩህ እኮ አሙ...አሁን ብዙ አትዘብዝበኝ ስለ እራሴ እንኳን አውርቼ ጥቂቷን ሳስብ እታመማለሁ።በርገር መች ነበር እጋብዝሃለሁ ያልከኝ?"
* * * *
"ሰለ እኔ ብዙ ለማወቅ አትድከም አማኑ።እኔ ታሪክ የለኝም።"
"ለምንድነው ሃይማኖትህን ይሄን ያህል የምትወደው!?"
"ሃይማኖት አይደለም ክርስቶስን ነው የወደድኩት...ከእርሱ ጋር ነው ፍቀር የያዘኝ።እንደሚገባኝ አላውቀውም ለዛም ነው ለጓደኞቼ ላወራቸው እኔ ያገኘሁትን ሰላም ልገልጥላቸው ያልቻልኩት።"
"እንዴት!?"
"እኔ ጌታን የተቀበልኩት አምና ነው።ዓመትም አልሞላኝ።እዚህ መጥተው ሲሰብኩ ሰማሁ ተሸነፍኩለት።እርሱን ካስተዋወቁኝ በኋላ እነርሱ ስለምን እንደተዉኝ አላውቅም።ግን የነገሩኝን አልተውኩትም።ሰዉን አውቀዋለሁና እነርሱን ከክርስቶስ ጋር አላነፃፀርኩም።በቃ አፈቀርኩት ግን አላውቀውም።ሁሌ ከማነባት ያኔ ሲመሰክሩልኝ በነፃ ከሰጡኝ ትንሿ መፅሃፍ ቅዱሴ በስተቀር እውቀቱ የለኝም።"
"እንዲያስተምሩህ አልነገርካቸውም!?"
"ስልክ ስላልነበረኝ የከሪምን ሰጠኋቸው።ይደውላሉ ብዬ ብጠብቅ ብጠብቅ የውሃ ሽታ ሆነው ቀሩ።ምን አልባት ቁጥሩ ጠፍቶባቸው ይሆናል።ሌሎችን የማግኘት እድሉ ነበረኝ ግን አልቻልኩም።"
* * * *
"ድህነትን ይሄን ያህል እየጠላህ ለምን ለመስራት አልሞከርክም!?"
ከሪም ጥቂት ፈገግታ አሳየው
"እናቴ ስትሞት ውስጤም አብሯት ሞተ።ከዛ በኋለ በምንም መንገድ አቅምን ማግኘት አልቻልኩም ነበር።የሰው ልጅ ውስጡ ከሞተ ሞተ ነው።ለሞቱም ተገዢ ነው።ስጋህ ቢፍጨረጨረ ዋጋ የለውም።የሞተ ሰው ምንም ሊያደርግ አይቻለውም አማኑ።"
* * * *
"የጨረስኩ መስሎኝ ነበር።ያወኳቸው።የጨረስኳቸው።ዛሬ ሁሉንም ላወራቸው ሞከርኩ።ገና መች የህይወታቸውን መዝገብ መግለጥ ጀመርኩና!?የማያልቁ እልፍ ናቸው።እነርሱን ሳላውቅ ከዚህ ወዴትም አልሄድም።ለብሩክ የገባሁለትን ቃል ኪዳን አፈርሰው ይሆናል።ግን አባቴን ፈልጌ አላገኘሁትም።ገና ብዙ ይቀረኛል።" ማስታወሻውን ወደ መደርደሪያው መለሰው።

ይቀጥላል...

@Mercy_ena_berua
245 viewsMercy, edited  17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ