Get Mystery Box with random crypto!

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

የቴሌግራም ቻናል አርማ mahibere_kidusan — ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
የቴሌግራም ቻናል አርማ mahibere_kidusan — ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
የሰርጥ አድራሻ: @mahibere_kidusan
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 29.91K
የሰርጥ መግለጫ

The channel of mahibere kidusan

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-05-01 19:57:37 ንጉሥ ዱድያኖስም ስለዚህ ነገር ቅዱስ ጊዮርጊስን ጽኑ ሥቃይን አሠቃየው፤ ከአንድም ሦስት ጊዜም አስገደለው፤ ሆኖም ግን እግዚአብሔር አምላክ ከሞት ያስነሣው ነበር፤ ቅዱሱም “ይህን ከሀዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰድ” በማለት እግዚአብሔርን ስለመነ እንደጸሎቱ ተደርጎለታል። ነገሥታቱ የሚያመልኩትን ጣዖት ያጠፋ ዘንድ ወደ ፈጣሪው በጸለየ ጊዜ ምድር ተከፍታ ውጣዋለች፤ ጣዖታቱን ያገለግሉ የነበሩትንም አጥፍቷቸዋል፡፡ (መጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ሚያዚያ ፳፫)

ንጉሡም በዚህ ተቆጥቶ የቅዱስ ጊዮርጊስ ራስ እንዲቆረጥ ባዘዘው መሠረት በሚያዚያ ፳፫ ቀን ሰማዕትነቱን ፈጸመ፤ የድል አክሊልንም ተቀዳጀ፤ በዚያም የነበሩ ክርስቲያኖች ሥጋውን ወደ ከሀገሩ ልዳ ወስደው በክብር ቀበሩት፡፡
አምላካችን እግዚአብሔር በሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሎት ይማረን፤ ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን! 
3.3K views16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 19:57:37
ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ

ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ   የተወለደው በፍልስጤም ሀገር ልዳ በተባለች ከተማ በጥር ፳ ቀን በ፪፻፸፯ ዓ.ም ነው፤ አባቱ ዞሮንቶስ (አንስጣስዮስ) የተባለ መስፍን ነበር፤ እናቱ ቴዎብስታ (አቅሌስያ) ትባላለች። ማርታና እስያ የሚባሉ እኅቶች ነበሩት። ዐሥር ዓመት ሲሞላው አባቱ በሞት ተለየው፤ በዚህም ጊዜ ሌላ መስፍን ከቤቱ ወስዶ ካሳደገው በኋላ ወታደር ሆነ። ፳ ዓመት ሲሞላውም መስፍኑ የ፲፭ ዓመት ልጁን ሊያጋባው አስቦ ድግስ ደገሰለት፤ ሆኖም ግን ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ አልነበረምና አምላክ የመስፍኑን ነፍስ ወስደ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስም ወደ ቤሩት ሀገር ሄደ።

በቤሩትም ሕዝቡ ደራጎንን ያመልኩና ሴት ልጃቸውን ይገብሩለት ነበር፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ በመስቀል ኃይል ድል ነሥቶ ሕዝቡን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር አስገብቷቸዋል።
ከዚህ በኋላ ቅዱሱ ወደ ፋርስ ተመልሶ ሄደ፤ ከዚያም እንደደረሰ ንጉሥ ዱድያኖስ ፸ ነገሥታት ሰብስቦ እና ፸ ጣዖታት አቁሞ ሲሰግድና ሲያሰግድ አገኛቸው፤ በዚህም ተከፍቶና አዝኖ ከንጉሡ ፊት በመቆም “እኔ ክርስቲያን ነኝ፤ በኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ” አለው። እርሱም መልሶ እንዲህ አለው፤ “አንተማ የእኛ ነህ፤ በዐሥር አህጉር ላይ እሾምሃለሁ፤ የኔን አምላክ አጵሎንን አምልክ፡፡” ቅዱስ ጊዮርጊስም “ሹመት ሽልማትህ ለአንተ ይሁን፤ እኔ አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክድም” አለ።
3.4K views16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 13:29:04
#ግንቦት_ልደታን_ለግቢ_ጉባኤያችን

ቤተ ክርስቲያንን በጥቂቱ ያወቅንባት፣ መንፈሳዊ ዕውቀትን ከሕይወት ጋር የጀመርንባት፣ ያለ ምክንያት እርስ በእርስ መዋደድን የተማርንባት ግቢ ጉባኤያችንን በታሪካዊው የግንቦት ልደታ ሰሞን እንድንደግፍ የአንድ ሳምንት የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻ ተዘጋጅቷል።

እርስዎ በግቢ ጉባኤ ሕይወት አልፈው ያገኙት በረከት ለእህት ወንድሞችዎ  እንዲደርስ የግቢ ጉባኤ አገልግሎትን ያግዙ

ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻው ከሚያዝያ 28 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ግንቦት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ብቻ ይከናወናል።

ስለዚህ ቀድመው ይዘጋጁ! የግቢ ጉባኤ አገልግሎትን ይደግፉ!

የባንክ አካውንት ቁጥር አማራጮች

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ   1000003774957
አቢሲኒያ ባንክ   15203196
አዋሽ ባንክ       01304800017700
ሕብረት ባንክ    1110410459418011
ዓባይ ባንክ       1841117256280019
አሐዱ ባንክ       00034 88 710101
የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ   1033 100028297
2.0K views10:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 12:07:35 “በጎነትነትን አደርግልሃለሁ” (ኦሪት ዘፍጥረት 32:9)

አባቶቻችን ‘በጎ ማድረግ ለራስ ነው’ ይላሉ፤ ይህን አባባል በአንድም ይሁን በሌላ ሰምተነው ሊሆን ይችላል፤ ግን ስንቶቻችን እንሆን አስተውለን የቃሉን ትርጉም የመረመርነው? ስንቶቻችንስ ነን ፍቺውን ተረድተን በሕይወታችን የተገበርነው?

በሕይወታችን ውስጥ በርካታ ሰዎችን ልናውቅ እንችላለን፤ ከሁሉም በበለጠ በልባችን ትልቅ ስፍራ ያላቸው ወላጆቻችን፣ ወንድሞቻችንና እኅቶቻችን እንዲሁም ዘመድ አዝማዶቻችን እና ባልንጀሮቻችን እንደራሳችን የምንወዳቸው ቤተሰቦቻችን ናቸው፡፡ በጎ ልናደርግላቸውም የተገባ ነው፤ ለእነርሱ ዘወትር መልካም ማድረግን ቸል ልንል አይገባም፡፡

አምላካችን እግዚአብሔር መልካምነትን የሚወድ አባት መሆኑን በመጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያው ክፍል ኦሪት ዘፍጥረት ላይ በተደጋጋሚ ተገልጾ እናገኘዋለን፤ ሰውን የፈጠረውም ለመልካም መሆኑን ተገልጿል፤ ፈጣሪያችን ነገርን ሁሉ ለበጎ እንዳደረገው በሥነ ፍጥረቱ መግለጹን እዚህ ላይ እንመለከታለን፡፡ (ዘፍ.፪፥፩-፯)

ቅዱስ ያዕቆብ “የአባቴ የአብርሃም አምላክ ሆይ፥ የአባቴ የይስሐቅ አምላክ ሆይ፥ ‘ወደ ምድርህ ወደ ተወለድህበት ስፍራ ተመለስ፤ በጎነትንም አደርግልሃለሁ’ ያልኸኝ እግዚአብሔር ሆይ፥ ለባሪያህ በአደረግኸው በምሕረትህና በእውነትህም ሁሉ በጎውን አድርግልኝ” በማለት በጎነትን የሚያደርግ አምላክ እንዳለን አመልክቶናል፡፡ (ዘፍ.፴፪፥፱)

የበጎነቱ ተምሳሌትም በአርአያውና በአምሳሉ የፈጠረን እኛ ሰዎች በክርስቲያናዊ ሕይወታችን የምንተገብረው ምግባር እንደሆነ በቅዱሳን መላእክት፣ በነቢያትና በሐዋርያት ላይ አድሮ በቅዱስ ቃሉ አስተምሮናል፡፡
ሰው ለመልካም ተፈጥሮ መልካም ማድረግን ገንዘቡ ሊያደርግ እንደሚገባ በሥነ ፍጥረት ትምህርት የምንረዳው ነው፤ አምላካችን መልካም እንደሆነ እኛም ሰዎች መልካም መሆን፣ አምላካችን ለፍጥረታቱ መልካም እንዳደረገ እኛም ለሰዎች መልካም ማድረግ የተገባን ነን፡፡

በጎነት ሰው ላይ ክፋት ካለማሰብ ይጀምራል፤ ያም ለሰው መልካም መመኘትን ያመጣል፤ ወንድማችን፣ እኅታችንና ወዳጆቻችን ጥረው ግረው ስኬታማ ሲሆኑ ማየትን፣ መልካም ትዳር ሲይዙ መደሰትን እንዲሁም በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ሲበረቱ ምስክር ለመሆን መብቃትን ያስከትላል፡፡ ይህ ብቻም አይደለም! ለዚህ ሁሉ ስኬት ለሚወስዱት እርምጃና ለሚያከናውኑት ተግባር የሚያስፈልጋቸውን ነገር ማድረግና መርዳት ለሰው በጎ መሆን ነው፡፡

በወተትና በፍትፍቱ መግበው ያሳደጉንን አባት እናቶታችንን መጦር፣ የታላላቆቻችንን ውለታ መክፈል፣ አያቶቻችንን መንከባከብ እንዲሁም የሃይማኖት አባቶቻችን ምክርና ትእዛዝ በመተግበር እነርሱን ማገልገል ይገባል፡፡ በተጓዳኝም በሕይወታቸው ለሚያጋጥማቸው ማንኛውም ችግር መድረስና የተቻለንን ርዳት ማድረግ ከእኛ የሚጠበቅ ተግባር ነው፡፡
በጎ ማድረግ ለሰዎች መልካም መሆን ብቻ ሳይሆን በውስጣችንም የሚፈጥረው መልካም ስሜት ይኖረዋል፤ ለሌሎች በጎ ነገር ባደረግን ቁጥርም መልካምነት በውስጣችን ከመስረጹም ባሻገር አምላክችን ደስ ስለሚሰኝብን መንፈስ ቅዱስ ያድርብናል፡፡ ይህም ዘወትር መልካም ሰው እንድንሆን ይረዳናል፤ አባቶቻችን “በጎ ማድረግ ለራስ እንዲሉ ያደረጋቸውም ይህ ነው!

አምላካችን እግዚአብሔር በበጎ ምግባር የታነጽን መልካም ሰዎች እንድንሆን ይርዳን!
4.2K views09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 15:20:32
#ግንቦት_ልደታን_ለግቢ_ጉባኤያችን

ቤተ ክርስቲያንን በጥቂቱ ያወቅንባት፣ መንፈሳዊ ዕውቀትን ከሕይወት ጋር የጀመርንባት፣ ያለ ምክንያት እርስ በእርስ መዋደድን የተማርንባት ግቢ ጉባኤያችንን በታሪካዊው የግንቦት ልደታ ሰሞን እንድንደግፍ የአንድ ሳምንት የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻ ተዘጋጅቷል።

እርስዎ በግቢ ጉባኤ ሕይወት አልፈው ያገኙት በረከት ለእህት ወንድሞችዎ  እንዲደርስ የግቢ ጉባኤ አገልግሎትን ያግዙ

ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻው ከሚያዝያ 28 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ግንቦት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ብቻ ይከናወናል።

ስለዚህ ቀድመው ይዘጋጁ! የግቢ ጉባኤ አገልግሎትን ይደግፉ!

የባንክ አካውንት ቁጥር አማራጮች

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ   1000003774957
አቢሲኒያ ባንክ   15203196
አዋሽ ባንክ       01304800017700
ሕብረት ባንክ    1110410459418011
ዓባይ ባንክ       1841117256280019
አሐዱ ባንክ       00034 88 710101
የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ   1033 100028297
4.7K views12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 15:20:32
3.9K views12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 09:32:11
4.7K views06:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 09:32:11
4.5K views06:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 12:18:12
#ግንቦት_ልደታን_ለግቢ_ጉባኤያችን

ቤተ ክርስቲያንን በጥቂቱ ያወቅንባት፣ መንፈሳዊ ዕውቀትን ከሕይወት ጋር የጀመርንባት፣ ያለ ምክንያት እርስ በእርስ መዋደድን የተማርንባት ግቢ ጉባኤያችንን በታሪካዊው የግንቦት ልደታ ሰሞን እንድንደግፍ የአንድ ሳምንት የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻ ተዘጋጅቷል።

እርስዎ በግቢ ጉባኤ ሕይወት አልፈው ያገኙት በረከት ለእህት ወንድሞችዎ  እንዲደርስ የግቢ ጉባኤ አገልግሎትን ያግዙ

ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻው ከሚያዝያ 28 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ግንቦት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ብቻ ይከናወናል።

ስለዚህ ቀድመው ይዘጋጁ! የግቢ ጉባኤ አገልግሎትን ይደግፉ!

የባንክ አካውንት ቁጥር አማራጮች

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ   1000003774957
አቢሲኒያ ባንክ   15203196
አዋሽ ባንክ       01304800017700
ሕብረት ባንክ    1110410459418011
ዓባይ ባንክ       1841117256280019
አሐዱ ባንክ       00034 88 710101
የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ   1033 100028297
2.7K views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 11:26:10
#ግንቦት_ልደታን_ለግቢ_ጉባኤያችን

ቤተ ክርስቲያንን በጥቂቱ ያወቅንባት፣ መንፈሳዊ ዕውቀትን ከሕይወት ጋር የጀመርንባት፣ ያለ ምክንያት እርስ በእርስ መዋደድን የተማርንባት ግቢ ጉባኤያችንን በታሪካዊው የግንቦት ልደታ ሰሞን እንድንደግፍ የአንድ ሳምንት የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻ ተዘጋጅቷል።

እርስዎ በግቢ ጉባኤ ሕይወት አልፈው ያገኙት በረከት ለእህት ወንድሞችዎ  እንዲደርስ የግቢ ጉባኤ አገልግሎትን ያግዙ

ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻው ከሚያዝያ 28 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ግንቦት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ብቻ ይከናወናል።

ስለዚህ ቀድመው ይዘጋጁ! የግቢ ጉባኤ አገልግሎትን ይደግፉ!

የባንክ አካውንት ቁጥር አማራጮች

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ   1000003774957
አቢሲኒያ ባንክ   15203196
አዋሽ ባንክ       01304800017700
ሕብረት ባንክ    1110410459418011
ዓባይ ባንክ       1841117256280019
4.2K views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ