Get Mystery Box with random crypto!

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

የቴሌግራም ቻናል አርማ mahibere_kidusan — ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
የቴሌግራም ቻናል አርማ mahibere_kidusan — ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
የሰርጥ አድራሻ: @mahibere_kidusan
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 29.91K
የሰርጥ መግለጫ

The channel of mahibere kidusan

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-04-12 13:08:37
ዕለተ ረቡዕ፣ ዕለተ ምክር፣ ዕለተ ዕፍረት ወዕለተ ዕንብ

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማግሰኞ ዕለት ትምህርቱ ጸሐፍት ፈሪሳውያንን ዝም ስላሰኛቸው ሌሊቱን ርሱን ለመግደል ሲመክሩና ሲያሴሩ ቆይተው በዕለተ ረቡዕ ምክራቸውን በአንድ ሐሳብ ቋጭተዋል። የአይሁድ ልቃነ ካህናትና ጸሐፍት በሊቀ ካህናቱ ቀያፋ ግቢ ተሰባስበው መድኅን ክርስቶስን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው የመከሩበት ቀን በመሆኑ “የምክር ዕለት” ይባላል። ነገር ግን የፋሲካ በዓል ቀርቦ ስለነበር ሁከት እንዳይፈጠር እንዴት መያዝ እንዳለበት ሲጨነቁ ከጌታችን ደቀ መዛሙርት መካከል ይሁዳ ከምክራቸው በመቀላቀሉ ጥያቄአቸውን አቀለለላቸው፡፡
(ማቴ.፳፯፥፫-፭፣ሉቃ.፳፪፥፩-፪፣ማር.፲፬፥፩-፪) እንዲሁም እንዲሞት የወሰኑበት ዕለት ነው፡፡ (ማቴ.፳፮፥፫-፭) በተጨማሪም ይህ “ዕለተ ኢዮብ” እና “የመልካም መዓዛ ቀን” ተብሎም ይጠራል።
939 views10:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 00:31:41
ዕለተ ሠሉስ፣ ዕለተ ትምህርት

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ሠሉስ (ማግሰኞ) ስለ ፍርድ ቀንና ስለ ቤተ መቅደስ መፍረስ ሲያስተምር ውሏል። በወንጌል እንደተጻፈው በማለዳ ሲያልፉ ቅዱስ ጴጥሮስ በዕለተ ሰኑይ የተረገመችው የበለስ ዛፍ ከሥሯ መድረቋን አይቶ “እነሆ የረገምካት በለስ ደርቃለች” አለው። ጌታችንም ከዚህ በመነሳት በዚህች ዕለት ስለ እምነትና ስለ ይቅርታ አስተምሯል። (ማር. ፲፩÷፳-፳፮)
ጌታችን ኢየሱስ በቤተ መቅደስ ሲያስተምር የካህናት አለቆችና የሕዝብ ሽማግሌዎች መጥተው ‹‹ከምድራውያን ካህናት አይደለህ፣ ከምድራውያን ነገሥታት ወገን አይደለህ፣ ይህን የምታደርግ በምን ሥልጣን ነው?›› ብለው ጠየቁት፤ እርሱም መልሶ ጠየቃቸው፤ ‹‹የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነው?›› እነርሱም ከሰማይ እንዳይሉ አያምኑበትም፤ ከምድር እንዳይሉ ሕዝቡን ፈሩና ‹‹አናውቅም›› አሉት፡፡ እርሱም ‹‹እኔም አልነግራችሁም›› ብሎ ረታቸው፡፡
(ማቴ.፳፩፥፲፫-፳፫፣ማር.፲፩፥፳፯፣ሉቃ.፳፥፳፩-፵) ‹‹በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋልና ያዘዟሁን ሁሉ አድርጉ፤ ጠብቁትም፤ ነገር ግን እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ፡፡ ከባድና አስቸጋሪ ሸክም ተብትበው በሰው ትከሻ ይጭናሉ፤ እነርሱ ግን በጣታቸውስ እንኳ ሊነኩት አይወዱም›› በማለት እየወቀሰ ተናግሯል፡፡ በዚህም ዕለቱ የጥያቄ ቀን በመባል ይታወቃል፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን እርሾ ተጠንቀቁና ተጠበቁ” በማለት እንዳስተማረን በሃይማኖታችን፣ በመንፈሳዊ ሕይወታችንና በሥነ ምግባራችን የጥርጥርና የክፋት ትምህርት ከሚዘሩ ሰዎች ራሳችንን መጠበቅና መጠንቀቅ ይገባናል። (ማቴ.፲፮÷፯)

ዳግመኛም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዕለት በቤተ መቅደስ ረዥም ትምህርት በማስተማሩ ምክንያት ዕለተ ሠሉስ “የትምህርት ቀን” ይባላል።
2.6K views21:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 23:27:11 በተጨማሪም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ከርስቶስ “ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ትሰመይ (ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች፤ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችኋት” በማለት በቤተ መቅደስ የሚሸጡትንና የሚገዙትን አስወጥቷል። (ማር.፲፩÷፲፭-፲፯) ይህ ዕለት አንጽሖተ ቤተ መቅደስ የተፈጸመበት ዕለት መታሰቢያ ነው፤ ስለዚህም ዕለተ ሰኑይ “አንጽሖተ ቤተ መቅደስ” ይባላል። ይህም የሚያሳየው ማደሪያው ቤቱ የነበረውን የአዳም ልጆች ኃጥአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአትን ሁሉ እንዳራቀልን የሚገልጽ ነው።
2.7K views20:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 23:27:10
ሰሙነ ሕማማት

ሰሙነ ሕማማት የሚባለው ሳምንት በዐቢይ ጾም መጨረሻ ከሆሣዕና ዋዜማ ጀምሮ እስከ ትንሣኤ ባሉት ቀናት ውስጥ ያለው ነው። ሰሙነ ሕማማት የተባለበት ምክንያት ነቢዩ ኢሳይያስ አስቀድሞ የጌታችንን ምሥጢረ ሕማማቱን ነገር በመንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት “ውእቱ ነሥአ ደዌነ ወፆረ ሕማምነ” እርሱ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፤ ሕማማችንንም ተሸከመ ሲል እንደተናገረው የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ስለኛ ድኅነት በፍቃዱ ሕማማተ መስቀልን በትዕግሥት በመሸከም ማህያዊ ሞቱ በመስቀሉ የተፈፀመበት በመሆኑ እኛም መከራ መስቀሉን የምናስብበት ስለሆነ ሰሙነ ሕማማት ተብሏል። (ኢሳ.፶፫፥፬፣ማቴ.፰፡፲፣፯፣ዮሐ ፩፥፳፱)

ዕለተ ሰኑይ መርገመ በለስ ወአንጽሖተ ቤተ መቅደስ

በዚህ ዕለት ሰኑይ (ሰኞ) አዳምና ሔዋን ከገነት እንደተባረሩ፣ የበለስ ቅጠል እንዳገለደሙ ይታሰባል። ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ እንደጻፈው (ማር.፲፩፥፲፪-፲፬) ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በበዓለ ሆሣዕና በመሸ ጊዜ ከዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት ጋር ወደ ቢታንያ ወጣ። በማግሥቱም ከቢታንያ ሲወጡ ተራበ። ቅጠል ያላት በለስ ከሩቅ አይቶ ምናልባት አንዳች ይገኝባት እንደ ሆነ ብሎ መጣ። የበለስ ወራት አልነበረምና ከቅጠል በቀር ምንም አላገኘባትም። በዚያን ጊዜ “ከአሁን ጀምሮ ማንም ከአንቺ ፍሬ አይብላ” ብሎ ረገማት። ስለዚህም በሰሙነ ሕማማት የሚገኘው ሰኞ “መርገመ በለስ” የተፈጸመበት ዕለት መታሰቢያ ነው። የዚህም ትርጉም ወይም ምሥጢሩ ከበለስ ፍሬ መሻቱ ከሰው ፍቅር ተርቦ ለማጣቱን ለመግለጽ ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ከእኛ መልካም የሃይማኖትና የምግባር ፍሬ ሽቶ ይመጣልና ፍሬ አልባ ሆነን እንዳያገኘን፣ ፍሬ የማያፈራ ዛፍ እንደሚቆረጥና ቅጠሎቹም እንዲቃጠሉ ለእሳት እንደሚሰጡ የተነገረውን አስታውሰን መልካም ፍሬን ልናፈራ ይገባል።
2.8K views20:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 12:45:11 #የሰሙነ_ሕማማት_ሰኞ

#መርገመ_በለስ የተፈጸመበት ዕለት ነው

ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሆሣዕና ዕለት ቢታንያ አድሮ በማግሥቱም ከቢታኒያ ሲመጡ ተራበ፡፡ (ማር.11፤11-12) ቅጠል ያላት በለስ ከሩቅ አይቶ ወደ በለሲቱ ቀረበ፤ ነገር ግን ከቅጠል በቀር አንዳች ፍሬ አላገኘባትም፡፡ ከአሁን ጀምሮ ማንም ከአንቺ ፍሬ አይብላ ብሎ ረገማት። በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ናት፤ ፍሬ የተባለች ሃይማኖትና ምግባር ናት፤ ከእስራኤል ፍቅርን፤ ሃይማኖትን፤ ምግባርን ፈለገ አላገኘም፤ እስራኤል (ሕዝበ እግዚአብሔር) መባልን እንጂ፤ ደግ ሰው አይገኝብሽ ብሎ ረገማት፤ በመርገሙ ምክንያት እርሱ ከለያቸው በስተቀር ደግ ሰው ጠፋባት፡፡

በለስ ኦሪት ናት፤ ኦሪትን በዚህ ዓለም ሰፍና ቢያገኛት ኦሪትና ነቢያትን ልሽር አልመጣሁም ልፈጽም እንጂ በማለት ፈጸማት፤ ሕገ ኦሪትን ከመፈጸም በቀር በእርሷ ድኅነት አላደረገባትምና፤ ፍሬ በአንቺ አይሁን አላት፤ ደኅነት በአንቺ አይደረግብሽ ብሏታልና እንደመድረቅ ፈጥና አለፈች፡፡

በለስ ኃጢአት ናት፤ የበለስ ቅጠል ሰፊ እንደሆነች ሁሉ ኃጢአት በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፍና አገኛት፡፡ በለስ ሲበሉት ይጣፍጣል፤ ቆይቶ ግን ይመራል፤ ኃጢአትም ሲሰሩት ደስ ደስ ያሰኛል፤ ኋላ ግን ያሳዝናል፤ ወደ እርሷም ሄዶ ማለትም ከኃጥአን ጋር ዋለ፤ ኃጥእ ከመባል በቀር በአንደበቱ ሐሰት፤ በሰውነቱ ክፋት እንዳልተገኘበት ለማመልከት ፍሬ አላገኘባትም አለ፤ በአንቺ ፍሬ አይገኝ የሚለውም፤ በኃጢአት ፍዳ ተይዞ የሚቀር አይኑር ለማለት ነው፤ ስትረገም ፈጥና መድረቋም፣ በአዳም ምክንያት ያገኘችን ዕዳ በደል በእርሱ ካሣነት እንደጠፋችልን ለመግለጽ ነው፡፡

#አንጽሆተ_ቤተ_መቅደስ የተፈጸመበት ዕለት ነው፦

ጌታችን በለስን ከረገማት በኋላ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደ፤ ቤተ መቅደስ፣ ቤተ ጸሎት፣ ቤተ መሥዋዕት መሆኑ ቀርቶ ቤተ ምስያጥ (የንግድ ቤት) ሆኖ ቢያገኘው ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች፤ እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት ብሎ የሚሸጡበትን ሁሉ ገለበጠባቸው፤ ገርፎም አስወጣቸው፤ ይህም የሚያሳየው ማደሪያው ቤቱ የነበርን የአዳም ልጆች ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአታችንን ሁሉ እንዳራቀልን የሚገልጽ ነው፡፡

በዚህ በሰሙነ ሕማማት ካህናትና ምእመናን በቤተክርስቲያን ተገኝተው ወዛቸው ጠብ እስኪል ድረስ በነግህ፤ በሠለስተ፣ በስድስቱ ሰዓት፤ በተሰዓቱ ሰዓትና በሠርክ መላልሰው ሲሰግዱና ሲጸልዩ ይሰነብታሉ፤ በተለይም ካህናት በማንኛውም አገልግሎት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፤ ምክንያቱም የደረሰብን መከራ ኀዘኑን እና 5ሺ ከ5መቶ ዘመን የሰው ልጅ በጨለማ ይኖር እንደነበረ ለማዘከር ነው፡፡
4.9K views09:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 12:43:20 #በሰሙነ_ሕማማት_የሚፈጸሙ_ሥርዓቶች

1, #ስግደት :-
በሰሙነ ሕማማት 41 ጊዜ ኪርያላይሶን 12 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት እየተዜመ እጅግ አብዝቶ ይሰገዳል።

2, #ጸሎት :-
በሰሙነ ሕማማት ከ24 ሰዓት ውስጥ 10 የጸሎትና የንባብ ሰዓታት ይገኛሉ እነዚህም ከጠዋቱ 1 ሰዓት; 3ሰዓት; 6ሰዓት; 9ሰዓት; 11ሰዓት እንዲሁም ከምሽቱ 1 ሰዓት; 3ሰዓት; 6ሰዓት; 9ሰዓት; 11ሰዓት ናቸው።
በእነዚህም ሰዓታት የጌታን ስቃይ ለማዘከር መዝሙረ ዳዊትና ግብረ ሕማማት ድርሳነ ማኅያዊ አብዝተው ይጸለያሉ።

3, #ጾም :-
በሰሙነ ሕማማት ብዙ አዝማደ መባልዕት / አዘውትረን የምንመገባቸው ምግቦች አይበሉም። በዚህም ሳምንት እስከ ምሽቱ #አንድ_ሰዓት እንድንጾም; ይኸውም ቆሎ;ዳቦ;ወኃና ጨው ብቻ እንደታዘዙ በግብረ ሕማማት ላይ ተጽፎ ይገኛል።

4, #አለመሳሳም :-
አይሁድ ጌታችንን ለመስቀል እየተንሾካሾኩ ስለተመካከሩና ይሁዳ ጌታችንን በመሳም አሳልፎ ስለሰጠው መሳሳም አይፈቀድም። መስቀልም በዘመነ ኦሪት የወንጀለኛ መቅጫ የእርግማን ምልክት ስለ ነበር ጌታችን በክቡር ደሙ ቀድሶ የድል አርማ እስኪያደርግልን ድረስ አንሳለመውም ገላ.3:13 ማቴ.10:38 ማቴ. 26:29

5. #አክፍሎት :-
እመቤታችን; ያዕቆብና ዮሐንስ የጌታችን ትንሳኤ ሳናይ እህልና ውኃ አንቀምስም ብለው እስከ ትንሳኤው መቆየታቸውን በማሰብ የሚጾም ነው።

6, #ጉልባን :-
ከባቄላ ከስንዴ ከገብስ የሚዘጋጅ በጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚበላ ንፍሮ ሲሆን ትውፊቱም የስቅለቱ ሐዘን መግለጫ ነው።

7, #ጥብጠባ :-
ይህ ምዕመናን በሰሙነ ሕማማት የፈጸሟቸውን ኃጢአቶች ለካህን እየተናዘዙ በወይራ ቅጠል ቸብቸብ እየተደረጉ ስግደት የሚቀበሉበት ነው። ይህም የጌታ ምሳሌ ነው።

8, #ቄጠማ :-
ጌታችን ብርሃነ ትንሳኤዉን እንደገለጠልን የምናስብበት ሲሆን የእሾህ አክሊል በመድፋቱ ምሳሌም በራሳችን ላይ እናስረዋለን።

እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻም ወድካም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም።
4.9K viewsedited  09:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 08:20:34 ጌታችን በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ኢየሩሳሌም የገባበትን ዕለት በጌትነትና በክብር፣ በውዳሴና በቅዳሴ “ሆሣዕና በአርያም” እየተባለ በሽማግሌዎችና በሕፃናት አንደበት ሲመሰገን እንዲሁም ሕፃናት “ዝም በሉ” በተባሉ ጊዜ በድንጋዮችም ሳይቀር እየተመሰገነ ወደ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም በከብር ሲገባ ጌታ ለሰጠው ሰላምና ፍቅሩ መታሰቢያ ተደርጎ በዕለቱ ይዘከራል፡፡

ነቢየ እግዚአብሔር ዘካርያስም ‘አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይበለሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልል በይ፤ እነሆ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያያቱ ግልገል (ውርንጫይቱ) ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል… ሰላምን ይናገራል’’ በማለት ትንቢት ተናግሯል፤ (ዘካ.፱፣፱) ጌታ ይህን የሰላምን ብሥራት እንደሚያበሥር የተነገረ የትንቢት ቃል ነው።
በዓሉም ጌታ ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ ሕዝቡ ‘ፀበርት’ ወይም ‘ዘንባባ’ በመያዝ ‘ቡርክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር፤ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረክ ነው’’ በማለት በቤተ ክርስቲያን ይዘከራል፡፡ (መዝ.፻፲፯፣፳፯) በዚህ ትውፊት መሠረትም ቤተ ክርስቲያናችን በየዓመቱ ዘንባባ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ታድላለች። በመሆኑም ይህን የሆሣዕና በዓል ስናከብር ሰላምንና ፍቅርን የእርሱን የክብር አመጣጥ እያሰብን ልናከብረውና ልናዘክረው ይገባል።

የአህያን ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ ስንመለከት ግን የሚከተሉት ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ ‘ሰማይ ስሚ፤ ምድርም አድምጪ፤ በሬ የገዢውን አህያም የጌታውን ጋጣ አወቀ፤ እስራኤል ግን አላወቀም’’ በማለት ነቢዩ እንደተናገረው ጌታ በተወለደ ጊዜ ትንቢቱን ባልተቀበሉ ሰዓት በብርድ ወራት እናቱ የምታለብሰው ልብስ አጥታ ቅጠል አልብሳው በነበረ ጊዜ ለጌታ ሙቀት የገበሩለት ከብቶች፣ ላሞችና አህዮች ናቸው። (ኢሳ.፩፥፫) ‘ወአስተማወቅዎ አድግ ወላህም፤ አህያዎችና ላሞች ሙቀት ገበሩለት’’ እንዲል አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም።

በሆሣዕና ዕለት ጌታን ለከብር የተሸከመችው አህያ ናት። አህያ በሆሣዕና ጌታ ተቀምጦ በሄደበት ዕለት ልብሳቸውን ሁሉ አንጥፈው በልብሱ ላይ በክብር እንዲትሄድ አደረጉ። ክርስቶስ በአህያይቱ ላይ ሆኖ ሲመጣ ልብስም ተጎዝጉዞለታል፡፡ ስለዚህም ጌታ በጸጋውና በረድኤቱ እንዲያድርብን ልባችንን ከኃጢአትና ከተንኮል አንጽተን ፍቅርንና ትሕትና ልንለብስ ይገባል።

አህያዋ የኦሪት ምሳሌ ስትሆን ቀንበር መሸከም መቻሏ ሕገ ኦሪትን መጠበቅ የለመዱ የእስራኤል ዘሥጋ፣ ውርንጫይቱ ደግሞ ቀንበር መሸከም የማትችል ስትሆን የአሕዛብ ምሳሌ ናት።  አህያይቱ ቀንበር መሸክም የለመደች እንደሆነች ሁሉ ኦሪትም ሕግ ናትና፤ ውርንጫይቱ ቀንበር መሸክም ያልለመደች እንደሆነች ወንጌልም ያልተለመደች ሕግ ናትና፡፡ (ወንጌል አንድምታ)
የልብስ ምሳሌነት ደግሞ ልብስ የውስጥ ገመናን ሸፋኝ ነው። “አንተ ገመናችንን የምትሸፍን ነህ” ሲሉ ልብስ አነጠፉለት። በተጨማሪም ልብስ ክብር ሲሆን “አንትም ክብራችን ነህ” ሲሉ ልብስ አነጠፉለት።

ከበዓለ ሆሣዕና ረድኤት በረከት ሱታፌ እንድናገኝ የእግዚአብሔር ቸርነት ከሁላችን ይሁን።
3.6K views05:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 08:20:34
ሆሣዕና በአርያም!

እንኳን ለበዓለ ሆሣዕና በሰላም አደረሳችሁ!!!

ሆሣዕና በዕብራይስጥ “ሆሼዕናህ” ከሚለው ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉም “እባክህ አሁን አድን” ማለት ነው፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊትም “ኦ እግዚኦ አድኅንሶ፤ ኦ እግዚኦ ሠርሕሶ፤ ብሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር፤ አቤቱ እባክህ አሁን አድን፤ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፤ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩከ ነው” እያለም ዘምሯል፤ (መዝ.፩፻፲፯፥፳፭-፳፮)፡፡ “እነሆ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፣ በአህያዪቱ ግልገል በውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል” እንዲል፡፡ (ዘካ.፱፡፱)

ሆሣዕና ስያሜውንም ያገኘው በዕለቱ ከሚዘመረው መዝሙር ነው፡፡ ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሑዶች የመጨረሻው ሳምንት የሚወክል ሲሆን ከትንሣኤ አስቀድሞ በሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ዕለት የሚዘከርም በዓል ነው። በዚሁ በዓል የሚዘመረው ጾመ ድጓ “ሆሣዕና በአርያም፤ ሆሣዕና ለወልደ ዳዊት’’ በማለት የሚቀርብ ውዳሴ ነው፡፡

በዓለ ሆሣዕና ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ አእሩግ እና ሕፃናት “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም ሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም” እያሉ ጌታችንን መቀበላቸው የሚታወስበት ነው።
3.4K views05:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 17:32:35
4.1K views14:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 15:41:25 ቤተክርስቲያን በሕንጻ ግንባታዎች ላይ በመሰማራቷም ለበርካታ ወገኖች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድሎችን እንደፈጠረች የገለጹት ብፁዕነታቸው በቤት ችግር ምክንያት የሚንገላቱ ወገኖችም የመኖሪያ ቤት የሚያገኙበትን ዕድል ከመፍጠር አልፋ ለከተማችን አዲስአበባ ገጽታ ግንባታም ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች ብለዋል።

ዛሬ የቁልፍ ርክክብ የሚደረግለት ይህ ሕንጻ በብፁዕ አቡነ ያሬድ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅነት ጊዜ ተጀምሮ በአንድ ዓመት ውስጥ በመጠናቀቁ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው ቀደም ተብለው የተጀመሩና የግንባታ ሥራቸው በልዩ ልዩ ምክንያቶች የተጓተቱት ሁለት ሕንጻዎችን በተቻለ ፍጥነት ለማጠናቀቅ የሚያስችል ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በቅርብ ጊዜ የግንባታ ሥራቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቁም ያላቸውን ተስፋ ገልጸው  አሁን የተጠናቀቀው ሕንጻም በህጋዊ የጨረታ ሥርዓት ለተጠቃሚዎች ይተላለፋል ብለዋል።

ሕንጻው 21 ክፍሎች ያሉት እያንዳንዱ ክፍልም 3 መኝታ ቤቶች፣ ሊፍትና ጄኔሬተር  ያለው ሲሆን ቴራሱ  በሕንጻው ላይ ለሚኖሩ ነዋሪዎች ልዩልዩ ዝግጅቶች የሚያገለግል ይሆናል፤ከዚህ በተጨማሪም ሕንጻው የእሳት ማጥፊያ እና የውሀ ፓንፕ የተገጠመለትና ከወዳጅነት ፓርክ ፊት ለፊት  ለመኖሪያ ምቹ በሆነ ሥፍራ ላይ የሚገኝ ነው።

የሕንጻ ግንባታ ሥራውም በአተም ኮንስትራክሽንና በዘዶር አማካሪ ድርጅት የተገነባ ሲሆን ለዚህ ሕንጻ ግንባታ በታቀደለት ጊዜ መጠናቀቅም የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅና የሥራ ኃላፊዎች ሚና የጎላ ነው።

ብፁዕ አቡነ ያሬድ በዘመነ ሢመታቸው ይህን ሕንጻ ግንባታን ጨምሮ በድሬዳዋ ከተማ ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃውን ባለ አራት ወለል የገበያ ማእከልና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት በመገንባት ላይ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ግንባታዎችን በማስጀመር ለብፁዕ አቡነ አብርሃም ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ማስረከባቸው ይታወሳል።

በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁን ጨምሮ ፣ ም/ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት መምሪያ ኃላፊዎች የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የሕንጻ ሥራ ተቋራጩና የአማካሪ ድርጅቱ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በድሬዳዋ ከተማ የተገነባው ሁለገብ የገበያ ማእከል እና በዛሬው ዕለት የቁልፍ ርክክብ የተደረገለት ሕንጻ የምርቃት መርሀ ግብር ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በበዓለ ሀምሳ ውስጥ እንደሚከናወን ከቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ኢ/ኦ/ቴ/ቤ ቴሌቪዥን እንደዘገበው።
4.2K views12:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ