Get Mystery Box with random crypto!

LEYU NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ leyu_news — LEYU NEWS L
የቴሌግራም ቻናል አርማ leyu_news — LEYU NEWS
የሰርጥ አድራሻ: @leyu_news
ምድቦች: ቴሌግራም
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 527
የሰርጥ መግለጫ

#ልዩ_መረጃ  |  #ቀዳሚ_ምርጫዎ
➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ
➠ወቅታዊ መረጃዎች
➠ልዩ ልዩ ዘገባዎች
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዜናዎች
➠ጠቃሚ ጥቆማዎች ይደርሶታል።
አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን።
         PROMOTION
➥   
🎬  "ተመራጭ የዜና ምንጭ"
News & Media Channel®

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-04-20 19:09:51
የዒድ አልፈጥር በዓል በነገው ዕለት ይከበራል!

የሸዋል ወር ጨረቃ በሳኡዲ አረበያ ዛሬ ሕሙስ በመታየቷ የዒድ አልፈጥር በዓል ነገ አርብ እንደሚውል ታውቋል።የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪዓ ፍርድ ቤት 1444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል አስመልክቶ በዛሬው ዕለት በሰጠው መግለጫ፤ ሙስሊሙ ሕብረተሰብ በዓሉን ሲያከብር ያጡና የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብና በመርዳት እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል።

@Leyu_News
@Leyu_News
2.3K views16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 15:52:49 አራት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በፌስቡክ ማንነቱን ቀይሮ በመተዋወቅ ‘‘ካናዳ እና እንግሊዝ እወስዳችኋለው’’ በማለት ጾታዊ ግንኙነት እንዲፈጽሙ አድርጓል የተባለው ግለሰብ በጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጣ።

ግለሰቡ ከግማሽ ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብ እና 20 ግራም ወርቅ ተቀብሎ የማታለል ወንጀል ፈጽሟል ተብሎ ነው በጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ የተወሰነው። የቅጣት ውሳኔውን የወሰነው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ 2ኛ አርቲዲ ወንጀል ችሎት ሲሆን÷ተከሳሹ ታዲዮስ ዘላለም በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ነዋሪ ነው።

ተማሪዎችን በማህበራዊ ትስስር ገጽ “ናቲ መላኩ” ብሎ ማንነቱን ቀይሮ በካናዳ ነዋሪ በመምሰል ከተዋወቃቸው በኋላ ‘’ካናዳና እንግሊዝ እወስዳችኋለው’’ ብሎ የማታለል ተግባር መፈጸሙ በክሱ ተመላክቷል። ከዚህም በኋላ ተከሳሹ ከካናዳ ወደ አዲስ አበባ እንደመጣ በማስመሰል በግንቦትና በሰኔ ወር 2014 ዓ.ም በተለያዩ ቀናቶች ለ4 የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የግል ተበዳዮች ስልክ ይደውላል፡፡ በዚህም'' ከእንግሊዝ ኤምባሲ ጉዳይ የሚፈጽምላችሁ ሰው ይመጣል፤ አሻራ የሚወሰደው ከዘር ፈሳሽ እና ከወርቅ ስለሆነ አልጋ ይዛችሁ ጠብቁ በማለት'' የግል ተበዳዮች በተለያየ ቀናቶች በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 13 አልጋ ይዘው እንዲጠብቁ ማድረጉ በክሱ ተጠቅሷል።

አልጋ እንዲይዙ ካደረገ በኋላ ማንነቱን ቀይሮ ወደ አልጋ ቤት በመሄድ የግብረስጋ ግንኙነት እንዲፈጽሙ ማድረጉም በክሱ ተመላክቷል።

በተጨማሪም ተከሳሹ ከግል ተበዳይ ተማሪዎች ከእያንዳንዳቸው የተለያየ መጠን ያለው በአጠቃላይ 20 ነጥብ 7 ግራም ወርቅ ለአሻራ ምርመራ ያስፈልጋል ብሎ መውሰዱ በክሱ ተገልጿል፡፡ ለጉዳይ ማስፈጸሚያ በሚል ከእያንዳንዳቸው ግማሽ ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብ መቀበሉም በክሱ ተዘርዝሯል።

ተከሳሹ ከግል ተበዳዮች መካከል ከአንደኛዋ ተማሪ ጉዳይ ለማስፈጸም "አይፎን "ሞባይል ስልክ ያስፈልጋል በማለት እንድታመጣ በማዘዝ የስልክ ቀፎውን ለመቀበል በቀጠራት ዕለት ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ በኦፕሬሽን ክትትል በቁጥጥር ስር መዋሉ  በክሱ ተመላክቷል። በዚህም ተከሳሹ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 692/1 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ በማታለል ወንጀል ተደራራቢ አራት ክሶች ቀርቦበታል።

ተከሳሹ ክሱ ከደረሰውና በችሎት በንባብ ከተሰማ በኋላ ወንጀሉን አልፈጸምኩም ሲል የዕምነት ክህደት ቃሉን ሰጥቷል። የፍትህ ሚኒስቴር የቦሌ ምድብ ዓቃቤ ሕግ ለወንጀሉ መፈጸም ያስረዳሉ ያላቸውን የግል ተበዳዮችን ጨምሮ 6 ምስክሮችን በችሎት አቅርቦ የምስክርነት ቃላቸውን አሰምቷል።

ፍርድ ቤቱ የምስክር ቃል መርምሮ ተከሳሹ ወንጀሉን መፈጸሙ በዐቃቤ ሕግ ምስክር ቃል ማረጋገጡን በመግለጽ ተከሳሹ በተከሰሰበት አንቀጽ እንዲከላከል ብይን ተሰጥቶ ነበር። ይሁንና ተከሳሹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መከላከል ባለመቻሉ በመጋቢት 15 ቀን 2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት በተከሰሰበት በአራት ክሶች በአንቀጽ 692 (1) ስር የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎበታል።

ተከሳሹ ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ ማድረጉን ለህዳሴ ግድብ የቦንድ ግዢ መፈጸሙን እንዲሁም ለማህበራዊ በጎ አድራጎት  ያበረከተውን አስተዋጾን የሚገልጽ   ከቦሌ ክ/ከ ወረዳ 13  ጽዳት አስተዳደርና ከዚሁ ወረዳ ከሴቶችና ሕጻናት ቢሮ የተሰጠውን ማስረጃ ጨምሮ  አራት የቅጣት ማቅለያ አስተያየት አቅርቦ በፍርድ ቤቱ ተይዞለታል።

በዐቃቤ ሕግ በኩል ግን የቅጣት ማክበጃ አስተያየት አለመቅረቡን የችሎቱ ዳኛ ገልጸዋል።

በቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 2/2006 መሰረት በደረጃ ስድስት በዕርከን 25 መነሻ በ7 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ የተወሰነ ሲሆን÷በዕርከን 3 መሰረት ደግሞ በ3 ሺህ ብር የገንዘብ እንዲቀጣ ተወስኗል። ቅጣቱን የአዲስ አበባ  ማረሚያ ቤት እንዲያስፈጽም የታዘዘ ሲሆን÷የቅጣት ውሳኔ ሲወሰን የግል ተበዳይ ከሆኑት ተማሪዎች መካከል ሁለቱ በችሎት ተገኝተው ቅጣቱን ተከታትለዋል።(በታሪክ አዱኛ)

@Leyu_News
@Leyu_News
3.3K views12:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 13:53:18
በኬንያ የታገተው ኢትዮጵያዊ ቤተሰቦች በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ክስ መሰረቱ!

ከአንድ ዓመት ከስድስት ወር በፊት ኬንያ ውስጥ “የፖሊስ ደንብ ልብስ” በለብሱ ሰዎች ተወስዶ እስካሁን ያለበት አልታወቀም የተባለው የአቶ ሳምሶን ተክለሚካኤል ቤተሰቦች የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ላይ ክስ መሰረቱ።

የመንግስት አካላቱ ላይ የተከፈተውን ክስ በተመለከተ በዛሬው እለት የአቶ ሳምሶን ባለቤት ወ/ሮ ሚለን ሀለፎም እንዲሁም በፌደራል እና በኦሮሚያ ክልል ፍርድ ቤቶች ጠበቃ የሆኑት አቶ ዳባ ጩፋ (ዶ/ር) በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።

ወ/ሮ ሚለን ሀለፎም እንደተናገሩት ከባለቤታቸው መሰወር በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት የተወሰኑ ጥረቶች ቢያደርግም አንድ ዜጋ በውጭ ሀገር መብቱ ሲጣስ ማድረግ ከሚገባውው አንፃር በቂ ባለመሆኑ ክስ መክፈቱ አስፈላጊ ሆኗል ብለዋል።

ጉዳዩን የያዙት የህግ ባለሞያ አቶ ዳባ ጩፋ በበኩላቸው “ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት የመጣበት ምክንያት እነዚህ የተከሰሱ አካላት ግዴታቸውን ባለመወጣታቸው ነው። ፍርድ ቤት በህግ አግባብ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ማስገደድ የሚችል በመሆኑ እንደሚያስገድዳቸው እንጠብቃለን” ሲሉ ተናግረዋል።

[Addis Zeybe]

@Leyu_News
@Leyu_News
3.4K views10:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 12:26:45
የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪዓ ፍርድ ቤት የዒድ አልፈጥር በዓል ጨረቃ ዛሬ ሀሙስ ማታ ከታየች ነገ አርብ ካልታየች ደግሞ ቅዳሜ ይከበራል ሲል አሳውቋል

ይህን ያሳወቀው ዛሬ በሰጠው መግለጫ ነው።

1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ፤ ለኢትዮጵያና ለመላው ዓለም ህብረተሰብ  የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞቱን የገለፀው ሼሪዓ ፍርድ ቤቱ  ሙስሊሙ ህብረተሰብ  በዓሉን ሲያከብር ያጡና የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብና በመርዳት እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል።
@Leyu_News
@Leyu_News
3.4K views09:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 11:28:15
በየመን ለረመዳን እርዳታ ሲታደል በተፈጠረ መጨናነቅ 78 ሰዎች ሞቱ!

በየመን ዋና ከተማ ሰንአ በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት ውስጥ የረመዳን ወርን በማስመልከት ሲደረግ የነበረ ድጋፍን ተከትሎ በተፈጠረ ትርምስ ቢያንስ 78 ሰዎች መሞታቸውን ባለስልጣናት ገልጸዋል።በማህበራዊ ትስስር ገጾች የሚዘዋወሩ ቪዲዮዎች በከተማዋ ባብ አል የማን በተባለ ቦታ የነበረውን ግርግር አሳይተዋል።

በስፍራው በነፍስ ወከፍ ሲታደል የነበረውን 9 ዶላር ወይም 485 ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመቀበል በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች በተጨናነቀ ሁኔታ በትምህርት ቤት ውስጥ ተሰባስበው እንደነበር ሮይተርስ ዘግቧል።ከአውሮፓውያኑ 2015 ጀምሮ ከተማዋ በሁቲ አማጽያን ቁጥጥር ስር ወድቃለች።

እርዳታውን ሲያድሉ የነበሩ ሰዎች ታስረው ምርመራ እየተደረገ እንደሆነ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ገልጿል።የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ እርዳታውን ከአከባቢው አስተዳደር ጋር ሳይቀናጁ በዘፈቀደ ለማደል መሞከሩ የችግሩ ምንጭ ናቸው ሲሉ ወቅሰዋል።በአደጋው በከርካታ ሰዎችም እንደተጎዱና 13 ሰዎች ደግሞ ለህይወት በሚያሰጋ ሁኔታ እንደሚገኙ በሰንአ ያሉ የጤና ባለሙያዎች ገልጸዋል።

[BBC]

@Leyu_News
@Leyu_News
3.5K views08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 09:36:55 በኢትዮጵያ እና በሱዳን ድንበር ላይ ጦርነት መጀመሩ ተሰማ!

የሱዳን ሰራዊት ከሕወሓት ጋር የአብይ መንግስት የሚያደርገውን ጦርነት ተከትሎ ወረራ በመፈጸም ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ዘልቆ መግባቱ ይታወሳል። ዘልቆ በመግባትም ከፍተኛ ጥፋት ከማድረሱም በላይ ተጨማሪ መሬቶችን በቁጥጥር ስር በማዋል ይዞ መቆየቱ ይታወቃል። ሱዳን በአሁን ሰአት በአልቡርሃን ጦር እና በፈጥኖ ደራሽ ጦር መካከል ካርቱም ውስጥ ጦርነት ላይ ናቸው። በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር ላይ ያሉ ወታደሮችም የኢትዮጵያን ጦርና የአማራ ልዩ ኃይልን ለመተንኮስ ጥረት ማድረጋቸውን ተከትሎ ጦርነት መቀስቀሱን አልሱዳን የተሰነው የዜና ምንጭ ዘግቧል ።  ከምሽቱ ስምንት ሰአት በፊት የኢትዮጵያ ወታደሮች ጥቃት ሰንዝረው ካምፖችን በማውደም እስረኞችን በማስፈታት መመለሱን ተሰምቷል። ሲል አል ሱዳኒ ዘግቧል።

የሱዳን ሰራዊት በአል ፋሽቃ አል-ሱራ ላይ የኢትዮጵያውያንን ወረራ ለመመከት ተጋድሎ እያደረገ ነው ያለው አልሱዳኒ የተሰነው የዜና ምንጭ  በሰው ህይወት እና በመሳሪያ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል ሲል ገልጿል። ዘገባው አያይዞም በትናንትናው እለት የኢትዮጵያ ጦር በታንክ፣ በታጠቁ መኪኖች እና ብዙ እግረኛ ወታደሮች ታግዞ በአል ፋሽቃ አል-ሱግራ ላይ ወረራ እና ጥቃት ፈጽሟል። በሱዳን ወታደሮች እና በመሳሪያዎች ላይ ከባድ ኪሳራ አድርሶባቸዋል ሲል ተናግሯል።

የአልሱዳን ዜና መረጃ እንደሚለው በካርቱም በሱዳን ወታደሮች እና በፈጣን የድጋፍ ሃይሎች መካከል የተካሄደው ጦርነት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በምስራቅ ድንበር ላይ የሰፈረው የሱዳን ጦር ሃይሎች በኢትዮጵያ ሃይሎች እና ካምፖች ውስጥ የነቃ እና ያልተለመደ እንቅስቃሴ ሲከታተሉ ቆይተዋል። እንዲሁም በኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች የተካሄደው ከፍተኛ የስለላ እና የቁጥጥር ስራ በአል-ፋሽቃ አል-ሱራ ውስጥ በአብዱራፊ ሴክተር ውስጥ በአጥቂ ስፍራዎች ተጨማሪ የታጠቁ ሰዎች ተስተውለዋል፣ እና ይህ በካርቱም ውስጥ በታጣቂ ሃይሎች እና በፈጣን የድጋፍ ሃይሎች መካከል የተፈጠረው ክስተት ከጀመረበት ጊዜ ጋር ተገጣጥሟል። ይላል

የዜናው ምንጭ የኢትዮጵያ ወታደሮች ብቻ ሳይሆኑ ወረራውን የፈጸሙት የአማራ ክልል “ፋኖ” ሚሊሻ፣ ​​ልዩ ሃይል ያቀፈ ነው ያለ ሲሆን የነዚያ ሃይሎች አላማ አል ፋሽቃ አል-ስጉራ እና ደቡብ ከጋላባት ደቡብ እና ከባሳንዳ በስተደቡብ ወደ አል-ዲንድር ሀንጋር ለመመለስ እና አሁን ያለውን የሱዳን ሁኔታ በመጠቀም የግብርና መሬቶችን ማስመለስ ነው። ብሏል ዘገባው በትናንትናው እለት የሱዳን ሃይሎች በአቡ አል ቱዩር ሴክተር ጥቂት ኢትዮጵያውያን የስለላ አካላትን ተከታትለው መትረየስ ተኩሰው አባረዋል። የስለላ አካላቱ ኝ አልተያዙም። 

ምንጭ፦አልሱዳን የዜና ወኪል

@Leyu_News
@Leyu_News
3.7K viewsedited  06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 08:02:09 አጫጭር መረጃዎች በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ

የሱዳን የባህር ሃይል ጦር አዛዥ የነበሩት ፋት አል ራህማን ሙህይዲን ለአልጀዚራ እንደተናገሩት “ካርቱም በሙሉ” በጦር ኃይሉ ቁጥጥር ስር መግባቷን ገልፀዋል። "ለሱዳን ህዝብ እንደማረጋግጠው ከሁለት ግዛቶች በስተቀር ሁሉም ግዛቶች በጦር ኃይሉ ቁጥጥር ስር ናቸው" ሲሉ አክለዋል።

ከ20,000 በላይ የፈጣን ድጋፍ ሰጭ ሃይሎች ለሠራዊቱ እጃቸውን መስጠታቸው የሱዳን የባህር ሃይል ጦር አዛዥ የነበሩት ፋት አል ራህማን ሙህይዲን  ተናግረዋል።አንዳንዶች ግን እስከ ሞት ድረስ መታገል ይፈልጋሉ” ሲል ሙህይዲን አክለዋል። አስተያየታቸውን ግን በገለልተኛነት አካል ማረጋገጥ አልተቻለም።

በካርቱም የፖለቲካ ተንታኝ አሽራፍ አብደል አዚዝ የግጭቱ ምንጮች በጦር ኃይሎች አዛዥ ጄኔራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን እና በአርኤስኤፍ መሪ ጄኔራል መሀመድ ሀምዳን “ሄሜቲ” ዳጋሎ መካከል “ግላዊ” ፀብ ናቸው ብለዋል። "ነገር ግን መጥፎው የሰብአዊ ሁኔታ ግጭቱን እንዲያቆሙ በሁለቱም ወገኖች ላይ ጫና ያሳድራል" ሲሉ ከካርቱም ተናግረዋል።

ድንበር የለሹ የሀኪሞች ቡድን ባልደረባ ባክሪ ባሽር ለአልጀዚራ እንደተናገሩት በሱዳን ያለው የጤና ሁኔታ “ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ” መልኩ አስጊ መሆኑን ተናግረዋል። ከኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ባሽር እንደተናገሩት “ጦርነቱ በዚህ ፍጥነት የሚቀጥል ከሆነ በሀገሪቱ ያለውን የጤና ስርዓት ሙሉ በሙሉ እናጣለን የሚል ስጋት ተጋርጦብናል” ብለዋል።

በካርቱም ከሚገኙት 59 ሆስፒታሎች እና ክሊኒኮች 39ኙ ህሙማንን ማገልገል የማይችሉ መሆናቸውን የሱዳን የህክምና ኮሚቴ አስታውቋል።በመግለጫውይ አንዳንድ ሆስፒታሎች በቦምብ መመታታቸውን ገልጿል። ታካሚዎችን እና የህክምና ባለሙያዎችን ለመጠበቅ “አስቸኳይ ጣልቃ ገብነት” እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

በጦር ሠራዊቱ እና በፈጣን ድጋፍ ሰጭ ኃይሎች መካከል ግጭት ከተቀሰቀሰ በኋላ ቢያንስ 270 ሰዎች መሞታቸውን የዓለም ጤና ድርጅት የሱዳንን የጤና  ሚኒስቴርን ጠቅሶ አስታውቋል። ሌሎች 2,600 ሰዎችም ቆስለዋል ሲል አክሏል።
ዳጉ_ጆርናል

@Leyu_News
@Leyu_News
3.6K views05:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 08:01:35
ትላንት የቱርኳ ኢስታንቡል በድንገት እስከ አስር ኪሎ ሜትር በሚሸፍን ግዙፍ ጥቁር ደመና ተሸፍና ነበር ። ፀሐይ ለ5 ደቂቃ ያህል አልታየችም ። ከተማዋ እንደ ሌሊት ጨለማ ሆና ነበር።

ቪዲዮው ከማህበራዊ ሚዲያ የተገኘ ነው።

@Leyu_News
@Leyu_News
3.6K views05:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 21:10:36
በሀዲያ ዞን በፀጥታ ኃይሎች በተወሰደ እርምጃ በሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተሰማ!

በደቡብ ክልል ሀዲያ ዞን የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤት ሰራተኞች ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ ደመወዝ አልተከፈለንም በሚል ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ከጀመሩ ሁለተኛ ቀናቸውን አስቆጥረዋል፡፡

በዞኑ ባደዋቾ ወረዳ እና ሾኔ ከተማ ከ ሰባት ሰዓት በላይ በተደረገዉ ሰላማዊ ሰልፍ አዲስ አበባን ከአርባ ምንጭ  የሚያገናኘዉ መንገድ ዝግ ሆኖ ሲውል ከምሽቱ 12 ሰዓት በኋላ ሰልፈኞችን ለመበተን በዞኑ ፓሊሶች ተኩስ መከፈቱን የአዲስ ዘይቤ ምንጮች ገልጸዋል።

በሾኔ ከተማ ሰልፉን ለመበተን በተወሰደዉ እርምጃ አንድ የፓሊስ አባል በእራሱ ተኩሶ ጉዳት ሲደርስበት ሶስት ሰዎች ድብደባ ተፈፅሞባቸዉ በከተማዋ ወደሚገኘዉ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል መወሰዳቸዉን ምንጮቻን ተናግረዋል።

[Addis Zeybe]

@Leyu_News
@Leyu_News
2.1K views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 18:53:52 በአርሲ ዞን በድጋሚ ለቅርጫ ከተገዛ ሰንጋ ውስጥ 7.5 ግራም ወርቅ ተገኘ

ወርቁ 21 ሺህ 500 መቶ ብር ተሽጧል

በምስራቅ አርሲ ለትንሳኤ በዓል የገዙት በሬ ለእርድ በሚቀርበበት ሰዓት በሀሞቱ ውስጥ 7.5 ግራም የሚመዝን ወርቅ መገኘቱን የጢዮ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ግረማ ጣፋ በተለይ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

ግለሰቦቹ  ኩማ ተሰማ እና ንጉሴ ዲንቃ የተባሉ ሲሆን ለበዓል ቅርጫ በ38 ሺህ ብር በሬ ገዝተው  በሚያርዱበት ወቅት  በበሬው ሃሙት ውስጥ 7.5 ግራም የሚመዝን ወርቅ አግኝተዋል። ወርቁ  ሃያ አንድ ሺ አምስት መቶ ብር መሸጡ ተሰምቷል።

ከቀናት በፊትም በዚሁ አካባቢ 18.5 ግራም የሚመዝን ወርቅ በበሬ ሀሞት ላይ ስለመገኘቱ እና ወርቁን 53 ሺህ ብር ስለመሸጡ ብስራት ሬዲዮ መዘገቡ ይታወሳል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው እንዳሁኑ ይፋ የወጣ ነገር ባይኖርም በተደጋጋሚ  በበሬዎች ሃሞት ላይ ወርቅ ስለመገኘቱም ኮማንደር ግርማ ጣፋ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

ዳጉ ጀርናል

@Leyu_News
@Leyu_News
3.0K views15:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ