Get Mystery Box with random crypto!

ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda

የቴሌግራም ቻናል አርማ kegnitbekuasmeda — ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda
የቴሌግራም ቻናል አርማ kegnitbekuasmeda — ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda
የሰርጥ አድራሻ: @kegnitbekuasmeda
ምድቦች: ስፖርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.72K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ በአፍሩ ፊልም ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት ተዘጋጅቶ በኤፍኤም አዲስ 97.1 ላይ ታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች በቀጥታ የሚቀርቡበት ቻናል ነው።

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-01 06:34:25 ማንቸስተር ሲቲ ከ ሊቨርፑል ቅድመ ጨዋታ ትንታኔ በቅኝት በኳስ ሜዳ

  በአገራት ጨዋታ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የሊግ ጨዋታዎች የእንግሊዝ ሁለተኛው እርከን ጨምሮ የተለያዩ አገራቶች ጨዋታ አርብ ምሽት በተደረጉ ጨዋታዎች የተጀመሩ ሲሆን ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪሜየር ሊግ በተጠባቂው የማንቸስተር ሲቲ ና የሊቨርፑል ጨዋታ ዛሬ በምሳ ሰአት ጨዋታ ይመለሳል።
 
   አሁን ላይ ሁለቱን ቡድኖች እያሰለጠኑ የሚገኙት ፔፕ ጋርዲዮላና የርገን ክሎፕ በአጠቃላይ በሁሉም ጨዋታዎች ለ 28 ጊዜ ቅዳሜ ከሰዓት 8:30 ላይ በኢቲሀድ የሚገናኙ ሲሆን ፔፕ ጋርዲዮላ በአሰልጣኝነት ቆይታው  የየርገን ክሎፕን ያህል ደጋግሞ በተቃራኒ የገጠመው አሰልጣኝ የለም፤በተመሳሳይ ጀርመናዊው አሰልጣኝ እንደ ስፔናዊው አሰልጣኝ ብዙ ጊዜ የገጠመው አንድም አሰልጣኝ የለም።
  ታዲያ እነዚህ ሁለት የውብ እግርኳስ አቀንቃኞች በጀርመን ቡንደስሊጋ በነበሩበት ወቅት ይሁን በእንግሊዝ ፕሪሜየር ሊግ ላይ በሚገናኙበት ወቅት ሜዳ ላይ ከሚያስመለክቱን አስደናቂ ፉክክር የተሞላበት ማራኪ እግርኳስ በዘለለ በተለይ ወደ እንግሊዝ ፕሪሜየር ሊግ ከመጡ በኋላ  ከ 2020/21 የውድድር አመት ውጪ ላለፉት አምስት  አመታት እነሱ የሚያሰለጥኗቸው ቡድኖች የሊጉ አሸናፊ ለመሆን ከፍተኛ ትንቅንቅ ያደርጉ የነበሩ መሆኑን ተከትሎ ሁለቱን ቡድኞች እርስ በእርስ የሚያገናኘው መርሀግብር በእግርኳስ ቤተሰቡ ዘንዴ  በጉጉት እንዲጠበቅ አድርጎታል።
  “That is why we love the game,” ሮይኪን APRIL 10 2022 በኢትሀድ 2 ለ 2 በሆነ ውጤት የተጠናቀቀውን ከሁለቱ ቡድኞች ማራኪ ጨዋታ በኋላ ጨዋታውን የገለፀበት መንገድ ነበር።
  ከአመት በኋላ በ APRIL ወር ላይ በኢትሀድ ሁለቱ ቡድኖች ቅዳሜ ምሳ ሰአት ሲገናኙ በተመሳሳይ አቋም በተመሳሳይ ደረጃ ላይ ሆነው እንዳልሆነ የሚታወቅ ቢሆንም በዚህ ጨዋታ ላይ የሚመዘገብ ውጤት ለማንቸስተር ሲቲ የዋንጫው አሸናፊ ለመሆን ከአርሰናል ጋር እያደረገ ላለው ትንቅንቅ ላይ በሊቨርፑል በኩል ደግሞ በሚቀጥለው አመት የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ተሳታፊ የሚያደርገውን ቦታ ይዘው ለማጠናቀቅ ለሚያደርጉት ጥረት ስለሚረዳቸው ጨዋታው ተጠባቂ እንዲሆን አድርጎታል።

   ባለሜዳዎቹ ሲትዝኖቹ በዚህ የውድድር አመት እያስመለከቱን ያሉት አቋም ከራሳቸው ያለፉት አመታት አቋም አንፃር መውረዶች ቢታዩበትም አሁንም የዋንጫው አሸናፊ ለመሆን ከመድፈኞቹ ጋር ከፍተኛ ፉክክር እያደረጉ እንዳለ የሚታወቅ ነው ምንም እንኳን አንድ ጨዋታ ከመድፈኞቹ  ያነሰ ተጫውተው በ8 ነጥብ አንሰው ሁለተኛ ደረጃ ላይ ቢቀመጡም ብዙዎች አሁንም የዋንጫ አሸናፊነት ግምታቸውን ለውሀ ሰማያዊዎቹ እየሰጡ ይገኛሉ።
ብዙዎች እየገመቱት እንዳሉት የ2022/23 የውድድር አመት የዋንጫ አሸናፊ ውሀ ሰማያዊዎቹ  ለመሆን ግን በሚኬል አርቴታ ስር አስደናቂ ጊዜን እያሳለፉ የሚገኙት የሊጉ መሪ የሆኑት መድፈኞቹ  ውጤት መጣል መጠበቅ በተጨማሪ የፔፕ ጋርዲዮላው ቡድን ተከታታይ ድሎች በሊጉ ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል። በዘንድሮ የውድድር አመት ማንቸስተር ሲቲዎች ተከታታይ ድሎችን ወጥ የሆነ አቋም ለማሳየት መቸገራቸው ከሚያሳዩ ነገሮች አንዱ በዚህ የውድድር  ዘመን ማንቸስተር ሲቲዎች በሊጉ ላይ አንድ ጊዜ በተከታታይ አራት ጨዋታዎችን አሸንፈው አያቁም፤በአገራት ጨዋታ የሊጉ ጨዋታ ከመቋረጡ በፊት ማንቸስተር ሲቲ አንፃራዊ ወጥ ተከታታይ ድሎችን ማስመዝገብ ችለው ነበር፤በሊጉ ላይ በመጨረሻ ያደረጉዋቸው ሶስት ጨዋታዎች ያሸነፉ ሲሆን ምናልባት በዛሬው የምሳ ሰአት ጨዋታ ላይ ድል ማስመዝገብ የሚችሉ ከሆነ  በ2022/23 የውድድር አመት ለመጀመሪያ ጊዜ በተከታታይ አራት ጨዋታዎችን ላይ ድል ማስመዝገብ እንዲችሉ ያደርጋቸዋል ።

 
    ከሜዳቸው ውጪ የቅርብ አመታት ተቀናቃኛቸውን የሚገጥሙት የሊቨርፑል  አለቃ ጀርመናዊው የርገን ክሎፕ በአሰልጣኝነት ህይወታቸው ውስጥ ማስታወስ ከማይፈልጋቸው የውድድር አመታት አንዱ የዘንድሮው ሲሆን በ2022/23 የውድድር አመት ከመጀመሩ በፊት ለዋንጫ ከፍተኛ ግምት ካገኙ ቡድኖች ውስጥ አንደኛው የክሎፑ ሊቨርፑል እንደነበር ይታወሳል፤በተለይ በ2021/22 የውድድር ዘመን ላይ ቡድኑ ካሳየው አቋም አሳክቶት ከነበረው ስኬት አንፃር ከፍተኛ ግምት ማግኘቱ ብዙ አስገራሚ አልነበረም።
በተለያዩ ምክንያቶች ሊቨርፑል በዚህ የውድድር ዘመን እያስመዘገበ ያለው ውጤትና የቡድኑ አጠቃላይ እንቅስቃሴ ከተጠበቀው በተቃራኒ ሆኗል ።

  "At the start of this season if you had asked us what we expected in March it would have been to be coming towards the climax of the title race.
Now it is going to be difficult to win a trophy this season. It looks impossible. We will need a miracle, really. So there is a different type of motivation and it is difficult to adjust.
“We have drawn a line and know the top four is everything now. የሊቨርፑል የቀኝ መስመር ተጨዋች አርኖርድ ከቴሌግራፍ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ወቅት የተናገረው ነው።
   አሁን ላይ የሊቨርፑል አሰልጣኞችን ጨምሮ ተጫዋቾቹ መሬት ላይ ያለውን እውነታ ተረድተው ቡድኑ በሚቀጥለው አመት የአውሮፓ ተሳታፊ ለማድረግ የሚያስችለውን ቦታ ለማግኘት በቀሩት ጥቂት መርሀግብሮች እያሳዩ ካሉት አቋም ከፍ በማድረግ የተቻላቸው ያህል መጣር ይኖርባቸዋል።የአውሮፓ ተሳትፎ ለማግኘት የመርሲሳይዱ ቡድን ከነገ ምሳ ሰአት ጀምሮ በሚቀጥሉት ቀናቶች የተጋረጡበትን ፈተናዎች መወጣት ይጠበቅባቸዋል።
 
ሊቨርፑሎች በዚህ የውድድር ዘመን ከሜዳቸው ወጥተው ባደረጉዋቸው 13 ጨዋታ ላይ መሰብሰብ የቻሉት ነጥብ 12 ብቻ ነው ይህም ከሜዳቸው ወጥተው በሊጉ ላይ ትንሽ ነጥብን ከሰበሰብ ቡድኖች መሀል አድርጎታል ሊቨርፑሎችን።
   የክሎፕ ልጆች ዘንድሮ ከሜዳቸው ውጪ ያላቸውን ደካማ ሪከርድ አሻሽለው ከኢቲሀድ ውጤት ይዘው ይመለሱ ይሆን?

   የሲትዝኖቹ ዋነኛ ጎል አስቆጣሪ ኖርዊያዊው የፊት አጥቂ ኤርሊግ ሀላንድ በዚህ ጨዋታ ላይ በጉዳት ምክንያት የመሰለፉ ጉዳይ አጠራጣሪ ሆኗል።
  ስፔናዊው የማንቸስተር ሲቲ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ካለ ዋነኛ አጥቂያቸው ሊቨርፑል ለማሸነፍ ምን አይነት መፍትሔ ይዞ ይገባ ይሆን?

ለሁሉም መልስ ለመስጠት ዛሬ ቀን 8:30 ላይ ማንቸስተር ሲቲ ከሊቨርፑል የከባድ ሚዛኑን ፍልሚያ በኢቲሀድ ያደርጋሉ።


ቅኝት በኳስ ሜዳ
1.3K views03:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 21:49:27
Arsenal Vs Leeds United

በ29ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቅዳሜ 11 ሰዓት ላይ አርሰናል ከሊድስ ዩናይትድ የሚያደርጉትን ጨዋታ በቀጥታ በኢቲቪ መዝናኛ ይከታተሉ።

EBC-መዝናኛ


ቅኝት በኳስ ሜዳ
457 views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 17:27:10
ናይል ቪው ሆቴል

ለሥራም ሆነ ለመዝናናት ወደ ውቢቷ ባህር ዳር ከተማ ካመሩ ማረፊያዎን በናይል ቪው ሆቴል ያድርጉ።

ናይል ቪው ከ90 በላይ ውብ እና ፅዱ የማረፊያ ክፍሎች ያሉት ባለ 9 ፎቅ 4 ስታር ሆቴል ነው።

አድራሻ :- ከባህር ዳር ወደ ጎንደር መውጫ ከአባይ ድልድይ 150 ሜትር እንደተጓዙ ያገኙናል።

+251 90 992 9292
+251 90 991 9191

የፌስቡክ ገጻችን ይቀላቀሉ https://www.facebook.com/NileviewhotelEthiopia
ቴሌግራም ቻነላችን - https://t.me/nileviewhotelbahirdar

ድረ-ገፃችን - www.nileview.com.et

እያንዳንዱ ቀን የደስታ ቀን ነው!

Nile View Hotel
687 views14:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 14:40:22
➥ ሚኬል አርቴታ የመጋቢት ወር ምርጥ አሰልጣኝ በመሆን ተመርጧል

የአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የመጋቢት ወር የፕሪሚየር ሊጉ ኮከብ አሰልጣኝ በመሆን ተመርጧል።

ስፔናዊው አሰልጣኝ በመጋቢት ወር አርሰናልን እየመራ ካደረጋቸው 4 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች አራቱንም በድል ተወጥቷል።

መድፈኞቹ በመጋቢት ወር ኤቨርተን፣ቦርንማውዝ፣ፉልሀምንና ክሪስታል ፓላስን በድምሩ 14 ጎሎችን በማስቆጠር ያሸነፉ ሲሆን ሊጉንም በ8 ነጥብ ልዩነት እየመሩ ይገኛሉ።

ሚኬል አርቴታ በ2022/23 የውድድር ዓመት የወሩ ኮከብ አሰልጣኝ ተብሎ ሲመረጥ አሁን ለአራተኛ ጊዜ ነው።


ቅኝት በኳስ ሜዳ
721 views11:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 13:48:12
➥ ቡካዮ ሳካ የወሩ ኮከብ ተጫዋች በመሆን ተመርጧል

የአርሰናሉ የመስመር አጥቂ ቡካዮ ሳካ የመጋቢት ወር የፕሪሚየር ሊጉ ምርጥ ተጫዋች በመሆን ተመርጧል።

የ21 ዓመቱ እንግሊዛዊው ቡካዮ ሳካ በመጋቢት ወር ሶስት ጎሎችንና ሁለት ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን ለመድፈኞቹ አመቻችቶ አቀብሏል።


ቅኝት በኳስ ሜዳ
727 views10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 17:55:13
የዘካ ተቀማጭ ሂሳብ
=========
ዘካዎትን በዘካ ተቀማጭ ሂሳብ ያስቀምጡ፣
እርስዎ ለመረጧቸው ዘካ ተቀባዮች በቀላሉ እናደርስልዎታለን!
#ramadan #mubarak
1.1K views14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 20:21:53
የማስታወቂያ ሰዓት

➫ አፍሩ ፊልም ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት

ለበርካታ ዓመታት በስራዎቹ አንቱታን ያተረፈው አፍሩ ፊልም ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ በመታገዝ በከፍተኛ ጥራት የተለያዩ ፕሮግራሞች በመቅረጽ ቀንዎን የማይረሳ ያደርጋል።

➫ የዶክመንተሪ ቀረጻዎች ለድርጅቶች
➫ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ማስታወቂያዎች
➫ የሰርግና የልደት ልዩ ቀረጻዎች
➫ የሙዚቃ ክሊፖች
➫ ትልልቅ ኢቨንቶች ማዘጋጀት


እያንዳንዱን ፕሮግራሞች በልዩ ጥራት በአፍሩ ፊልም ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት ያገኛሉ።

ለበለጠ መረጃ ይደውሉልን
+251111263773
+251930004144

የላቀ ጥራት
አፍሩ ፊልም ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት
1.3K views17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 19:12:18
ናይል ቪው ሆቴል

ለሥራም ሆነ ለመዝናናት ወደ ውቢቷ ባህር ዳር ከተማ ካመሩ ማረፊያዎን በናይል ቪው ሆቴል ያድርጉ።

ናይል ቪው ከ90 በላይ ውብ እና ፅዱ የማረፊያ ክፍሎች ያሉት ባለ 9 ፎቅ 4 ስታር ሆቴል ነው።

አድራሻ :- ከባህር ዳር ወደ ጎንደር መውጫ ከአባይ ድልድይ 150 ሜትር እንደተጓዙ ያገኙናል።

+251 90 992 9292
+251 90 991 9191

ቴሌግራም ቻነላችን - https://t.me/nileviewhotelbahirdar

ድረ-ገፃችን - www.nileview.com.et

እያንዳንዱ ቀን የደስታ ቀን ነው!
Nile View Hotel

Nile View Hotel
1.1K views16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 15:22:08
ከ17ተኛ እስከ 27ኛው ሳምንት ያለው የሊጉ መርሃ ግብር ይፋ ሆኗል።

የ2015 ዓ.ም ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ኘሪሚየር ሊግ ከ17ተኛ እስከ 27ኛው ሳምንት ያሉ ጨዋታዎች በአዳማ ከተማ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም እና በሃዋሳ ከተማ ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም እንደሚካሄዱ መገለፁ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ከመጋቢት 23/2015 ዓ.ም እስከ ግንቦት 27/2015 ዓ.ም የሚደረገው ከ17ኛ እስከ 27ኛ ሳምንት ያለው የሊጉ መርሃ ግብር ዛሬ ይፋ ተደርጓል።

የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ አ.ማ

ቅኝት በኳስ ሜዳ
1.0K views12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 07:35:20 አሠልጣኝ ውበቱ አባተ ከጨዋታው በኋላ ምን አሉ?

”ከዓርቡ ጨዋታ ዛሬ አቀራረባችን የተሻለ ነበር ማለት እችላለው”

”ከእኔ በብዙ እጥፍ አቅም ያለው ሰው በዚህ ቦታ ላይ ቢቀመጥ ያሉት እነዚሁ ተጫዋቾች ናቸው”

”…እኛ ካልቻልን ደግሞ የሚችል አካል በቅርብ ጊዜ ወደዛ እንዲመለስ ያደርገዋል ብዬ አስባለው”


”ለአፍሪካ ዋንጫው ለማለፍ ያለን ዕድል በጣም ጠባብ ነው”

ስለጨዋታው….

የመጀመሪያውን ጨዋታ ከመሸነፋችን ጋር ተያይዞ ትንሽ ከዐምሮ ጋር በተገናኘ የሥነ-ልቦና ትግል ተጫዋቾቹ ጋር ነበረን። ከዓርቡ ጨዋታ ዛሬ አቀራረባችን የተሻለ ነበር ማለት እችላለው። ጎሎች ያስተናገድንበት መንገድ ምናልባት ቶሎ ከሪትም እንድንወጣ አደረገን እንጂ በአብዛኛው የጨዋታ ክፍል የተሻለ ለመንቀሳቀስ ሞክረናል።

ቡድኑ ከዓርቡ ጨዋታ ተሻለ ስለተባለበት መንገድ…

በዓርቡ ጨዋታ ባልተለመደ መልኩ ቡድናችን ከምንፈልገው መንገድ ውጪ ነበር። ይሄ ደግሞ ጊኒዎች እንደልባቸው እና እንደፈለጉ በተደጋጋሚ እንዲያጠቁና ብዙ የጎል ዕድል እንዲፈጥሩ አድርጓል ፤ ጨራሽ አልነበሩም እንጂ ካስቆጠሩት የበለጠ ማስቆጠሩት የሚችሉበት ፐርፎርማንስ ነው ያደረጉት። እኛ በተቃራኒው ጥሩ አልነበርንም ነበር። ዛሬ እኛ ከባለፈው ጨዋታ አንፃር በኳስ ቁጥጥርም ሆነ ወደ ጎል በመድረስ ረገድ የተሻልን ነበርን። በእነሱ በኩል በተለይ በሽግግር የሚመጡ ኳሶችን በመጨረሱ በኩል ክሊኒካል ነበሩ። ይሄ ነገር ውጤቱን ይዘን እንዳንወጣ እንቅፍት ሆነን እንጂ ቡድኑ ላይ ባልኩት መስፈርቶች ጥሩ ነገር ነበር ማለት እችላለው።

ወደሞሮኮ ሲመጡ አቅደውት ስለነበረው ውጤት…

አፍሪካ ዋንጫ ላይ ለመካፈል የምንፈልግ ከሆነ ውጤት መያዝ አለብን። ማክሲመም ነጥቡ ደግሞ ሁለቱን ጨዋታዎች ማሸነፍ ነበር ፤ ይህ አልሆነም። ለዚህ ግን እንደ መሠረታዊ ነገር አድርጌ የምቆጥረው የመጀመሪያውን ጨዋታ በምንፈልገው መንገድ አለመቆጣጠራችን ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጥሮብናል። ለአፍሪካ ዋንጫው ለማለፍ ያለን ዕድል በጣም ጠባብ ነው። በእኛ ላይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ላይም የተመሰረተ እንዲሆን አድርጎታል። ከውድድር አንፃር አስቸጋሪ ነገር ውስጥ ነው ያለነው። እርግጥ 100% የማለፍ ዕድላችን አክትሟል ማለት አይቻልም። በሂሳባዊ ስሌት ሙሉ ለሙሉ ውጪ አይደለንም ፤ ግን ዕድሉ የጠበበ ነው።

ስለአጥቂ…

እንደ ሀገር የ9 ቁጥር ተጫዋች የለንም። የትኛው ሰፊ አማራጭ አለን ብለን መጠየቅ አለብን። የምናየው ከሀገር ውስጥ አንፃር ነው። የ9 ቁጥር ጉዳይ ግብ ካለማስቆጠራችን እና ከመሸነፋችን ጋር የሚያያዝ አይደለም። በዓርቡ ጨዋታ ሙሉ ለሙሉ ጨዋታን ከመቆጣጠር ጋር ከዕቅዳችን ውጪ ነበርን። ከጎል ጋር ተያይዞ ግን በርካታ ተጫዋቾች ጎል ጋር እየደረሱ እና የግብ ዕድሎችን እየፈጠሩ ነው። 9 ቁጥር ኖሮም ያለ 9 ቁጥር መጫወትን ልንመርጥም እንችላለን። ለጊዜው ግን 9 ቁጥር ሆኖ በዛ ቦታ ልብ የሚያስደፍር ተጫዋች የለንም። አንዳንዴ ማነፃፀር ይገባናል። ለራሳችን የምንሰጠውም ግምት የተሳሳተ ይመስለኛል። ሜዳ ላይ የእነሱን ተጫዋቾች ተመልከቱ! ይሄንን ለሰበብ ለማቅረብ አይደለም። ከጥራት አንፃር እንደ ሀገር መስራት አለብን። ባለን ነገር የምንችለውን ለመታገል ሞክረናል።

ከግብፁ ጨዋታ በኋላ በጊኒ በተከታታይ ስለመሸነፋቸው…

የግብፁ ጨዋታ እና የጊኒው ጨዋታ የተለየ ነው። በግብፁ ጨዋታ በብዙ ነገር የተሻለ ነበርን። በተለይ ከፊትም ያገኘነውን ዕድል በሚገባ ተጠቅመናል። ከኳስ ቁጥጥር ጀምሮ በብዙ ነገሮች ጥሩ ነበርን። አሁን ያለው ቡድን ውስጥ አራት እና አምስት ተጫዋቾች የሉም። በተጫዋች ብቃትም በጉዳት ምክንያት አብረውን የሉም። የግብፁ ብቻ ሳይሆን የዓርቡ እና የዛሬው ጨዋታም ይለያያል። ዛሬ ከዓርቡ ጨዋታ በተሻለ ተጫውተናል ፤ እንደ አጋጣሚ ሆኖ ግን ተሸንፈናል።

ስለቡድኑ ወጥነት…

ብሔራዊ ቡድን በተለይ እንደኛ አይነት ብሔራዊ ቡድን በወጥነት ለረጅም ጊዜ የሚጫወቱ ተጫዋቾችን ማግኘት ከባድ ነው። ከግብፁ ጨዋታ በኋላ እንኳን የተወሰነ የተጫዋች ልዩነት አለ። በወጥነት የሚጫወቱ ተጫዋቾችንም ማግኘት አንዱ ክፍተት ነው። እንደ ሌሎች ቡድኖች በወጥነት አምስት እና ስድስት ዓመት የሚጫወቱ ተጫዋቾችን እያገኘን ነው ወይ የሚለው ላይ እውነታው የሚያሳየው ያንን አይመስለኝም።

ዞሮ ዞሮ የፈለከው አይነት አቅም ቢኖርህ ፤ ከእኔ በብዙ እጥፍ አቅም ያለው ሰው በዚህ ቦታ ላይ ቢቀመጥ ያሉት እነዚሁ ተጫዋቾች ናቸው። ጥራት ያላቸው ተጫዋቾችን የማፍራት ስራ ላይ እንደ ሀገር መትጋት ያለብን ይመስለኛል ፤ ባለው ነገር ግን የምንችለውን ነገር ለማሳየት ሞክረናል።

ወደአፍሪካ ዋንጫ ስለማለፍ…

ፍላጎታችን ቀጣይ አፍሪካ ዋንጫ ላይ መገኘት ነው። በፍላጎት ደረጃ ይሄ ነው። በነጥብ ደረጃ ግን ይሄንን የሚያመላክት ነገር አይደለም እያየን ያለነው። ያ እንዳይርቅ መስራት ነው ያለብን። ምክንያቱም ኢትዮጵያ በየሁለት ዓመቱ አፍሪካ ዋንጫ ላይ ስትገኝ የነበረች ሀገር እንዳልሆነች ሁላችንም እናውቃለን። ስለዚህ ያ የራቀውን ነገር ለማሳጠር መሞከር ነው። እኛ ካልቻልን ደግሞ የሚችል አካል በቅርብ ጊዜ ወደዛ እንዲመለስ ያደርገዋል ብዬ አስባለው።

ሶከር ኢትዮጵያ
1.1K views04:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ