Get Mystery Box with random crypto!

ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda

የቴሌግራም ቻናል አርማ kegnitbekuasmeda — ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda
የቴሌግራም ቻናል አርማ kegnitbekuasmeda — ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda
የሰርጥ አድራሻ: @kegnitbekuasmeda
ምድቦች: ስፖርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.72K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ በአፍሩ ፊልም ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት ተዘጋጅቶ በኤፍኤም አዲስ 97.1 ላይ ታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች በቀጥታ የሚቀርቡበት ቻናል ነው።

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 50

2022-07-01 06:49:13 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ አሸናፊዉ ዛሬ ይለያል

የ2014 ዓ.ም የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮኑና አንድ ወራጅ ቡድን ያልተለዬ ሲሆን እኚህ ሁለት ጥያቄዎች ዛሬ በሚደረጉ የ30ኛ ሳምንት ጨዋታዎች መልስ ያገኛሉ።

➔ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ አዲስአበባ ከተማ

በባህርዳር ኢንተርናሽናል ስቴዲየም የሚከናወነውና በዲኤስቲቪ የቀጥታ ስርጭት ሽፋን የሚያገኘዉ የቅዱስ ጊዮርጊስና አዲስአበባ ከተማ ጨዋታ ከወዲሁ ከፍተኛ ትኩረትን አግኝቷል።
የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታውን ማሸነፍ 15ኛ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫቸዉን እንዲያሳኩ የሚያደርጋቸው ሲሆን አዲስአበባ ከተማ ደግሞ በሊጉ ለመቆዬት የተሻለ ዕድል ይዞ የ4:00 ሰዓቱን ጨዋታ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።

ፈረሰኞቹ ከዛሬዉ ጨዋታ አስቀድሞ ከተከታያቸዉ ፋሲል ከነማ በአንድ ነጥብ ከፍ ብለዉ ሊጉን እየመሩ ሲሆን ከ2009 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሊጉን ዋንጫ ለማግኘት የ90 ደቂቃ ከባድ ፍልሚያ ብቻ የሚቀራቸዉ ሲሆን አዲስአበባ ከተማ ደግሞ በቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና፣ባህርዳር ከተማና ወልቂጤ ከተማ አሰልጣኝ ጳውሎስ ጌታቸዉ እየተመሩ በሊጉ በመጡበት አመት ላለመዉረድ ከሊጉ መሪ ጋር የሚያደርጉት የከባድ ሚዛን ፍልሚያ ከወዲሁ የበርካታ የስፖርት ቤተሰቦችን ትኩረትን ስቧል።

➔ ድሬደዋ ከተማ ከ ፋሲል ከነማ

ይኼኛው ጨዋታ ደግሞ ሁለቱም ቡድኖች ሻምፒዮናነታቸዉንና ላለመዉረድ የሚያደርጉትን ትንቅንቅ የሚወስኑት በቅዱስ ጊዮርጊስና አዲስአበባ ከተማ መሸነፍ አልያም አቻ መዉጣት ላይ ብቻ ይሆናል።

በአስደናቂ የማሸነፍ ግስጋሴ ላይ የሚገኙት አጼዎቹ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ባለፈዉ ዓመት የሊጉን ዋንጫ እንዲያሸንፉ የረዳቸዉን ስዩም ከበደን በማሰናበት አሰልጣኝ ኃይሉ ነጋሽን በጊዜያዊነት ከቀጠሩ በኋላ እውነተኛ የዋንጫ ተፎካካሪ መሆናቸዉን አረጋግጠዋል።

በዉድድር ዓመቱ አጋማሽ ከመሪዉ ጊዮርጊስ ጋር ያላቸዉ የነጥብ ልዩነት ሰፊ የነበረ ሲሆን በሁለተኛው የዉድድር ዓመቱ አጋማሽ ከፍተኛ የሆነ መሻሻል በማሳዬት ያለቀ የሚመስል የነበረዉን የ2014 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ፉክክር ላይ እንደገና ነፍስ በመዝራት የነጥብ ልዩነቱን በአንድ ብቻ ዝቅ እንዲሉ አድርጓቸዋል።

ፋሲል ከነማ በተከታታይ ሁለት ዓመታት ሻምፒዮን ለመሆን ለግድ የቅዱስ ጊዮርጊስን ነጥብ መጣል ይጠብቃሉ።

ሌላዉ የፋሲል ከነማ ተጋጣሚ የሆነዉ ድሬደዋ ከተማ በሊጉ ለመቆዬት በጣም ጠባብ ዕድል ቢኖረዉም የምስራቁ ቡድን የመጨረሻ ሙከራውን ለማድረግ ከአጼዎቹ ጋር ይፋለማሉ።
30 ነጥቦችን በመሰብሰብ ከላይ ከተቀመጠው አዲስአበባ ከተማ በ2 ነጥቦች ዝቅ ብለዉ 14ኛ ላይ የሚገኙት ብርቱካናማዎቹ በዚህ ከባድ ትንቅንቅ አሸናፊ ሆነዉ ለመገኘት የ4:00 ሰዓቱን ጨዋታ በጉጉት ይጠብቃሉ።
የድሬደዋ ከተማና የፋሲል ከነማ ጨዋታ ረፋድ 4:00 ላይ በባህርዳር ዩንቨርስቲ ስቴዲየም የሚከናወን ሲሆን ጨዋታዉ በአማራ ሚዲያ ኮርፕሬሽን (አማራ ቴሌቪዥን) የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ይኖረዋል።

➔ ሀዋሳ ከተማ ከ አዳማ ከተማ

ሌላኛው በሊጉ የመዉረድ ስጋት ዉስጥ የሚገኘዉ አዳማ ከተማ የተሻለ በሊጉ የመቆየት ዕድል በመያዝ ከሀዋሳ ከተማ ጋር ይጫወታል።
32 ነጥቦችን በዉድድር ዓመቱ የሰበሰቡት አዳማ ምንም እንኳን በተሻለ የጎል ልዩነት 12ኛ ደረጃ ላይ ቢገኙም የወራጁን ወጥመድ ግን ሙሉ ለሙሉ ለመላቀቅ የዛሬዉን የዘጠና ደቂቃ ግዳጅ መወጣት ግድ ይላቸዋል።

ሀዋሳ ከተማ በአንጻሩ ይኼንን ጨዋታ የሚያከናውኑት የ3ኛ ደረጃን ይዞ ለማጠናቀቅ ይሆናል።

የሀዋሳ ከተማና አዳማ ከተማ ጨዋታ ዛሬ ረፋድ 4:00 ሰዓት ላይ በባህርዳር ዓፄ ቴዎድሮስ ስቴዲየም የሚደረግ ሲሆን ጨዋታዉ ግን የቀጥታ ስርጭት ሽፋን አይኖረዉም፤ቢሆንም ግን በሱፐር ስፖርት ቀረጻ ተከናዉኖለት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በድጋሚ የምንመለከትበት ዕድል ይኖራል።


ልብ አንጠልጣዩ ትንቅንቅ፣ሻምፒዮኑንና ወራጁን ያለየዉ ፍልሚያ በመጨረሻም መልስ ለመስጠት ዛሬ 4:00 ሰዓት ላይ በባህርዳር ቀጠሮ ይዟል።

ተጨማሪ የስፖርት መረጃዎችን ለማግኘት ወደ 6655 OK ብለዉ ይመዝገቡ

ቅኝት በኳስ ሜዳ
651 viewsTadesse Abiyu, 03:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 21:06:29
627 viewsTadesse Abiyu, 18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 21:06:19 ማንቸስተር ዩናይትድ የግራ መስመር ተከላካይ ለማስፈረመ ተቃርቧል

ማንቸስተር ዩናይትድ ኦሎምፒክ ሊዮን ለመግባት የቃል ስምምነት ላይ ደርሶ የነበረውን የፌኖርድ የግራ መስመር ተከላካይ ማላሲያ ፊርማውን ከማኖሩ በፊት ጣልቃ በመግባት ልጁን ወደ አልትራፎርድ ለማስኮብለል መቃረቡን ፋብሪዚዮ ሮማኖ የሆላንድ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል፤ሁለቱ ቡድኖች ስምምነት ላይ መድረሳቸውም ተነግሯል።
የማላሲያ ወኪል ከባርሴሎና የመሀል ሜዳ ተጨዋቾች ፍሬንኪ ዲዮንግ ተመሳሳይ መሆኑም ተገልጿል።

በተያያዘ የዩናይትድ የዝውውር ዜና ማንቸስተር ዩናይትድ በፍሬንኪ ዲዮንግ ዝውውር ዙርያ ከ ባርሴሎና ጋር ወደ ስምምነት መጠጋታቸው እየተዘገበ ይገኛል፤ለዝውውሩ ዩናይትድ በጠቅላላ ወደ €85 ሚሊየን እንደሚጠጋ አሁን ላይ €65 ሚሊየን እንደሚከፍሉ ተጨማሪ ክፍያዎች እንዳሉትና ከጭማሪ ክፍያዎቹ ጋር ዩናይትድ ለተጨዋቹ ዝውውር €85 ሚሊየን እንደሚከፍል ተገልጿል።

ተጨማሪ ትኩስ የስፖርት መረጃዎችን በየዕለቱ ለማግኘት በስልክዎ ወደ 6655 Ok ብለዉ ይመዝገቡ!!

ቅኝት በኳስ ሜዳ
577 viewsTadesse Abiyu, 18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 19:14:51
656 viewsTadesse Abiyu, 16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 19:14:24 የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው

በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገደው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ተገልጿል።

ረፋድ ላይ በ29ኛ ሳምንት ወሳኙን ጨዋታቸውን ከሲዳማ ቡና ጋር ያደረጉት አዲስ አበባ ከተማዎች 2-1 መሸነፋቸው ይታወሳል፤ ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ወደ መልበሻ ክፍል ባመሩበት ወቅት የሰባት ተጫዋቾች የእጅ ስልክ መሰረቁን አረጋግጠናል።
ብዙም ያልተለመደው ይህ ጉዳይ እንዴት ሊፈጠር ቻለ የሚለውን የባህር ዳር ከተማ ዘጠነኛ ፖሊስ ጣቢያ ጉዳዮን በመያዝ ምርመራ እያደረገ ሲሆን በድርጊቱ የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ታውቋል።
ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በድርጊቱ ያዘኑት የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባለት ጉዳዩ በፍጥነት ተጣርቶ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ምንጭ:- ሶከር ኢትዮጵያ

ተጨማሪ ትኩስ የስፖርት መረጃዎችን በየዕለቱ ለማግኘት በስልክዎ ወደ 6655 Ok ብለዉ ይመዝገቡ!!
634 viewsTadesse Abiyu, 16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 22:56:04
668 viewsTadesse Abiyu, 19:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 22:55:33 አርሰናል የጋብሬል ሄሱስን ዝውውር አጠናቋል

የሰሜን ለንደኑ ቡድን አርሰናል ጋብሬል ሄሱስን ከማንቸስተር ሲቲ ለማዘዋወር £45 ሚሊየን እንደከፈለ ተዘግቧል።
ሄሱስ ማክሰኞ ወይም ረቡዕ ወደ ለንደን በማቅናት የጤና ምርመራውን እንዲሁም በይፋ ፊርማውን ያኖራል ተብሎ ይጠበቃል።
ሄሱስ በአርሰናል እስከ 2027 ድረስ ለመቆየት መስማማቱ ታውቋል።

ተጨማሪ ትኩስ የስፖርት መረጃዎችን በየዕለቱ ለማግኘት በስልክዎ ወደ 6655 Ok ብለዉ ይመዝገቡ!!

ቅኝት በኳስ ሜዳ
629 viewsTadesse Abiyu, 19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 22:44:52
551 viewsTadesse Abiyu, 19:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 22:44:29 የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ተሳታፊ ከሆኑ ቡድኖች ውስጥ የ"ቶፕ 6" የቅድመ ውድድር ዝግጅት መች ይጀምራሉ ? የወዳጅነት ጨዋታዎች ከማን ጋር ያደርጋሉ ?የቡድኖቹን የቅድመ ውድድር ዘመን እቅድ የምናጋራቹህ ይሆናል።

1. ማንቸስተር ሲቲ
ማንቸስተር ሲቲ በትክክል ወደ ቅድመ ልምምድ መቼ እንደሚመለሱ ባይቀመጥም ፣ ቅድመ ውድድር ልምምዳቸውን እንዲሁም የመጀመሪያ የአቋም መፈተሻ በአሜሪካ እንደሚያደርጉ ታውቋል።
ጁላይ 21 ከ ክለብ አሜሪካ ጋር የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ጁላይ 24 ከባየርን ሙኒክ
ጁላይ 30 በኪንግ ፓወር በእንግሊዝ ኮሚኒቲ ሺልድ ጨዋታ ሊቨርፑል ካስተናገዱ ከሳምንት በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ከዌስተሀም ጋር በሚደረግ ጨዋታ የ 2022/23 የውድድር አመት የሚጀምሩ ይሆናል።

2.ሊቨርፑል
የሊቨርፑል የቡድን አባላት july 4 ልምምድ መስሪያቸው በመሰብሰብ የቅድመ ውድድር ልምምዳቸውን የሚጀምሩት ቀዮቹ ፣ የአቋም መፈተሻ ጨዋታቸው ለማድረግ ጁላይ 9 ወደ ታይላንድ በማቅናት የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ጁላይ 12 ከማንተስተር ዩናይትድ ጋር በባንኮክ የመጀመሪያ የወዳጅነት ጨዋታ ያከናውናሉ።
ጁላይ 15 ከ ክሪስታል ፓላስ ጋር ሁለተኛ ጨዋታዎች ያከናውናሉ።
ጁላይ 27 ከ ሳልዝበር ጋር ጨዋታ ያደርጋሉ።
ጁላ 30 በኪንግ ፓወር ከማንቸስተር ሲቲ ጋር የኮሚኒቲ ሺልድ ጨዋታ ካደረጉ በኋላ በነጋታው ጁላይ 31 ከስትራስቡርግ ጋር በአንፊልድ የመጨረሻ የአቋም መፈተሻ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

2.ቼልሲ
ቼልሲዎች ወደ አሜሪካ ጁላይ 9 ከመብረሩ በፊት በኮብሀም የቅድመ ውድድር ዘመን ዝግጅት ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ጁላይ 16 ከክለብ አሜሪካ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ የአቋም መፈተሻ ጨዋታቸውን ይጀምራሉ።
ጁላይ 20 ከ ቻርለት ጋር ሁለተኛ ጨዋታውን ለማድረግ መርሀግብር ወጥቶለታል።
ጁላይ 23 በአሜሪካ ከአርሰናል ጋር የመጨረሻ የአቋም መፈተሻቸውን ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

4. ቶተንሀም ሆትስፐር
ቶተንሀም ሊጉ ከተጠናቀቀ በኋላ የሀገራት ጨዋታ ላይ ተሳትፎ ያላደረጉ ተጨዋቾች ጁላይ 4 የቅድመ ውድድር ልምምዳቸውን እንዲጀመሩ ተነግሯቸዋል፤የሀገራት ጨዋታ ተሳትፎ ያደረጉ ተጨዋቾች ጁላይ 9 ከቡድኑ ጋር በመቀላቀል ወደ ደቡብ ኮሪያ ከቡድኑ ጋር እንደሚጓዙ ታውቋል።
ጁላይ 13 ቲም ከ ሊግ ጋር የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በደቡብ ኮሪያ በማድረግ ይጀምራሉ።
ጁላይ 16 ከሲቪያ ጋር ይጫወታሉ ።
ጁላይ 23 ከሪንጀርስ ጋር ይጫወታሉ።
ጁላይ 30 ከ ሮማ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ የቅድመ ውድድር ዝግጅታቸውን ይፈፅማሉ።

5.አርሰናል
የሚኬል አርቴታ ልጆች ጁን 27 ወደ ቅድመ ውድድር ዝግጅት ይመለሳሉ።
አርሰናል ወደ ጀርመን በማቅናት
ጁላይ 8 ከ ኖርበርግ ጋር የመጀሪያዉን የአቋም መፈተሻ ያደርጋል።
ጁላይ 16 ከኤቨርተን ጋር ይጫወታሉ።
ጁላይ 20 ከ ኦርላንዶ ሲቲ ጋር ይጫወታሉ።
ጁላዬ 23 ቼልሲ ጋር
ጁላይ 30 በኤምሬትስ ከ ሲቪያ ጋር ጨዋታ በማድረግ የቅድመ ውድድር ዝግጅታቸውን ያጠቃልላሉ።

6.ማንቸስተር ዩናይትድ
አዲሱ ሆላንዳዊው የዩናይትድ አለቃ ተጨዋቾች በጊዜ ወደ ቅድመ ውድድር ዘመን እንዲመለሱ በማድረግ የበለጠ የመዘጋጃ ጊዜ ለማሳለፍ በማሰብ የቡድን አባላቶቹ ጁን 27 ወደ ልምምድ ማዕከል እንዲመጡ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።
ወደ እስያ በማምራት በታይላንድ የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ያደርጋሉ።
ጁላይ 12 ከሊቨርፑል ጋር በሚያደርግጉት ጨዋታ የአቋም መፈተሻ ጨዋታቸውን ይጀምራሉ።
ጁላይ 15 ሜልቦርን ቪክቶር ጋር ይጫወታሉ።
ጁላይ 19 ከክሪስታል ፓላስ ጋር ይጫወታሉ።
ጁላይ 23 አስቶን ቪላ ጋር ይጫወታሉ።
ጁላይ 30 ከ አትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ጨዋታ ካደረጉ በኋላ ጁላይ 31 በኦልትራፎርድ የመጨረሻ የቅድመ ውድድር ጨዋታውን ከ ራዮ ቫዬካኖ ጋር የሚያደርግ ይሆናል።

ተጨማሪ ትኩስ የስፖርት መረጃዎችን በየዕለቱ ለማግኘት በስልክዎ ወደ 6655 Ok ብለዉ ይመዝገቡ!!

ቅኝት በኳስ ሜዳ
565 viewsTadesse Abiyu, 19:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 21:03:40 ዲን ሄንደርሰን ወደ ኖቲንግሃም ፖል ፖግባ ወደ ዩቬንቱስ አቅንተዋል

በተለያዩ ክለቦች በውስት ሲባዝን ከቆየ በኋላ በ2018/19 እና 2019/20 በክሪስ ዋይልር ሲመራ በነበረው ሼፍልድ ዩናይትድ አስደናቂ ጊዜን ማሳለፍ መቻሉን ተከትሎ የእንግሊዛዊው ግብ ጠባቂ እናት ክለብ የሆነው ማንቸስተር ዩናይትድ የዋናው ቡድን ዉስጥ እንዲካተት አድርጎት ነበር።
ወደ እናት ክለቡ ከተመለሰ በኋላ ግን ዲን ሄንደርሰን አብዛኛውን ጊዜ የስፔናዊው ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴሂያ ተጠባባቂ በመሆን ነበር ጊዜውን ያሳለፈው፤ ከ 18 ወራት በኋላ እንግሊዛዊው የ 25 አመት የግብ ዘብ ዲን ሄንደርሰን እስከ ሰኔ 2023 በሚቆይ የውሰት ውል ወደ እንግሊዝ የመጀመሪያው እርከን ከ 23 አመት በኋላ መመለስ የቻለውን ከእንግሊዝ አንጋፋ ቡድኖች ውስጥ አንዱ የሆነውን ኖቲንግሀም ፎረስትን መቀላቀሉን የእንግሊዝ መገናኛ ብዙኃኖች ዘግበዋል።

ከ10 አመት በኋላ ተመሳሳይ ታሪክ በፈረንሳያዊው ዝውውር ላይ ተደግሟል፤በማንቸስተር ዩናይትድ ወጣት ቡድን ባሳየው አስደናቂ እንቅስቃሴ የተማረኩት የቀድሞ የዩናይትድ አለቃ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ወጣቱን ተጨዋች ከሌሎች ሶስት የዩናትድ ወጣት ቡድን ጓደኞቹ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ በ 2011 ለኤፌካፕ 5ተኛ ዙር ፍልሚያ የመጀመሪያ ቡድን ስብስብ ውስጥ እንዲካተት ወደ ላይ አሳድገውት የ42 ቁጥር ማሊያ በመስጠት ያን የውድድር አመት እስኪጠናቀቅ ወጣ ገባ እያለ ለወጣት ቡድኑ ለ ዋና ቡድኑንም የተወሰነ ግልጋሎት መስጠት እንዲችል አድርገውት ነበር።
2011/12 የውድድር ዘመን ፖግባ በቋሚነት የዋና ቡድኑ አባል እንዲሆን ተደርጓል። ይሁንና በወቅቱ ፈረንሳዊው የመሀል ተጨዋቾች ፖል ፖግባ የኮንትራት አመቱ መጨረሻ ላይ ይገኝ ነበርና በዩናይትድ የተወሰነ የጨዋታ እድል በዋና ቡድኑ ማግኘት ቢችልም በተጨዋቹ ወገን የተሰጠው የመጫወቻ እድሜ በቂ ነው ብለው ስላላሰቡ ዩናይትድ ያቀረበለት ኮንትራት የማራዘም ጥያቄ ውድድቅ አድርጎ በ 2012 ቡድኑን በነፃ ለቆ እንዲወጣ ሆኗል።
ከማንቸስተር ዩናትድ ጋር እንደማይቀጥል ከታወቀ በኋላ ፖል ፖግባ ወደ ጣልያን አምርቶ ለጣልያኑ ኃያል ዩቬንቱስ ግልጋሎቱን ለመስጠት ፊርማውን ማኖር ችሏል።
በቱሪን በቆየባቸው 4 አመታት ፖግባ በአግባቡ እራሱን በማሳደግ በተለያዩ የአውሮፓ ክለቦች ትኩረት ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል።
በፖግባ አቋም እንቅስቃሴ ከተማረኩ ተጨዋቹን የግላቸው ለማድግ የዩቬን በር ላይ ከጠኑ የፖግባ ፈላጊዎች መሀል አንዱ የቀድሞ ቡድኑ ማንቸስተር ዩናይትድ ነበር።
ዩናይትድ በ 2016 የወቅቱ የተጨዋቾች ዝውውር ክብረ ወሰን የሆነ ገንዘብ በነፃ ከ አራት አመት በፊት ከቡድኑ ጋር ለተለያየው ተጨዋቾች በመክፈል ወደ ትያትር ኦፍ ድሪም መመለስ ችለዋል።
ኦልድትራፎርድ ከደረሰ በኋላ ግን የመሀል ተጨዋቹ በቱሪን ያሳየውን ብቃት በዩናይትድ አመራሮችና ደጋፊዎች ጭምር ለቡድኑ ይሰጣል የተባውን ግልጋሎት መስጠት አልቻለም፤ሜዳላይ ከሰጠው ግልጋሎቶት ይልቅ ከሜዳ ውጪ ህይወቱ፣ ከአሰልጣኞች ጋር በሚፈጥረው ሰጣ ገባና አለመግባባቶች እንዲሁም የጉዳት ታሪኮቹ የበለጠ ጎልቶ የታየባቸውን ስድስት አመት በዩናይትድ ለሁለተኛ ጊዜ ካሳለፈ በኋላ በተጠናቀቀው የውድድር አመት ፖግባ በድጋሚ በነፃ ዩናይትድ እንደሚለቅ ተረጋገጠ።
ልማደኛው የጣልያኑ ኃያል ቡድን ዩቬንቱስ የ 29 አመቱን ፈረንሳዊው የመሀል ሜዳ ተጨዋቾች ፖል ፖግባን በነፃ ዝውውር በድጋሚ ማስፈረም ችለዋል።
640 viewsTadesse Abiyu, 18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ