Get Mystery Box with random crypto!

ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda

የቴሌግራም ቻናል አርማ kegnitbekuasmeda — ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda
የቴሌግራም ቻናል አርማ kegnitbekuasmeda — ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda
የሰርጥ አድራሻ: @kegnitbekuasmeda
ምድቦች: ስፖርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.72K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ በአፍሩ ፊልም ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት ተዘጋጅቶ በኤፍኤም አዲስ 97.1 ላይ ታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች በቀጥታ የሚቀርቡበት ቻናል ነው።

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 42

2022-08-30 11:42:03
➔ ስኮት ፓርከር የመጀመሪያው የፕሪሚየር ሊጉ ተሰናባች አሰልጣኝ ሆነዋል

የ2022/23 የውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከተጀመረ ገና የአራት ጨዋታዎች ዕድሜ ብቻ ያስቆጠረ ሲሆን አዲስ አዳጊው ቡድን ቦርንማውዝ ከአሁኑ የፕሪሚየር ሊጉን ወጣቱን አሰልጣኝ ማሰናበቱን ይፋ አድርጓል።

ስኮት ፓርከር ቦርማውዝን ከሻምፒዮንሺፑ በቀጥታ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ያሳደጉት ሲሆን በመጀመሪያ የሊግ ጨዋታቸውም የስቴቨን ዠራርዱን አስቶንቪላን 2-0 በመርታት በድል ቢጀምሩም በ2ኛ ጨዋታቸው በማንቸስተር ሲቲ ኢቲሀድ ላይ 4-0 ተሸንፈዋል፤በ3ኛ ሳምንት ደግሞ በሜዳቸው ቫይታሊቲ ስቴዲየም በሰሜን ለንደኑ አርሰናል የ3-0 ሽንፈት ደርሶባቸዋል፤ከሁሉም በላይ ግን ለእኚህ የቀድሞው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የአማካይ ስፍራ ተጫዋች ለስንብት የዳረጋቸው በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ቅዳሜ ዕለት ወደ አንፊልድ ተጉዘው በሊቨርፑል የደረሰባቸው የ9-0 ሽንፈት የፓርከርና ቦርንማውዝ የመጨረሻ የጋብቻ ውል የፈረሰበት ጨዋታ ሆኗል።

የስኮት ፓርከርን ስንብት ተከትሎ ነገ ዕረቡ በ5ኛ ሳምንት በቫይታሊቲ ስቴዲየም ምሽት 3:30 ላይ በ5ኛ ሳምንት የፕሪሚየር ሊጉ መርሐግብር ቦርንማውዝ ዎልቭስን የሚገጥምበትን ጨዋታ በጊዜያዊ አሰልጣኝ ጋሪ ኦኔይል የሚመሩ ይሆናል።

ቦርንማውዝ በፕሪሚየር ሊጉ በ4 ጨዋታዎች 3 ነጥቦችን ሰብስቦ 17ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።


ቅኝት በኳስ ሜዳ
634 views08:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 09:43:53
ቅኝት በኳስ ሜዳ

አፍሩ ፊልም ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፕሬሽን ጋር በመተባበር በኤምኤም አዲስ 97.1 ላይ ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ የሚያደርሱት ቅኝት በኳስ ሜዳ የቀጥታ የእግርኳስ ስርጭት ፕሮግራም በዚህ ሳምንት ጉዞውን ወደ ደቡብ ጠረፍ በማድረግ በሴንት ሜሪ ስቴዲየም በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 5ኛ ሳምንት መርሃግብር ቅዱሳኖቹ ሳውዛፕተን ከሰማያዊዎቹ ቼልሲ ጋር ማክሰኞ ምሽት 3:45 ላይ የሚያደርጉትን ጨዋታ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ ወደ እርስዎ እናደርሳለን።

ሳውዛፕተን ከ ቼልሲ
ሴንት ሜሪ
ማክሰኞ 3:45
ኤፍኤም አዲስ 97.1
በቅኝት በኳስ ሜዳ ከ3:00 ጀምሮ
በጥልቅ ትንታኔ በበሳል የባለሞያዎች አስተያየት

ይጠብቁን!


ቅኝት በኳስ ሜዳ
695 views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 08:56:47
ማንቸስተር ዩናይትድ አንቶኒን ለማስፈረም ተስማማ

የእንግሊዙ ቡድን ማንቸስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን የመስመር አጥቂ አንቶኒ ሳንቶስን ከአያክስ አምስተርዳም ለማስፈረም ስምምነት ላይ ደርሷል።

የ22 ዓመቱ ተስፈኛ ተጫዋች በአያክስ ጥሩ እንቅስቃሴ ማሳየት የቻለ ሲሆን ዩናይትድ ስምምነት ለማድረግ ብዙ እርቀቶችን ከተጓዘ በኋላ በ80.75£ ሚሊየን የክለቡ የምንጊዜም 2ኛው ውዱ ፈራሚ በማድረግ ወደ ክለቡ ቀላቅሏል።

አንቶኒ ሳንቶስ በ2020 በአሁኑ የዩናይትድ አሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሀግ አያክስ አምስተርዳምን የተቀላቀለ ሲሆን ለኔዘርላንዱ ቡድን በ82 ጨዋታዎች 25 ጎሎችንና 22 ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።

ማንቸስተር ዩናይትድ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት አንቶኒ 5ኛ ፈራሚው ሆኗል።

ቅኝት በኳስ ሜዳ
650 views05:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:59:39
ኢትዮጵያዊው አጥቂ አቡበከር ናስር በኤምቲኤን 8 የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ማሜሎዲ ሰንዳውንስ ሱፐር ስፖርት ዩናይትድን 2-0 በረታበት ጨዋታ ያስቆጠራት ጎል
666 viewsTadesse Abiyu, 18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:15:02
➔ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 4ኛ ሳምንት የእሁድ ውጤቶች

አስቶንቪላ 0-1 ዌስትሃም ዩናይትድ
ዎልቭስ 1-1 ኒውካስል ዩናይትድ
ኖቲንግሃም 0-2 ቶተንሀም

ቅኝት በኳስ ሜዳ
689 viewsTadesse Abiyu, 18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 11:49:52
➔ አቶ ኢሳያስ ጅራ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት በመሆን በድጋሚ ተመርጠዋል።
690 viewsTadesse Abiyu, 08:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 08:36:01
➔ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ዛሬ ይመረጣል

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የምርጫ ጠቅላላ ጉባኤ በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ ኢሲኤ አዳራሽ የተጀመረ ሲሆን በዕለቱም የተለያዩ ውሳኔዎች በማሳረፍ የትናንት ውሎውን አጠናቋል።

በመርሐግብሩ የ2014 ዓ.ም በጀት ዓመት አፈጻጸም፣የፋይናንስ ሪፖርትና የኦዲት ሪፖርት በጉባኤው የቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም ለጉባኤው በአጀንዳነት የቀረበው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል እግርኳስ ፌዴሬሽን የጠቅላላ ጉባኤ አባል እንዲሆን የቀረበ ሲሆን ጉባኤው በሙሉ ድምፅ አጽድቋል፤እንዲሁም የአፋር ክልል ያቀረበው አቶ አሊሚራ መሐመድ በስራ አስፈጻሚ ኮሜቴ አባልነት ይወዳደሩልን ጥያቄ በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል።

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የምርጫ ጠቅላላ ጉባኤ በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ሲከናወን ጉባኤው ለቀጣዮቹ አራት አመታት የፌዴሬሽኑን ፕሬዚዳንት የሚመረጥ ይሆናል።
ከወዲሁ ትኩረትን በሳበውና በዕጅ አዙር ትልቁን የእግርኳስ ፌዴሬሽን ስልጣን ለማግኘት ድምጾችን በገንዘብ ለመግዛት ከሚደረጉ ከፍተኛ ጥረቶች ጋር ተደምሮ አሸናፊው ዛሬ የሚለይ ሲሆን በዕጩነት ሶስት ፕሬዚዳንቶች ቀርበዋል።

1. አቶ መላኩ ፈንታ
2. አቶ ኢሳያስ ጅራ
3. ኢ/ር ቶኩቻ ዓለማየሁ

እርስዎ የትኛው ቢመረጥ ለኢትዮጵያ እግርኳስ ይበጃል ብለው ያስባሉ?


ቅኝት በኳስ ሜዳ
730 viewsTadesse Abiyu, 05:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 21:51:10
➔ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 4ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ውጤት

ሳውዝአምፕተን 0-1 ማን ዩናይትድ
ሊቨርፑል 9-0 ቦርንማውዝ
ማን ሲቲ 4-2 ክሪስታል ፓላስ
ቼልሲ 2-1 ሌይስተር
ብሬንትፎርድ 1-1 ኤቨርተን
ብራይተን 1-0 ሊድስ ዩናይትድ
አርሰናል 2-1 ፉልሃም


ቅኝት በኳስ ሜዳ
684 viewsTadesse Abiyu, 18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 07:36:48
➔ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወሳኟን አማካይ በነገው ጨዋታ ያገኛል

በሞሮኮ ራባት ለሚካሄደው 2ኛው የሴቶች የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ በሴካፋ ዞን የማጣሪያ ውድድሩን እያከናወነ የሚገኘው የ2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮኑ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወሳኟን የአማካይ ስፍራ ተጫዋች መሳይ ተመስገንን ከቅጣት መልስ በነገው ጨዋታ ላይ ያገኛል።

በኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ያደገችውና ለኢትዮ ኤሌክትሪክና መከላከያ በአማካይ ስፍራ ላይ በመጫወት ያሳለፈችው መሳይ ተመስገን በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ሻምፒዮናዎቹን ንግድ ባንክን በመቀላቀል ወደ ታንዛኒያ ያመራች ሲሆን በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዎች ላይ የመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ በመካተት ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ አሳይታለች።
ሆኖም በምድቡ ሁለተኛ ጨዋታ የብሩንዲውን ፎፊላን 5-1 ኢትዮጵያዊ ንግድ ባንክ ባሸነፈበት ጨዋታ 71ኛው ደቂቃ ላይ በቀጥታ ቀይ ካርድ የተሰናበች ሲሆን አወዳዳሪው አካልም የአንድ ጨዋታ ቀጥታ አስተላልፎባት የምድቡ ሶስተኛ ጨዋታ የሩዋንዳውን ኤኤስ ኪጋሊን 2-0 በረቱበት ጨዋታ መሠለፍ አልቻለች ነበር።

የአንድ ጨዋታ ቅጣቷን የጨረሰችው ወጣቷ የአማካይ ስፍራ ተጫዋች መሳይ ተመስገን ነገ በግማሽ ፍጻሜው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከዩጋንዳው ሺ ኮርፖሬት ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ላይ እንደምትሰለፍ ቅኝት በኳስ ሜዳ አረጋግጣለች።


ቅኝት በኳስ ሜዳ
97 viewsTadesse Abiyu, 04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 00:59:04
➔ ኤሪክ ቴን ሀግ የመጀመሪያ ድላቸውን አስመዝግበዋል

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 3ኛ ሳምንት መርሃግብር በኦልድትራፎርድ ስቴዲየም ማንቸስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን 2-1 በማሸነፍ በውድድር አመቱ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል።

በሊጉ ሁለት ተከታታይ የመክፈቻ ጨዋታዎችን በብራይተንና ብሬንትፎርድ የተሸነፉት ማንቸስተር ዩናይትድ በዛሬው ጨዋታ ሀሪ ማጓየርንና ክሪስቲያኖ ሮናልዶን በተቀያሪ ቦታ በማስቀመጥ የጀመሩ ሲሆን ጎል ለማስቆጠርም 16 ደቂቃ ብቻ ፈጅቶባቸዋል፤በጄደን ሳንቾ አማካኝነት 16ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥረው ገና በጊዜ መሪ መሆን ችለዋል።
ከዕረፍት መልስ ማርከስ ራሽፎርድ ተጨማሪ ጎል ለዩናይትድ በማስቆጠር የጎል ልዩነቱን ወደ ሁለት ከፍ ያደረገ ሲሆን ወደ ጨዋታው መጠናቀቂያ አካባቢ ሊቨርፑል በመሀመድ ሳላህ አማካኝነት ጎል በማስቆጠር ወደ ጨዋታው ለመመለስ ጥረት ቢያደርጉም ተጨማሪ ጎል ሳያስቆጥሩ ጨዋታው በማንቸስተር ዩናይትድ 2-1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

ሊቨርፑል በ2022 ለመጀመሪያ ጊዜ በፕሪሚየር ሊጉ ተሸንፏል

ኤሪክ ቴን ሀግ በዩናይትድ ቤት የመጀመሪያ ድላቸውን አሳክተዋል

ማንቸስተር ዩናይትድ በፕሪሚየር ሊጉ ሊቨርፑልን ሲያሸንፍ ከ2018 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው

መሀመድ ሳላህ ማንቸስተር ዩናይትድ ላይ 10 ጎሎችን ያስቆጠረ የመጀመሪያው የሊቨርፑል ተጫዋች ሆኗል።

ማርከስ ራሽፎርድ ለማንቸስተር ዩናይትድ በሁለም ውድድሮች ጎል ሲያስቆጥር ከ997 ደቂቃዎች በኋላ ነው

በቀጣይ ማንቸስተር ዩናይትድ በ4ኛ ሳምንት በመጪው ቅዳሜ ወደ ሴንት ሜሪ በማቅናት ከሳውዛፕተን ጋር 8:30 ላይ ሲጫወት ሊቨርፑል ደግሞ በአንፊልድ የስኮት ፓርከሩን ቦርንማውዝን ይገጥማል።



ቅኝት በኳስ ሜዳ
220 viewsTadesse Abiyu, 21:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ