Get Mystery Box with random crypto!

ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda

የቴሌግራም ቻናል አርማ kegnitbekuasmeda — ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda
የቴሌግራም ቻናል አርማ kegnitbekuasmeda — ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda
የሰርጥ አድራሻ: @kegnitbekuasmeda
ምድቦች: ስፖርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.72K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ በአፍሩ ፊልም ፕሮሞሽንና ኢንተርቴይመንት ተዘጋጅቶ በኤፍኤም አዲስ 97.1 ላይ ታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች በቀጥታ የሚቀርቡበት ቻናል ነው።

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 49

2022-07-18 10:51:12
191 viewsTadesse Abiyu, 07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-18 10:50:59 ➔ የኢትዮጵያ አትሌቶች የሚሳተፉበት ሶስት የፍጻሜ ዉድድሮች ዛሬ ይካሄዳሉ

በአሜሪካ ኦሪገን እየተከናወነ በሚገኘዉ 18ኛዉ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና እስካሁን በሴቶች 10ሺህ ሜትር አንድ ወርቅና በወንዶች ማራቶን ወርቅና ብር በድምሩ ሶስት ሜዳልያዎችን ያገኘችው ኢትዮጵያ ዛሬም ተጨማሪ ሜዳልያዎችን ለማግኘት በሶስት የፍጻሜ ዉድድሮች ላይ ተሳታፊ ትሆናለች።

ሴቶች ማራቶን ቀን 10:15
ትናንት በወንዶች ማራቶን የወርቅና ብር ሜዳልያ ማግኘት የቻለችዉ ኢትዮጵያ ዛሬም ተጨማሪ ሜዳልያዎችን ለማግኘት በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ቀን 10:15 ላይ በሴቶች ማራቶን በሶስት አትሌቶች ተስፋ አድርጋለች።
ጎተይቶም ገ/ስላሴ
አባበል የሻነህ
እሸቴ በከሬ

የወንዶች 3000 መሰናክል ፍጻሜ ሌሊት 11:20
ዛሬ ለነገ አጥቢያ ከሚከናወኑ ዉድድሮች መካከል የ3000 ሜትር የወንዶች መሰናክል አንዱ ሲሆን በዚህ ዉድድር ኢትዮጵያ ሶስት አትሌቶቿን ታሳትፋለች።
ኃይለማርያም አማረ
ጌትነት ዋለ
ለሜቻ ግርማ

የሴቶች 1500 ሜትር ፍጻሜ ለሊት 11:50
ተጨማሪ ሜዳልያዎችን ለማግኘት ኢትዮጵያ ወደ ፍጻሜ ካለፈችባቸዉ ርቀቶች አንዱ የሴቶች 1500 ሜትር ሲሆን በዚህ ዉድድር ኢትዮጵያ በተጨማሪ ሶስት አትሌቶች ዉክልናን አግኝታለች።
ሂሩት መሸሻ
ጉዳፍ ጸጋዬ
ፍሬወይኒ ኃይሉ

መልካም ዕድል ለአትሌቶቻችን....

➔ ለተጨማሪ የስፖርት መረጃዎች ወደ 6655 OK ብለዉ ይላኩ

ቅኝት በኳስ ሜዳ
193 viewsTadesse Abiyu, 07:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 11:20:45
197 viewsTadesse Abiyu, 08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 11:20:35 ➔ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች የሚሳተፉበት ወሳኝ ዉድድሮች ዛሬ ይካሄዳሉ

በ18ኛዉ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ብሔራዊ ቡድን ትናንት በሴቶች 10 ሺህ ሜትር በለተሰንበት ግደይ አማካኝነት የመጀመሪያ ወርቅ ለኢትዮጵያ ያስገኙ ሲሆን ዛሬ ተጨማሪ ሜዳልያዎችን ለማግኘች ወሳኝ ዉድድሮችን ያከናውናሉ።

የማራቶን ወንዶች ቀን 10:15 ላይ
በማራቶን ዉድድሮች ስማቸዉ ከፍ ብሎ ከሚጠቀሱ ሃገራቶች መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ስትሆን ዛሬ በአራት አትሌቶቿ አማካኝነት ኦሪገን ላይ ደማቅ ታሪክ ለመጻፍ 10:15 ቀን ላይ ትፋለማለች።
በዚህ ዉድድር በኢትዮጵያ በኩል ሌሊሳ ዴሲሳ፣ ሞስነት ገረመዉ፣ሰይፉ ቱራ እና በታምራት ቶላ አማካኝነት ትወከላለች።

10 ሺህ ሜትር የወንዶች ፍጻሜ 5:00 ምሽት

ይህ ዉድድር በርካታ ኢትዮጵያዊያን በጉጉት የሚጠብቁትና ትናንት ምሽት ላይ በሴቶች የተፈጸመዉ አስደናቂ ገድል ዛሬም ኢትዮጵያ ሜዳልያ የምትጠብቅበት ርቀት ነዉ።

በእዚህ ርቀት ላይ ኢትዮጵያ በሪሁ አረጋዊ፣ሰለሞን ባረጋ እና ታደሠ ወርቁ ይወክሏታል።
የ10ሺህ ሜትር የወንዶች የፍጻሜ ዉድድር ዛሬ ምሽት 5:00 ላይ ይካሄዳል።

የወንዶች 1500 ሜትር ግማሽ ፍጻሜ

➔ ዛሬ ለነገ አጥቢያ ከሚከናወኑ ዉድድሮች መካከል የ1500 ሜትር የወንዶች ግማሽ ፍጻሜ ዉድድር አንዱ ሲሆን በዚህ ርቀት ላይ ኢትዮጵያ በሳሙኤል ተፈራና ታደሠ ለሚ ትወከላለች።
ይህ የማጣሪያ ዉድድር ሌሊት 11:00 ላይ ይካሄዳል።

በእስካሁኑ 18ኛዉ የኦሪገን የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ አንድ የወርቅ ሜዳልያ ማግኘት ችላለች።

መልካም ዕድል ለአትሌቶቻችን....

➔ ለተጨማሪ የስፖርት መረጃዎች ወደ 6655 Ok ብለዉ ይላኩ

ቅኝት በኳስ ሜዳ
206 viewsTadesse Abiyu, 08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 15:24:25
329 viewsTadesse Abiyu, 12:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 15:24:17 ተጨዋቾች ላይቸገር ይችላል ልንል እንችላለን። ሀላንድ በቁመት ዘለግ ያለ ማለቱ ብቻ ሳይሆን ወደ ራሳቸው ሳጥን ተጠግተው የሚጫወቱ ቡድኖች ላይ የበላይ ሊሆን ይችላል እንድንል የሚያደርገን ከሀላንድ ጥንካሬዎች ዋነኞቹ ሳጥን ውስጥ የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ማለትም ቦታ የሚይዝበት መንገድ እና ራሱን ከተቃራኒ ተከላካይ ነፃ አድርጎ ኳሱን ለመጠቀም የሚሞክርበት መንገድ ናቸው።

ሀላንድ ማሻሻል ከሚኖርበት ነገሮች አንዱ ወይም ልጁ ላይ እንደ ድክመት የሚነሳው ነገር ኳስ የማቀበል ስኬቱ ነው። ፔፕ ጓርዲዮላ አጥቂዎች ቡድኑ ኳስ በሚቆጣጠርበት ጊዜ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ይፈልጋል፤ሀላንድም ተሳትፎ በማድረግ ችግር የለበትም ፤ ችግሩ ኳሱን ተቀብሎ ለማስቀጠል በሚሞክርበት ጊዜ ስኬታማ ኳስ ማድረስ ላይ ነው። ሀላንድ ኳሱን ለመቀበል በሚሞክርበት ወቅት የሰውነት አቋቋሙ በመጀመሪያ ኳሱ በትክክል እንዳይቆጣጠር አልያም ሁለተኛ ውሳኔው በተፈለገው ደረጃ ስኬታማ እንዳይሆን እንደሚያደርገው የልጁን ስካውቲንግ ሪፓርት በምንመለከት ጊዜ ተገንዝበናል።
ሌላኛው ሀላንድ ያገኛቸውን ኳሶች በአንድ ንክኪ ለማቀበል የሚመርጥ ተጨዋቾች ነው። ይህ ደሞ የሚያቀብላቸው ኳሶች ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዳይሆን እና የማቀበል ስኬቱ እንዲወርድ እንዳደረገው ይታመናል፤ ይህ ድክመቱ በፔፕ ስር ያሻሽላቸዋል ብለን ከምናስባቸው ነገሮች አንዱ ነው።

ወደ ውኃ ሰማያዊዎቹ ባለንበት የዝውውር መስኮት የተቀላቀለው ሌላኛው ወጣት የፊት አጥቂ አልቫሬዝ ደግሞ ከአርጀንቲና ወደ አውሮፓ በቀጥታ መምጣቱ በአውሮፓ ሚዲያዎችና እግርኳስ ተመልካቾች በስፋት የሚታወቅ ስም እንዳይኖረው ያደርጋል። ይህ ደገሞ ከሀላንድ በተቃራኒ ጫና ሳይኖርበት በጊዜ ሂደት ውስጥ ከቡድን አጋሮቹ እና ከሊጉ ጋር እንዲላመድ እንዲሁን አቅሙን አውጥቶ እንዲጫወት ሊያደርገው ይችላል። አርጀቲናዊው የፊት አጥቂ የማንቸስተር ሲቲ አመራሮች ወደ ኢቲሀድ እንዲያመጡት ያደረጋቸው ቀጣዮቹ አመታት ላይ ለቡድኑ ሊሰጣቸው የሚችሉት የልጁ እምቅ አቅም ብቻ ሳይሆን ምናልባት በአዲሱ የወድድር ዘመን ላይ በፔፕ ስር የመጫወቻ ጊዜ አግኝቶ ለቡድኑ መጨመር የሚችለው አቅም ስላሉትም ጭምር ነው።
ልጁን አንደኛ ተፈላጊ ያደረገው ሁለገብ መሆኑ ነው፤ ከፊት አጥቂ ውጪ በፔፕ 4-3-3(4-2-3-1) የተጫዋች አደራደር ላይ ፊት መስመር ላይ ያሉት ሁሉም ቦታዎች ላይ ተሰልፎ መጫወት ይችላል። ከኳስ ጋር ምቹ መሆኑ እንዳለ ሆኑ ያለ ኳስ ታታሪና ታጋይ መሆኑ በስፔናዊው አሰልጣኝ እንዲወደድም አድርጎታል።

ወጣቱ አጥቂ በኢቲሀድ ሊያሻሽለው ይችላል ተብሎ ከሚጠበቁ ነገሮች ውስጥ አንዱ በተለይ ከመስመር ተነስቶ እንዲጫወት በሚደረግበት ወቅት ቦታው ላይ ታግሶ ኳስ መጠበቅ ላይ ነው፤ በአርጀቲና ልጁን ያዩት ባለሙያዎች ይናገራሉ 'አልቫሬዝ በኳስ እንቅስቃሴ የሚሳብ ተጨዋች ነው' ይሉታል። በተለይ ፔፕ የመስመር አጥቂዎቹ መስመሩን እንዲለጥጡለትና በትዕግስት መስመሩ ላይ በመሆን ኳሱን እንዲጠብቁ ስለሚፈልግ ልጁን ወደ ስብስቡ ከቀላቀለ በኋላ በዚህ ጉዳይ ከልጁ ጋር ሊሰራ እንደሚችል ይጠበቃል። ነገር ግን ይህ ሲባል ልጁን ሙሉ ለሙሉ ወደ መስመር ተጨዋቾችነት ይቀይረዋል ማለት ግን አይደለም። ምናልባት የፊሊፕስ ወደ ቡድኑ መምጣቱ እንዲሁም የብራይተኑ የመስመር ተከላካይ ኩኩሬያ ቡድኑን የሚቀላቀል ከሆነ ለቡድኑ ምን አይነት አማራጮችን ይጨምሩለታል የሚለውን ስንመለከት አልቫሬዝ ከመስመር እየተነሳ ማጥቃቱ ላይ ዋነኛ ትኩረት በማድረግ አሁን ያለውን ብቃቱን ሊያጎለብት እንደሚችል ይታሰባል።

➔ ዉድ የቅኝት በኳስ ሜዳ ቤተሰቦች ማንቸስተር ሲቲ በ2022/23 የዉድድር ዓመት ከባለፈዉ ዓመት ተሻሽሎ ለመምጣትና ለተፎካካሪዎችን ምንም ክፍተት ላለመተዉ ክፍተቶችን እየሞላ ይገኛል።
በቀጣይም የሌሎች ቡድኖችን እንቅስቃሴ በስፋት የምንመለከት ይሆናል።

ቅኝት በኳስ ሜዳ
379 viewsTadesse Abiyu, 12:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 15:24:17 ➔ ማንቸስተር ሲቲን በ2022/23 በምን መልኩ ልንመለከተዉ እንችላለን?

ለትንታኔያችን እንደ መንደርደሪያ የምንጠቀመዉ የማንቸስተር ሲቲ ዋና ስራ አስኪያጅ ፋራን ሶሪያኖ በቅርቡ ከሰጡት ሀሳብ ይሆናል። " the current squad is very good. we need to change only what we need to change and we need to change two things : we need a striker we have it and we need a replacement for fernandinho. we have one rodri ,but we need another because the season is very long.

ማንቸስተር ሲቲ በአውሮፓ ላይ ጥሩ የተጨዋቾች ስብስብ ከያዙ ቡድኖች አንዱ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፤ይህ ቢሆንም ግን ቡድኑ ጥገናዎች አይፈልግ ማለት ግን አይደለም፤ እውን በአመት በሊግ ላይ ብቻ ከ 90 በላይ ጎል ያስቆጠረ ቡድን አጥቂ ለማስፈረም ወደ ገበያ መውጣት ያስፈልገው ነበር ? ያስቆጠረውን የጎል ብዛት ብቻ ከተመለከትን ምናልባት ኧረ በፍፁም ምን አጥቶ ልንል እንችላለን፤ነገር ግን የፊት አጥቂ ወደ ቡድኑ መቀላቀሉ አስፈላጊ ነው የምንለው ትክክለኛ የፊት አጥቂ ባለመያዙ ውጤት ያጣባቸው ጨዋታዎች ስንት ናቸው ? ብለን ስንጠይቅ ነው።
በተለይ የተሻሉ ተጨዋቾች ከያዙ ቡድኖች ጋር ? የሚለውን በምንመለከት ጊዜ በተለይ በጥሎ ማለፍ ጨዋታ ላይ የሚመክኑት ኳሶች ቡድኑን ዋጋ እንዳስከፈሉት የምንረዳ ሲሆን የሲቲ መልማዮችም ወደ ቡድናቸው የፊት አጥቂ መጨመራቸው በጎ የሚያስብል ስራ እንደሆነ ልብ እንላለን።

ፔፕ ጓርዲዮላ "የፊት መስመር አጥቂ አይፈልግም ወይም ያለ አጥቂ የተሻለ ቡድን ነው የሚሰራው" የሚሉ ሀሳቦች በተደጋጋሚ በመገናኛ ለብዙኀን የሚሰራጩ መረጃዎች እንደሆኑ ይታወቃል።
እንደውም በተጠናቀቀው የውድድር አመት ቡድኑ ያለ አጥቂ እየተጫወተ ጎሎችን እያስቆጠረ ውጤት እያስመዘገበ በነበረበት ወቅት ጓርዲዮላ በጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለ አጥቂ ከጋዜጠኞች ጥያቄ በተነሳበት ወቅት" I think the club need a striker ,definitely. You say we play fantastically well without a striker because we are winning. When we are not winning ,you say we need striker." ብሎ ነበር ለተነሳለት ጥያቄ መልስ የሰጠው። በዛው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ፔፕ አጥቂ እንደሚያስፈልገው ብቻ ሳይሆን ያለ አጥቂ ቡድኑ ጥሩ እየተንቀሳቀሰ ቢሆንም ሁሌ ይሳካል ማለት አለመሆኑ ወይም ከአቅም በላይ የሚሆኑበት ጨዋታዎች እንዳሉ አመላክቶ ነበር።

ስለዚህ መጠየቅ የሚኖርብን ፔፕ ምን አይነት አጥቂ ነው የሚፈልገው ? ወይም ከአጥቂዎች ጎል ብቻ ነው የሚጠይቀው ? የሚለውን ይመስለኛል። ፔፕ በአንድ ወቅት አጉዌሮ ጎሎች እያስቆጠረ በነበረበት ወቅት ስለ ፊት አጥቂው ጥያቄ በቀረበለት ሰዓት ተከታዩን ሀሳብ ነበር ያጋራው" to score five goals in two games is a good statistic. But he has to help us in the first pressure and run a lot and help us a lot with movements.you can't be brilliant when you disappear When you don't have the ball."

ስፔናዊው የማንቸስተር ሲቲ አለቃ ከአጥቂዎቹ ጎል ብቻ ሳይሆን ያለኳስ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ቦታዎችን በመፍጠር እንዲሁም የተቃራኒ ቡድኑ ኳስ በሚይዙበት ወቅት መከላከሉን በማስጀመር ቡድኑን እንዲያግዙለት ይፈልጋል።
አሰልጣኙ ከፊት መስመር አጥቂው ከጎል አዳኝነት በተጨማሪ ምን ይፈልጋል የሚለውን በዚህ መልኩ ካየን የመጡት ተጨዋቾች ለእርሱ የሚሆን ነገር አላቸው ወይ ? የሚለውን እና ማሻሻል የሚኖርባቸው ነገር ለመመልከት እንሞክራለን።

የአጥቂ አቅም ዋነኛ መለኪያ ጎል ነው የምንል ከሆነ እና ወደ ፔፕ ስብስብ የተቀላቀሉትን የፊት አጥቂዎቹ አልቫሬዝ እና ሀላንድ ሲጫወቱበት በነበረው ሊግ ላይ ለቡድናቸው ያስቆጠሯቸውን ጎሎች ከተመለከትን እንዲሁም ገና አቅማቸው ከዚህ በላይ የማደግ እድል እንዳለው ታሳቢ ካደረግን ግዢው ለቡድኑ ጠቃሚ መሆኑን እና ለቡድኑ የሚጨምሩት አንዳች ነገር እንዳለ መመስከር ያስችለናል። ሀላንድ የጀርመኑን ቦርሲያ ዶርትሙንድን ከተቀላቀለ በኋላ በጨዋታ ቢያንስ አንድ ጎል ያስቆጥር ነበር ፤ ካስቆጠራቸው ጎሎች መሐል የፍፁም ቅጣት ምት ጎሎችን አውጥተን ከፍፁም ቅጣት ምት ውጪ በጨዋታ ያስቆጠራቸው ጎሎች 0.81 ናቸው፤ ወጣቱ አርጀቲናዊው የፊት አጥቂ አልቫሬዝ ደግሞ በአርጀቲናው ሪቨር ፕሌት በሚጫወትበት ጊዜ በ 90 ደቂቃ በአማካይ 0.8 ጎሎች ያስቆጥር ነበር ተጫዋቹ ከጎል ጋር የሚገናኝበትን ደቂቃ አማካይ ስናሰላው ደግሞ በየ 120 ደቂቃው ይሆናል።

ቁጥሮቹን እንደወረደ አይተን አውዱን ወደ ፕሪሚየር ሊግ አምጥተን መጠቀም አስቸጋሪ ያደርገዋል፤በተለይ በሊጎቹ መሀል ያለው ልዩነት ደግሞ ይህንን እንዳንል ዋነኛው ምክንያታችን ነው።
ከጀርመን ወደ እንግሊዝ ዝውውሩን የፈፀመው ኖርዊያዊው የፊት መስመር ተጨዋች ሀላንድ በደጋፊዎችም ሆነ በሚዲያ የሚጠበቅበት ነገር ከፍ ያለ ነው። ለአንዳንዶች ይህ ዝውውር በጥርጣሬ እንዲመለከቱት የሚያደርግ ያለፉ ታሪኮችም አሉ። ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ከጀርመን ወደ እንግሊዝ ከመጡ በኋላ በጀርመን የነበራቸውን ብቃት ለመድገም ሲቸገሩ ያስተዋልናቸው ተጫዋቾች አሉ።
በቅርቡ ከ ጀርመን ወደ እንግሊዝ ከመጡ በኋላ የእንግሊዝን ህይወት ለመላመድ ከተቸገሩ ተጨዋቾች መካከል የቀድሞ የሀላንድ የቡድን አጋር እና ባሳለፍነው የውድድር ዘመን ማንቸስተር ዩናይትድን የተቀላቀለው ጄደን ሳንቾ የመጀመሪያ አመት የማንቸስተር ህይወቱ ቀላል አልሆነለትም ነበር (የተለያዩ ምክንያቶች ቢኖሩም )። ሌላኛው ደግሞ ቲሞ ቨርነር ነው፤ ቨርነር በጀርመን ቡንደስሊጋው ላይ ጎሎችን በማስቆጠር በሎቫንዶቭስኪ ብቻ ነበር የሚበለጠው ፤ ወደ ለንደን ከመጣ በኋላ ግን በጀርመን ያሳየው ብቃት ለመድገም ተቸግሮ ነበር፤ ከሀላንድ በተቃራኒ የቆመው አንድ ጥናት የሚያሳየው ከጀርመን ቡንደስሊጋ ወደ ፕሪሚየር ሊግ የሚመጡ ወጣት አጥቂዎች በዘጠና ደቂቃ የሚያገኙት ጎል ሊሆኑ የሚችሉ እድሎች(XG) ወደ 0.07 ይወርዳል ይላል። ለዚህ ዋነኛ ምክንያት በሁለቱ ሊጎች መሀል ያለው የአጨዋወት መንገድ መለያየት እንደሆነም ይነሳል። በቡንደስሊጋ አጥቂዎች ከተቃራኒ ጀርባ ሰፊ የመሮጫ ቦታዎች አላቸው፤በእንግሊዝ በተለይ እንደ ማንቸስተር ሲቲና ሊቨርፑል ያሉ ቡድኖችን ጋር ሲጫወቱ የተቀሩት አብዛኞቹ ቡድኖች ለራሳቸው ጎል ተጠግተው ቦታ ለተጋጣሚያቸው ላለመስጠት በመከልከል ለመጫወት ስለሚሞክሩ አጥቂዎች ግልፅ የሚባሉ እድሎች የሚፈጥሩበትን መንገድ እንዲቀንስ ያደርገዋል።

እንደ ሀላንድ አይነት አጥቂ ፔፕ ጓርዲዮላ የፈለገበት ምክንያት አንደኛው ወደ ራሳቸው ሜዳ ተጠግተው የሚከላከሉ ቡድኖችን ለማስከፈት መሆኑ የሚታወቅ ነው። በፕሪምየር ሊጉ ባለፉት አምስት ዓመታት ከፍፁም ቅጣት ምት ጎሎች ውጪ የመሐል አጥቂዎች በግንባራቸው ያስቆጠሯቸው ጎሎች 19% ናቸው። የሲቲ አጥቂዎች ደግሞ 17% የሚሆነውን ጎል በጭንቅላት ነው ያስቆጠሩት። ይህንን መነሻ አድርገን ከተመለከትን ምናልባትም ሀላንድ ከሱ በፊት ከጀርመን ወደ ፕሪምየር ሊጉ መጥተው በሊጉ የአጨዋወት መንገድ ምክንያት ብቃታቸውን ለማሳየት እንደተቸገሩት ሌሎች
307 viewsTadesse Abiyu, 12:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 19:12:33
739 viewsTadesse Abiyu, 16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 19:12:24 የተጠናቀቁ የዝውውር ዜናዎች
ብራዚላዊው የኤቨርተን የመስመር አጥቂ ሪቻርሊሰን የሰሜን ለንደኑን ቶተንሀምን በ£60 ሚሊየን መቀላቀሉ ይፋ ሆኗል።
ማንቸስተር ሲቲ ሁለት ተጨዋቾችን ወደ ቡድኑ መቀላቀሉ ቀላቅሏል፤አምበላቸውን በዚህ የዝውውር መስኮት ያጡት ውኃ ሰማያዊዎቹ ለሱ ተተኪ በማድረግ የ 26 አመቱን እንግሊዛዊው ካልቨን ፍሊፕስን ከ ሊድስ በ £45 ሚሊየን ማስፈረማቸውን ተረጋግጧል፤በተጨማሪም ሁለተኛ ግብ ጠባቂያቸው ዛክ ስቴፈን በውሰት ውል ሊለቅ መሆኑን ተከትሎ ለሱ ምትክ ስቴፈን ኦርቴጋ ማስፈረማቸው ይፋ አድርገዋል።

ሊቨርፑሎች ሳይጠበቅ የኮከባቸውን ውል እንዳራዘሙ ይፋ አድርገዋል።
ሊቨርፑል ኮንትራቱ ሊጠናቀቅ አንድ አመት ቀርቶት የነበረውን ግብፃዊውን የፊት መስመር ተጨዋቾች መሀመድ ሳላህ እስከ 2025 ለማቆየት ከስምምነት ደርሰዋል፤ሊቨርፑል ለሳላህ በሳምንት £ 350,000 ለመክፈል መስማማታቸው ተዘግባል።

ለተጨማሪ የስፖርት መረጃዎች ወደ 6655 OK ብለዉ ይመዝገቡ!!

ቅኝት በኳስ ሜዳ
656 viewsTadesse Abiyu, 16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 06:49:27
669 viewsTadesse Abiyu, 03:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ