Get Mystery Box with random crypto!

ISLAM IS UNIVERSITY

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY
የሰርጥ አድራሻ: @islamisuniverstiy_public_group
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.69K
የሰርጥ መግለጫ

⭐️ሰው የሚገነዘብ አእምሮና የሚያፈቅር ልቦና ባለቤት ነው።እነዚህ ሁለቱ ካልተመጣጠኑ ስብእናው አደጋ ውስጥ ነው።የሚያገናዝበው አዕምሮው፣የሚያፈቅረው ልቡ፣የሚንቀሳቀሰው አካሉናወደ ሰማይ የሚወነጨፈው መንፈሱ በውህደት ካልተንቀሳቀሱ ሰውየው ላይ ችግር አለ ማለት ነው
📨የፍቅር እና የጥላቻ ስሜቱ፣የፍላጎት እናየፍርሃት መንፈሱ በአዕምሮ ብስለት ካልተገራ አስቸጋሪ ነው
አስተያየት👇
T.me/Aisuu_bot

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-05-05 14:17:12
«ከጥቂት ጭፍራ በአላህ ፈቃድ ብዙን ጭፍራ ያሸነፈች ብዙ ናት፤ አላህ ከታጋሾች ጋር ነው» አሉ፡፡ »
[አልበቀራህ 249 ]

አላህ እውነትን ተናገረ!
 
4.7K views11:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-04 06:32:28
ፈጣሪን አግኝቼ የመጠየቅ ዕድል ቢኖረኝ

አልበርት አይንስታይን እንዲህ ይላል:: ፈጣሪን አግኝቼ ጥያቄ መጠየቅ ብችል  ዓለምን(Universe) ለምን እንደፈጠረ እጠይቀው ነበር፡፡ ዓለምን ለምን እንደፈጠረ ካወቅኩ በኋላ እኔ ለምን እንደተፈጠርኩ አውቅ ነበር ይላል፡፡

እስልምና ውስጥ ግን እርሱ ለጠየቃቸው  ጥያቄዎች መልስ አለ፡፡

ጥያቄ 1. የሰው ልጅ ለምን ተፈጠረ?
መልስ፡- وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
[ ሱረቱ አል-ዛሪያት - 56 ]
ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡


ጥያቄ 2. ለምን ይህንን አለም ፈጠረ?
መልስ፡
وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ {الذاريات:56
هُوَ الَّذِي خَلَقَ لَكُم مَّا فِي الأَرْضِ جَمِيعاً  {البقرة:29
وَسَخَّرَ لَكُم مَّا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا مِّنْهُ  {الجاثية:13
  الَّذِي جَعَلَ لَكُمُ الأَرْضَ فِرَاشاً وَالسَّمَاء بِنَاء وَأَنزَلَ مِنَ السَّمَاء مَاء فَأَخْرَجَ بِهِ مِنَ الثَّمَرَاتِ رِزْقاً لَّكُمْ  {البقرة:22
وَهُوَ الَّذِي جَعَلَ لَكُمُ النُّجُومَ لِتَهْتَدُواْ بِهَا  {الأنعام:97
"" በአጭሩ…አላህ(ሱ.ወ) በሰማይም በምድርም እንዲሁም በውስጡ ያሉ ነገሮች በሙሉ  መጠቀሚያ(መገልገያ) እንዲሆኑላችሁ ነው የፈጠርኳቸው ይለናል፡፡ ""

الحمد لله على نعمة الاسلام

ዐምማር ዐሊ
4.3K viewsedited  03:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-03 13:59:10
በአንድ እጁ ቁራጭ ብስኩት በሌላኛው እጁ ደግሞ የሽንት መሽኛ ከረጢጥ ተሸክሞ ኩላሊቱን እስኪታጠብ ተራውን እየጠበቀ በሆስፒታሉ ውስጥ ይንከራተታል።
በሆስፒታሎች ውስጥ ሌላ ዓለም አለ ስለ ዱኒያ ፍቅር, ምኞት, ገንዘብ አያወሩም ጤናን ብቻ ይጠይቃሉ.
አምላኬ ሆይ ታካሚን ሁሉ ፈውስ ያረብ!!
.
.
ስላለህ ነገር ሁሌም አመስጋኝ ሁን
ኢላሂ ምህረትህን ጌታዬ በሽታ ላደከመው ሁሉ

http://t.me/IslamisUniverstiy_public_group
http://t.me/IslamisUniverstiy_public_group
5.5K viewsedited  10:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-19 11:12:31
ሰመአት የሆነ ልጇን እንዴት እንደምሸኝ
ያረብ ምን ያህል ወኔ ነዉ ግን?
እናትነት!!!

የፍልስጤም እናቶች ሴቶች ልዩ ናቸዉ


t.me/IslamisUniverstiy_public_group
  t.me/IslamisUniverstiy_public_group
5.3K viewsedited  08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-25 06:37:59
ከድህነቱ የተነሳ ትምህርቱን ሊገፋበት ይቅርና የሚላስ የሚቀመስ እንኳ በቅጡ አጣ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን አቋርጦ ለ24 አመታት ኤርፖርት ውስጥ በጽዳት ሰራተኝነት እያገለገለ ኑሮውን ይገፋ ጀመረ። ትውልደ ናይጄሪያዊ ነው። ሙሐመድ አቡበከር ይሰኛል። በማታ ፈረቃ ትምህርቱ ላይ እየተጋ ቀን ቀን ሽንት ቤት እያፀዳ በመጨረሻም አውሮፕላን አብራሪ ካፒቴን ሆኖ ተመረቀ።

እምነትና ቆራጥነት የጠንካሮች መሳርያ ናት


Join
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
  t.me/IslamisUniverstiy_public_group
1.0K viewsedited  03:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-22 05:45:50 እያለቀስክም ቢሆን የበሩ መከፈት ቢዘገይ እንኳን አትዘን፡፡ ዋናው ሳትሰለች በሩ ላይ ቆመህ መገኘትህ ነው፡፡ በሀይልና በተደጋጋሚ የተንኳኳ በር መከፈቱ ግድ ነው፡፡ እስልምናህን የምትወድ ከሆነ አላህ ይከፍትልሀልና ተስፋ አትቁረጥ፡፡ አላህ ይሰጥሀል፡፡ ውስጥህ ያለውንም ተስፋ ያድሳል፡፡ አል-ፈታሕ ብለህ በስሙ ጥራው፡፡ በርግጠኝነት ይከፍትልሀል፡፡


ነብዩ ሰዐወ በለሊት ተነስቶ ሚስቱንም ቀስቅሶ ሁለት ረከአ ለሰገዱት አላህ ይዘንላቸዉ ብለዋል፡፡
እናም ተኝቶ ድምፃችን ይሰማ እያሉ ከማንኮራፋት ተነስቶ ሚስትህ ጋር መስገድ አብራችሁ ዱአ ማድረግ ለዚህ ቅጥ ላጣ ዘመን መፍትሄ ነዉ፡፡

ዱንያ የደስታ ምንጭ አይደለችም ይሄን ማወቅ አለብን አላህ የትንኝ ክንፍ ለኔ ቦታ የላትም ብሎ እኛ ደስተኛ እንሆናለን ብለን ራሳችንን አናሳምን

አል ኢማም አር ራዚ ቆንጆ ልብስ መልበስ ይወዱ ነበር፡፡ አንድ ቀን ከመስጅድ ወጭ እያሉ አንድ ሙስሊም ያልሆነ ሰው ጋር ተገናኙ፡፡ ሰውዬው የተበጣጠሰ ልብስ ነበር የለበሰው፡፡ ለኢማም አርራዚ እንዲህ አላቸው የናንተ ነብይ ይህች ዓለም ለአማኞች እስር ቤት ለከሐዲዎች ጀነት ናት፡፡› ይላል፡፡ ይህን የመሰለ ፀጋ ውስጥ እያለህ ከየትኛው እስር ቤት ውስጥ ነህ? እኔስ በየትኛው ጀነት ውስጥ ነኝ? አላቸው፡፡ ኢማም እርራዚም እኔ አሁን ያለሁበት ሁኔታ በጀነት ውስጥ ካለው ድሎትና ፀጋ አንፃር እስር ቤት ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) በጀሃነም ውስጥ ለከሐዲያን ካዘጋጀው ቅጣት ደግሞ አንተ አሁን ያለህበት የችግር ኑሮ ጀነት ነው፡፡ አለው፡፡ ሰውዬውም ጥቂት ካስተነተነ በኋላ በርግጥም የናንተ መልእከተኛ የተናገረው እውነት ነው፡፡› አለና ሰለመ፡፡

ይህች ዓለም እስር ቤት መሆኗ፣ አላህ (ሱወ) ጀነትን ለኛ ማዘጋጀቱ፣ አኺራ በላጭና ዘላለማዊ መሆኗ ... ይህ ሁሉ አላህ (ሱ.ወ) እኛን ሊያስደስተን የፈለገ መሆኑ ያመላክተናል፡፡ _ ስለሆነም ጀነት ሊያስገባን ብሎ ይከታተለናል፣ ይጠብቀናል፣ በችግሮችም ይፈትነናል፡፡

በተጨማሪም ሲህርም ባይሆን ማንኛዉም ህመም ሲያጋጥመን ሀኪም ቤት ልሂድ ከማለት መጀመሪያ አላህ እንዲያሽረን እንማፀን

ዑሥማን ኢብን ጦለሐ የሚባል ሰሐባ ነብዩ (ሰዐወ) ዘንድ መጣና የአላህ መልእተኛ ሆይ!!! ሰውነቴ ውስጥ ህመም ይሰማኛል፡፡ አላቸው፡፡ ነብዩም (ሰዐወ)  በአላህ (ሱ.ወ) መካከል ያለው ግንኙነት የጠበቀ እንዲሆን ፈለጉ፡፡ እናም በሚያምህ ቦታ ላይ እጅህን አኑርና ሶስት ጊዜ ቢስሚላህ በል፡፡ ከዚያም ሰባት
ጊዜ አዑዙ ቢላሂ ወቁድረቲሂ ሚን ሸር ማ አጂዱ ወኡሓዚሩ፡፡" በል አሉት፡፡ ሰሐባውም እሳቸው እንዳሉኝ አደረኩኝ፡፡ ህመሙም ለቀቀኝ፡፡ በአላህ እምላለሁ ከዚያ ቀን ጀምሮ ለቤተሰቤና ለማውቀው ሰው ሁሉ ከማስተማር ወደኋላ አላልኩም፡፡› ብሏል፡፡


ታማሚም አስታማሚም አላህ ፅናቱን ጥንካሬዉን ይስጠን...እኛም ለዲናችን ጠቃሚ ለሰዉ የምንተርፍ ያድርገን
ለሰዉ ክፋት መጥፎ የምናስብ ሰዎች እባካችሁ ቶብቱ በሰዉ ደስታ ለምን እንደኛ ይቸገር እንላለን??
ክፉዉን ማዳመጥ ማየት የክፋት መጀመሪያ ነዉ
ክፋት በሰዉ ባህሪ ዉስጥ አብሮ የተፈጠረ ሳይሆን ክፋትን ማስወገድ ባለመቻሉና ዉጫዊ ተፅእኖዉን መቋቋም ስላቃተዉ የመጣበት ነገር ነዉ፡፡
ህይወት ወጪዉን የማትሸፍን ንግድ ነችና በእሷ ስኬትን በሀራም በጠንቋይ በሳሂር እገዛ እጨብጣለሁ ብለህ አትሰብ እናም በሰዉ ስቃይ ሀዘን ለቅሶ መደሰት ምን የሚሉት ህሊና ነዉ ?? አላሁ የስቱርና አላህ ከመጥፎ ባህሪ አመል ይጠብቀን


አላህ ሆይ ከደጋሚዎች ከሳሂሮች ተንኮል ጠብቀን...ምቀኛን ቀናተኛን ከጎናችን አርቅልን..ስቀዉ ከሚጎዱ የቅርብ ሰዎች ጠብቀን ያረብ...
ሲህር የተየደረገብን የታመምን ወይ ሲህር ተደርጎብን ሳናቅ ብዙ አመታት ፈጅቶ ከረፈደ ያወቅን አልሀምዱሊላህ ከረፈደም ማወቃቸዉን ...እንደ አጋጣሚ ያለወቅን ካለ አላህ አሳዉቀን ያረብ
ጠንቋይ ቤት ለሚሄዱትም ሂድያ ስጣቸዉ...

  ኢላሂ  ለዲነል ኢስላም  የምንጠቅም ባንጠቅም እንኳኝ በኛ እንዳይሰደብ የምንሆን ጀሊሉ ያድረገን
አንዳንዴ በማህበራዊ ሚዲያ ሙስሊሞች አለቅጥ ወንጀል ፈሳድ ላይ ተጥለቅልቀዉ የሌላ ሀይማኖት ወይም አንዳንድ ኢስላም ሲደፈር የሚቆጫቸዉ እህት ወንድሞች ሙስሊም አይደለሽ እንዴ ብለዉ ሰመከሩ
የማምለጫ ዘዴ አለች...እኔ ሙስሊም ነኝ ችግር ካለብኝ እኔን እንጂ እስልምናየን አትናገሩ ብለዉ ኮስተር ሲሉ ይታያሉ ይገርመኛል እነሱ ኢስላምን እያሰደቡ እስላምን አትሳደቡ እያሉ ቀጭን ኢስላምን አትንኩብኝ እያሉ የዉሸት ተስፋ ይዘራሉ...ተስፋ ጥሩ ቁርስ ቢሆንም መጥፎ እራት መሆኑን አንዘንጋ 
እናም በሚዲያ ላይ ሙስሊም ሁነን ጅልባብም ጀለብያም ለበስንም አለበስንም በኛ ኢስላም ሊሰደብ ሊመዘን አይገባም እኛ በኢስላም ሀይማኖት ማዕቀፍ ዉስጥ ነን አማኝ ነን ካልን ሙስሊም ተብለናል ...አማኝ ሙስሊም ባንሆን እንኳ ህሊናችን የሚሰራ ሰዉ እንሁን... አረ ሰዉ ሰዉ እንሁን እባካችሁ...ኢስላም በኔም በአንተም በእኛም በእናንተም እየተሰደበ እየተዋረደ ነዉ...አላህ ዲነል ኢስላምን እኔ ነኝ የምጠብቀዉ ስላለ ነዉ እንጂ በእኛ ስራ ቢሆን አፍርሰን ትቢያ አመድ አርገነዉ ነበር
ኢንሻ አላህ እያሉ ከመሾለክ ዝም ብሎ በምሉላስ አሏሁ አክበር እያሉ ሙስሊምን ከመጉዳት ያለችንን ትንሽየ ኢማን አላህ ያድስልን፡፡አላህ ጠንካራ የማይበገር ኢማን ይስጠን

#ዉድ የተከበራችሁ  አንባባዎች በ➊➎ part ስለሲህር ድግምት አይነጥላ ..ስለትዳር ስለስንፈተ ወሲብ በሁሉም ባሉት ቸግሮች ትኩረት አድርጌ አቅሪቢያሁ
የሰዉ ልጅ ነኝ እሳሳታለሁ ከኔ በላይ እዉቀት ያላችሁ እዚህ ቦታ ተሳስተሀል በሉኝ  edit ማድረግ እችላለሁ edit አሁኑ ላድርግ ከወር ቡሀላ edit ማድረግ ስለማይቻል ...ብዙ ሰዉ እያነበበዉ ሼር እያደረገዉ ስለሆነ ...ግን የተዘጋጀዉ ከመፅሀፍ እና ከሀዲስ ከሚያቁ ጠይቄ ስለሆነ እስከ አሁን በአስተያየት መስጫ አስተካክል የተባልኩት የለኝም፡፡ በአስተያየት ስሰጡ ሳነባቸዉ  በሲህር ተለክፈዉ የነበሩ እና በይፋ  ያደረገባቸዉ ሰዉ እየነገረን ነዉ ያሉኝ አሉ  ፡፡
ወደ 5 የሚሆኑ አስተያየቶች እኔን ካላገባሽ መቼም አታገቢ ብለዉ ከወንድየዉ ተነግሯቸዉ  እንዳላገቡ በተጨማሪ  አንዷ አግብታ ኒካሁ ታስሮ ሳይቆዩ እንደተፋታች የነገረችኝ አለች ...ሌሎቹ ይሄን ፁሁፍ ሲያነቡ ራሳቸዉን ፈትሸዉ ሩቃ ሊጀምሩ እንደሆነ አሳዉቀዉኛል...እናም በተለይ በትዳር ላይ የተተበተበ ጉድ ከባድ ነዉ ራሳችንን ማኔጅ ብናደርግ ጥሩ ነዉ

ለ15 ቀን በ15 ክፍል የቀረበዉን ፁሁፍ ሀምሌ 1 ጀምረን ሀምሌ 15 2015 ጨርሰናል ፡፡ባለመሰልቸት ባለመታከት አንብባችሁ ስለጨረሳችሁ ጀዛችሁን አላህ ይክፈላችሁ ለምን እኔም እናንተ ባነበባችሁበት ራሳችሁን በፈተሻችሁበት አጅር ስለማገኝ እናንተም ባነበበባችሁት እኔም ባዘጋጀሁት ተጠቃሚ ያድርገን፡፡

ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሁ ወበረካትሁ
  #ተ.......... #ፈ.......... #ፀ........... #መ

አንብባችሁ ምን ተረዳችሁ?
ምን አስተያየት አላችሁ?
እዚህ ላይ ይፃፉ
T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot
ከፁሀፉ ያልገባችሁ ያልተዋጠላችሁ ካለ
2.1K views02:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-22 05:39:46 ጧኢፍ ነዋሪዎቿን በነቂስ አውጥታ የስድብ እና የድንጋይ ናዳ እንዲወርድበት ፈቀደች። ምድር ከሰውነቱ የሚፈሰውን ደም መጠጠች።
በመርዝ የተለወሰ ምግብ ሲሱጠት፣ ከሚናፍቅው የትውልድ ቀዬ ሲባረር ይቅር ባይነት የዘወትር ስንቁ ነበር። ስቃይ በተሸከመው አካልና መንፈሱ ታግዞ እግሮቹ አስከሚያብጡ ድረስ ለሊቱን በመቆም አመስጋኝ ባሪያ ለመሆን ከአምላኩ ጋር ያወጋል ሰዎችን ይቅር ይሉ ነበር ሀቢቡና ሙሀመድ ሰዐወ 
እናም ፈተና  መብዛት ችግር መደራረብ ባይኖር ዱንያ የደስታ ሀገር ብትሆን ሀቢቡና ሙሀመድ ሰዐወ ባልተፈተኑ ነበር እናም አንተም አንቺም እሱም እሷም እናንተም ፈተና ላይ ናቸሁ ፈተና ጨርሳችሁ ትንሽ ከተደሰታችሁ ቡሀላ ሌላ የከበደ ፈተና እንደሚጠብቀን እርግጠኛ ሁን የዛን ጊዜ ነዉ ኢማንህ የሚለካዉ፡፡
ኢማናችን መለካት እንጂ መነካት የለብንም ወገን


እጅግ አምልኮ በማብዛት የሚታወቀው ታላቁ ታቢዒይ አልፉደይል ኢብኑ ዒያድ ረሒመሁላህ ፈገግታ አያበዙም ነበር፡፡ በአንድ ወቅት ግን ልጅ ሲሞትባቸው ፈገግ አሉ፡፡ ለምን ፈገግ እንዳሉ በተጠየቁ ጊዜ “አላህ የወደደው ነገር ነውና እኔም ወድጄ ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) የወደደውን እንድትወድ ነፍሴ ፈገግ እንድትል አስገደድኳት” አሉ፡፡

ዑለማዎች ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ያለቀሱበትንና አልፉደይል ግን ፈገግ ያሉበትን ሁኔታ በማንሳት ለመተንተን ሞክረዋል፡፡ በመታገስ ደረጃ አፉደይል ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ይበልጣሉ ማለት ፈጽሞ የማይታሰብ ነገር ነው፡፡ ነገር ግን ትርጉሙም፡- ሞት በሚመጣበት ቅፅበት ቀልብን በሁለት ሰሜት ውስጥ ይከታል፡፡ እዝነትና ውዴታ፡፡ ማንም ሰው ሁለቱን ስሜቶች በአንድ ጊዜ ማስተናገድ አይችልም፡፡ አልፉደይል ሁለቱን ማሳካት አልቻሉምና በውዴታ ስሜት አንድም ፈገግ ማለት አለባቸው አሊያም አብዝተው ማልቀስ ነበረባቸው፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ግን ሁለቱን ማሳካት ችለዋል፡፡ አላህ የወደደውን ወደዋል በሌላ በኩል ደግሞ አልቅሰው እዝነት ስሜት አሳይተዋል

የነቢያችን አክስት የሆነችው : እመት ሶፊያ በኡሑድ ጦርነት ወቅት ቁስለኞችን ውሃ ታጠጣ ነበር፡፡ ታላቁ ጀግና ሐምዛ (ረ.ዐ) ተገደሉና አካላቸውም እንዲቆራረጥ ሆዳቸው እንዲቀደድ ተደረገ፡፡ ሒንድ በበቀል ስሜት ጉበታቸውን እስከማኘክ ደረሰች። ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ለልጇ ዙበይር ኢብኑ አልዐዋም ዝበይር ሆይ! ሶፊያን ወደ መዲና ይዘሀት ሂድ ሐምዛን ማየት የለባትም፡፡” አሉት። ልጇም ሄደና “እናቴ ሆይ! ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ መዲና ተመለሽ ብለውሻል፡፡” አላት፡፡

ልጄ ሆይ! ይህን የምታደርጉት ሐምዛን እንዳላይ ብላችሁ ነው አይደል? አለችው፡፡
....“አዎን” አላት፡፡
....እሷም “ልጄ ሆይ! አላህ ከዋለልን ፀጋ አንፃር በሐምዛ ላይ የደረሰው በጣም ቀላል ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) በሐምዛ የፈተነን ሥራውን መውደድ አለመውደዳችንን ለማየት ነው፡፡ ወደ አላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሂድና የአላህ መልዕክተኛ ሆይ አላህ በሐምዛ የፈተነን ሥራውን መውደዳችንን ለመፈተን ነው ብላለች ሶፊያ በላቸው ፡፡ ልጁም ወደ ነብዩ (ሲዐወ) በመመለስ ነገራቸው፡፡
... ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) “እንግዲያውስ ማየት ትችላለች፡፡” አሉ፡፡ ሄደችና አይታው አለቀሰች፡፡ ኢንና ሊላህ ወኢንና ኢለይሂ ራጂኡን የኛዑን እኛ የአላህ ነን ወደ አላህም ተመላሾች ነን፡ በማለትም ዱዓእ አደረገችለት፡፡
እናም አላህ በሚያመጣብን ፈተና የዱንያም ሆነ የጂን የሲህርም አላህ ወዶን እየፈተነን እንደሆነ አንዘንጋ

ጅን ሲህር ሳሂር ደጋሚ ጠንቋይ ደብተራ እንደማይጎዳ አሏህ ብቻ ጎጂ እንደሆነ ማወቅን ከኢማኖች ውስጥ ጠንካራ ኢማን ሁኖ እናገኘዋለን!! በአሏህ ላይ የቂን እጅግ የምንፈልገው መሳርያ ነው!! ሌቦች ቤትን ሊዘርፉ ሲመጡ አለሁ ብሎ ድምፅን ማሰማት ሲቀጥልም የመሳርያን ድምፅ ማሰማት እነርሱን እንደሚያስበረግጋቸው ሁሉ የቂን ልክ እንደዛው ጅኖችን ያስፈራቸዋል እንዳይቀርቡን!! ይሁንና ያለ እውቀት ያለ መጠበቅያ የቁርአን አያዎች እና ዚክሮቸች ማለት ያለ መሳርያ መሳርያ ታጥቀው የመጡ ሌቦችን ማስፈራራት ብቻ ነው፡፡ ለኛ መሳርያችን ለጅኖች ሊያውም ከባለጌዎች ለመጠበቅ የምንታጠቀው መሳርያ ዚክርና ቁርአን እንዲሁም ዱአእ ነው፡፡ ሌላውን አይነት የመሀይማን መሳርያ የሆነውን ጥንቆላ መተት ፀበል እና አንጃ ግራንጃዎች ልክ ሌቦችን እንደመማፀን እንደመደራደር ነው የምንቆጥረው፡፡ ከሌባ ጋር ድርድር የለም ባንተ ንብረት ላይ መጥቷልና ፡፡ ከጅን ጋርም እያጠቃህ መደራደር የለም በቁርአን በዚክር ልኩን አሳይተሀው  መከባበር እንጂ፡፡


እናም ፈጣሪ ይሁን ብሎ ተፅፎብን ከሆነ ትዕግስት ጥንካሬ ፅናት ያስፈልጋል፡፡ በሲህር በጂን የሚፈተን ሰዉ በዛዉም የፀና የጠነከረ አላህ ወዶን ይሆናል ዱአ ላይ መበርታት ግዴታ ነዉ...ከዱአ በጭራሽ ተስፋ ልንቆርጥ አይገባም
{ وَإِذَا سَأَلَكَ عِبَادِی عَنِّی فَإِنِّی قَرِیبٌۖ أُجِیبُ دَعۡوَةَ ٱلدَّاعِ إِذَا دَعَانِۖ فَلۡیَسۡتَجِیبُوا۟ لِی وَلۡیُؤۡمِنُوا۟ بِی لَعَلَّهُمۡ یَرۡشُدُونَ }
ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ ጊዜ (እንዲህ በላቸው)፡- እኔ ቅርብ ነኝ፡፡ የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ፡፡ ስለዚህ ለኔ ይታዘዙ፤ በኔም ይመኑ፤ እነሱ ሊመሩ ይከጀላልና፡፡[አል በቀራህ: 186]


  አንድ ድንቅ የሆነ ሐዲስ አልቁድስይ ላካፍላችሁ፡፡ ነቢዩ ባስተላለፉት ሐዲስ አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡- “የአደም ልጅ ሆይ! እኔም እፈልጋለሁ አንተም ትፈልጋለህ፡፡ እኔ ለምፈልገው ነገር እጅ የሰጠህ እንደሆነ የምትፈልገውን አመጣልሃለሁ እኔ ለምፈልገው ነገር እጅ የማትሰጥ ከሆነ በምትፈልገው ነገር ላይ  እንድትደከም አደርግሃለሁ፡፡ በመጨረሻ እኔ የምፈልገው ነገር ብቻ እንጂ የሚሆን የለም፡፡” ይለናል፡፡ አላህ (ሱ.ወ) በተከበረ ቃሉ “አላህ ካሻ በስተቀር አናንተ አትሹም (አል-ኢንሳን ፡3) ብሏል፡፡

ኢብኑ ዑመር (ረ.ዐ) ዱዓዬ መቼ ተቀባይነት እንደሚያገኝ አውቃለሁ፡፡ አሉ፡፡ “እንዴት ልታውቅ ትችላለህ? ተባሉ፡፡፡ “ቀልቤ በጥልቀት የአላህ ፍራቻ ካደረበት፣ መላ አካላቴ ከተንቀጠቀጠ፣ ዐይኔ ካነባች፣ ይህች ሰዓት ዱዓዬ ምላሽ የሚያገኝበት ነው፡፡ በማለት በዱዓዬ እጠናከራለሁ፡፡ ብለዋል፡፡

ለዱአ መቸኮል አያስፈልግም
ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) “እስካልቸኮላችሁ ድረስ ምላሽ ይሰጣችኋል፡፡” አሉ፡፡ መቸኮል ሲባል እንዴት ነው? ሲሏቸው አንዳችሁ “ዱዓእ አደረግኩ፤ ዱዓእ አደረግኩ ምላሽ አላገኘሁም፡፡ ይላል፡፡ (ተስፋ መቁረጥ) ዱዓእ ይተውን ይተዉና በዚያው ምላሽ ያጣል፡፡” ብለዋል፡፡
ሲህር ከተደረገብን ወደ አላህ የማይቋረጥ ቀጣይ የሆነ ዱአ ያስፈልጋል፡፡

ኢብኑ አልቀይም ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡ ብትባረርም እንኳን ከአላህ በር ላይ ከመቆም ተስፋ አትቁረጥ፡፡ ቢመልስህም እንኳን ምክንያት ከማቅረብ አትውረድ፡፡ በሩ ተቀባይነትን ላገኙት የተከፈተ እንደሆነ ቀስ ብለህ በስርአቱ ግባ፡፡ ድሀ ነኝ ምፅዋት እፈልጋለሁ፡፡ በለው፡፡ ምፅዋት የሚሰጠው ለድሆችና ለችግረኞች ነው፡፡ እኔም ምስኪን ደሃ ነኝ፡፡ በለው፡፡
1.6K viewsedited  02:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-22 05:37:39 #ሲህር_ጂን_አይነጥላን_ራስን_በራስ_ማከም
                  አሚር ሰይድ


            
#የመጨረሻዉ_ክፍል



   #ራስን_በራስ_ማከም_ከዛም_ለሌላ_መትረፍ



ከpart ➊➍ ቀጥታ የቀጠለ.....
  ከዛር ዉጭ ያለን ሩቃን ለማድረግ ባንፈራ ጥሩ ነዉ ብቻ መጀመሪያ አላህን ይዘን ነይተን ሀስበነሏህ ብለህ መጀመር  ነዉ ፡፡


ከተሞክሮ እስኪ ጀባ ልበላችሁ ወላሂ ይሄን የምነግራችሁ ጀሊሉ ያቅብኛል ለጉራ አይደለም ባልፅፈዉ ደስ ይለኛል ግን እንድትደፍሩ እንዳትፈሩ ለመጠቆም ነዉ፡፡ እኔ የዲን እዉቀት የለኝም በማንበብ እና የሰሙትን በመተግበር ላይ አተከለራለሁ ...እና ማንኛዉም ነገር አንድ እርምጃ ያስፈልገዋል የብዙ ሰዉ ችግር ሶስት አራት እርምጃ ይራመዳል ሳያጣራ ከዛ ግብ ሳይመታ ይመለሳል ...እኔ የማምነዉ አንድ እርምጃ ካልሆነ ወደፊት ሳይሄዱ መለስ እርምጃዉ የተሳካ ከሆነ ቀኝን እግርህን ካስቀደሙ ግራህን አስተከትለህ ሁለት እርምጃ ላይ ትቆማለህ ከዛ ነገሮችን እያገናዘቡ መሄድ ነዉ...
#ከተሞክሮ

አንዲት ክርስቲያን ጎረቤታችን  የ7 አመት ልጇ አላት ለሊት አይተኛ ቀን ታዝሎ ይዉላል ስራዉ ማልቀስ ምግብ የሚበላዉ ትንሽ ለዛዉም ያስመልሰዋል እንደ እድሜ እኩየቹ አይጫወትም ብቸኛ ነዉ ... ይሄ ህመም የጀመረዉ ገና በ4 አመቱ ነዉ 3 አመት ያህል ተሰቃይቷል  ያልሄደችበት ፀበል የለም ሌላም ሀገር ሂዳለች ፡፡በፀበል መፍትሄ ሲያጡ ሌላ ሀገር ጠንቋይ ቤት ሄዱ አረንጓዴ እስስት አምጡ ብሏቸዉ አረንጓዴ እስስት ለማግኘት አራት ወር ፈጀ በግድ ተገኘ ጠንቋዩ በአረንጓዴ እስስት ሌላም  ጨምሮ አንገት ላይ የሚንጠለጠል ሰጠው ምንም ለዉጥ የለም...ከ3አመት ስቃይ ቡሀላ ሲጨንቃት ቁርአን ቅሩልኝ አለች...

#አላህ_ሆይ እንዳታስፍረኝ የቁርአንን ሀይልን ለነዚህ ክርስቲያኖች አሳያቸዉ ብየ ዱአ አደረኩ ...ከዛማ በስፒከር ሩቃ ከፈትኩ ሁለት ሁነን በቻልነዉ ቀራን ወላሂ 45 ደቂቃ ባልሞላ እንቅልፍ ወስዶት ላብ በላብ ሆነ ቁርአኑን ስንጨርስ ጩኾ ተነሳ በዛዉ ለቀቀዉ ከዛ ቀን ቡሀላ ታሞ አያቅም ይሄዉ እንቅልፍም ይወስደዋል እናቱም አታዝለዉ ምግብም መመገብ ጀመረ የሚያስመልሰዉ ቀረለት  ትምህርትም ተመዘገበ አልሀምዱሊላህ....እናት አባቱ አጥባቂ ክርስቲያን ነበሩ አሁን ግን ከምነግራችሁ በላይ ለሙስሊም ያለቸዉ አመለካከት ደስ የሚል ነዉ አላህ ሂድያ ይስጣቸዉ የቁርአንን ሀይል ቤተሰብ ዘመድ ልጁን ተሽሎ ሲያዩት ይገርማቸዉ ይደንቃቸዉ ይዟል፡፡

አክስቴ ክርስቲያን ነች ታማ ፀበል ብትመላለስ ምን ብትል ያልተሻላትን በ30 ደቂቃ ሩቃ በመቅራት በአላህ ፍቃድ እንዲሻላት አድርጊያለሁ

ከነዚህ ዉጭ  3 ሰዎች ጎረቤት ምናምን ሲታመሙ በአላህ እገዛ ተሳክቶሎኛል እናም እንደዚህ ልላችሁ ያሰብኩት ሩቃ ማድረግ ከባድ አይደለም መጀመሪያ ጀሊሉን አላህየን ከያዙ ምንም የሚያስቸግር የለም እናም እህት ወንድምህን እናት አባትህን ...እናት አባትሽን እህት ወንድምሽን ለሌላ ባዳ አሳልፋችሁ አትስጡ

----- ጂን ሲናገር  ሊዋሽም ላይዋሽም ስለሚቾል አንዳንዴ ሲናገር እዉነት ነዉ ብለን ከተናገረዉ ሰዉ ጋር ሂደን መጣላት አያስፈልግም፡፡

ከዚህ ርዕሱ ጋር ባይሄድም በፊት ክፍል ላይ ዘንግቼ ሳላስገባ የቀሁት ጉዳይ አሁን ያለቦታዉም ቢሆን ስለዚህ ጉዳይ ትንሽ ልበል...
በቅርብ አመታት በተለያየ ማህበራዊ ሚዲያ ወንድና ሴት ዚና ሲሰሩ ወይ በባል ወይ በሚስቱ ላይ ሲማግጥ  ተጣብቀዉ እያየን ነዉ፡፡ ይሄ ባልየዉ ሚስቱን ካላመናት ወይም ሚስት ባሏን ካላመነችዉ ጠንቋዮች ጋር ሂደዉ ሌላ ወንድ ጋር ከተኛች ወይም ሌላ ሴት ጋር ከተኛ እዛዉ እንዲጣበቅ ሰዉ እንዲያዋርደዉ ይሁን ብለዉ አስደግመዉ ሊሆን እንደሚችል አንዘንጋ...ካልሆነም ደግሞ ፈጣሪ እኛን ለማስተማር እነሱን ምሳሌም እያረገ ሊሆን ይችላል፡፡እናም ለትዳራቸዉ ታማኝ ያልሆኑ ሰዎች መጀመሪያ  ባለመተማመን ይጋባሉ ከዛ ይሄ ይፈጠራል፡፡
እናም ወይ የአላህ ቁጣ ነዉ ካልሆነ ድግምት ነዉ ...
ግን በተለይ በትዳር ላይ የሚሰሩ ሲህሮች በአሁን ዘመን ላይ በሰፊዉ ተንሰራፍቷል፡፡


  #በጂን_የተያዘ_ወይም_ሲህር_ወይ #በአይነጥላ_የተያዘ_ሰዉ_ወይም_አስታማሚዉ      
         
#ምን_ማድረግ_አለበት

      ኩን ፈየኩን ...አላህ ኩን ብሎት አላህ ሱወ በሲህር በጂን በአይነጥላ ሊፈትነን ይችላል ፡፡  ዱንያ የፈተና አለም ነች ለአላህ የትንኝ ክንፍ ያህል ቦታ የላትም ላለን ዱንያ ደስታን እናጣጥማለን ማለት አይደለም፡፡  ዱንያ በሀዘን ማቅ የተተበተበች ደስታ እንደመብረቅ ብልጭ ብሎ የሚጠፋበት የኑሮ መድረክ የፈተና መሸጋገሪያ ድልድይ ነች የጀነት መግቢያ የኸይር መሸመቻ የፈተና ማለፊያና መዉደቂያ የቁጥጥር ጣቢያ ነች፡፡  

  በርዚቃችን ትዳር እንዳናገባ ነገሮች እንዳይሳኩ ወዘተ ሲህር ድግምት  ከተደረገብን የአላህ ዉሳኔ ነዉ ፅናት ብርታት ጥንካሬ ያስፈልጋል ፡፡

አላህ (ሱ.ወ) የወሰነውን ነገር መደው የተቀበሉ  ነብዩ ሰዐወ ናቸዉ በሲህር ተሰቃይተዋል.....በተጨማሪ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ኢብራሂም የሚባል ልጅ በተወለደላቸው ጊዜ ከፍተኛ የሆነ የደስታ ስሜት ውስጥ ገብተው ነበር፡፡ ተሸክመውት ወደተለያዩ ሰሐቦች ቤት ይዘውት ይሄዳሉ፡፡ ለሰዎችም ልጇን ኢብራሂምን ተመልከቱት፡፡› ይሉ ነበር፡፡ ትንሹ ኢብራሂም አባት ለልጅ በእጅጉ በሚጓጓበት የህፃንነት ዕድሜ ጡት መጣያው አካባቢ ሞተ፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) አለቀሱ ፡፡ እንባ የልብ እዝነት ውጤት ነውና የአላህን ውሳኔ ካለመውደድ አይቆጠርም፡፡ እርሳቸውም ዐይን ያለቅሳል፣ ቀልብ ያዝናል፣ ጌታችን የሚወደውን ነገር እንጂ አንልም፡፡

#ኢብራሂም_ሆይ!!!! ከኛ በመለየትህ አዝነናል፡፡” አሉ፡፡ ከዚያም ወደቤታችው በመግባት ለአላህ (ሱወ) እንዲህ አሉ፡- ‹‹ጥሪህ ሰምተን በደስታ ወዳንተ መጣን፡፡ መልካም ነገር ሁሉ በእጅህ ነው፡፡ መጥፎ ካንተ አይደለም፡፡” ብለዉ የጌታቸዉን ዉሳኔ ተቀበሉ...

መቼም የሀቢቡና ሙሀመድ ሰዐወ ታሪክ ታቃላችሁ
በእናታቸዉ ሆድ ውስጥ ሳለ ወላጅ አባቱን በሞት ተነጠቁ
ዕድሜያቸዉ ስድስት ሲሞላ ወላጅ እናታቸዉን ቀበሩ።
በስምንት ዓመታቸዉ በፍቅር ተንከባክበው ያሳደጓቸዉ አያቱን አይቀሬው ሞት ነጠቀው።

እንደ አይን ብሌናቸው የሚሳሱለት በማራኪ ስብዕናው ተረታ የትዳር አጋሩ ለመሆን የበቃችው ውድ ሚስቱ በአንድ ዓመት ውስጥ ተከታትለው ተለዩት።
  ከሁለት ዓመታት ዕድሜ በላይ ያልቆዩ ሁለት ወንድ ልጆቹን ሞት ቀጠፋቸው። በህፃናቱ ፈገግታ ደምቆ የነበረው ቤት የሀዘን ጥላ አጠላበት።
ከእርሱ ህልፈት በኋላ በስድስተኛው ወር በሞት ከተከተለችው ተናፋቂ ልጁ በስተቀር ሁሉም ሴቶች ልጆቹ ወደ መጪው ዓለም ተጓዙ።

የአባቱ ጥሪት የነበሩት አጎቱ ተገደሉ። መገደል ብቻ አይደለም የሰው ልጅ ያደርገዋል ተብሎ የማይታሰብ ጭራቃዊ ተግባር በአካላቸው ላይ ተፈፀመ። ሂንድ አስክሬኑን አስቀድዳ ጉበቱን በላችው።
1.4K viewsedited  02:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-21 21:14:26
የምታመንህ ነኝ
1.6K views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-21 07:19:28
ዛሬ ጁምአ ነዉ የሆነ ችግር ሲበዛ ወይ ነይተን ለሰዉ ነግረን ያልተሳካ ካለ እንደዚህ ልጅ ሁኔታ ለጀሊሉ ነግረዉን ያሳፍረን ይሆን??
እስኪ ለጀሊሉ እንደዚህ ልጅ ሁኔታ አድርገን እንገረዉ
Join
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
  t.me/IslamisUniverstiy_public_group
1.9K viewsedited  04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ