Get Mystery Box with random crypto!

ISLAMIC SCHOOL

የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_and_science — ISLAMIC SCHOOL I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_and_science — ISLAMIC SCHOOL
የሰርጥ አድራሻ: @islam_and_science
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 15.55K
የሰርጥ መግለጫ

✍ ጅልከሆንክ ጅል ተከታይ ጀንትል ከሆንክ አስከታይ ትሆናለህ..!
ጅልም ጀንትልም ካልሆንክ ደግሞ አርፈህ በራስህ ዓለም ትኖራለህ..! አንባቢ እንሁን፡፡ለውጥ ከራስ ቢጀመር ...የቸገረን ጥሩ መካሪ ሳይሆን፤
የሰማነውን መተግበር ነው ያቃተን!ጅህልና በሽታ ነዉ፡፡
🎖For any comment T.me/Aisuu_bot
💠Another channal
@IslamisUniverstiy_public_group

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2022-08-27 08:40:02   #የመራም_ማስታወሻ
           ክፍል ~ ➊➎
ፀሀፊ ☞አሚር ሰይድ


" መሪ ሶስት ቀን ያህል ለመቆየት አዲስ አበባ መሄዴ አይቀርም እዛ ትንሽ እኔን የሚፈልግ ስራ አለ እሱን አስተካክየ በቻልኩት ፍጥነት እመለሳለሁ!" ሲለኝ በጣም ደነገጥኩ
... "እና ትተህን ልትሄድ ነዉ ?! አዩብ አይናፍቅህም ይወድሀልኮ!" አልኩት፡፡ አዩን ምክንያት አረኩ እንጅ እኔ ራሱ ገና ሳይሄድ ልሄድ ነው ሲል ነው የናፈቀኝ
......"በጣም ነው እንጂ የሚናፍቀኝ ሁላችሁም ትናፍቁኛላችሁ መሪ ደግሞ ካልሰለቸሁሽ በየሰአቱ ነው የምደውልልሽ" አለኝ
..... "አትሰለቸኝም ደውልልኝ!? አልኩት በደስታ ከተናገርኩ በኃላ ግን መውደዴን ያወቀብኝ መሰለኝ እና አፈርኩ፡፡ ቤት እንደደረስን አዩ ገና እንዳየው ሩጦ ተጠመጠመበት
"አየሀው ከእኔ አንተን አስበለጠ" አልኩት ተገርሜ፡፡
...."እና እየቀናሽ ነው እንዴ!?" ብሎ ሳቀብኝ ገና ከመቀመጣችን ለሪም እና ለማማየ "አብደልከሪም ሊሄድ ነው!" አልኳቸው በደከመ ድምፅ ሁለቱም እኩል "የት ነው የሚሄደው!!?" አሉ ደንግጠዋል፡፡ እማማየ ወደሱ ዞረው "ወዴት ነው የምትሄደው ልጄ!?" አሉት በጣም ስለተላመድን አዲስ አበባ መኖሪያው መሆኑን ረስተነው እንጅ እንደ እውነቱ እማ አንድ ቀን ወደ መኖሪያው እንደሚመለስ ብናውቅም ተላምዶ መለየት ከበደን "ለ3 ቀን ብቻ ነው እንጅ እመለሳለሁ!" አለ በርግጥ እሱም መለየት ከብዶታል፡፡


አዩ መሄዱን ሲሰማ "እኔን ትተከኝ ልትሄድ ነው!?" አለው በአይኑ እየተለማመጠ
..... " እመለሳለሁኮ አዩ ከዛ የትም ሳልሄድ አብረን እንሆናለን እሺ" አለው፡፡ ጉንጮቹን በእጁ ይዞ ወደ ደረቱ እያስጠጋ፡፡ ሪም ምንም ሳትል ደንግጣ ወሬውን ታዳምጣለች፡፡ እማማየ በቃ ነገ መንገደኛ ከሆንክ መቼም ሰው አይሸኝም ይቀበሉታል እንጅ "ሪም ምግብ ስሪ ቡናም ይፈላል" አሉ፡፡ ሪም ተነሳች እኔም አብሪያት ተነሳሁ ምግብ ሰራን ቡና ከተጠጣ በኃላ ከፋኝ.. ለካ አብደልከሪም ይሄዳል ግን እስካሁን አዩብ አለቀቀውም እንደተቃቀፉ ናቸው፡፡

ሰአቱ እየመሸ ነው አዩብ ያለወትሮው እንቅልፍ ከሱ ርቆ ንቅት ብሏል አትሄድም ብሎ የሙጥኝ ብሏል፡፡ "ይሄ ልጅ ዛሬ አለቀቀህም ልጄ ነገ መንገደኛ ነህ ናቶሎ እዚህ ጎንህን አሳርፍ" ብለው መኝታቸውን ለቀው እኛ ጋር መተው ተኙ፡፡ "አዩብ እና አብደልከሪም ተቃቅፈው ተኝተዋል፡፡ እኔ ግን እንቅልፍ ባይኔ ሳይዞር ነጋ፡፡ ቁርስ ከበላን በኃላ አብዲ ተሰናብቶን ወጣ፡፡ ቤቱ በሀዘን ተሞላ እርስ በእርሳችን ተኮራርፈን ቁጭ አልን፡፡ እኔ በጣም ደብሮኛል ቤቱ ሁሉ አስጠላኝ! ቶሎ ወደ ስራ ሂጄ ራሴን ቢዚ ማድረግ ፈለኩ፡፡


አብደልከሪም ከሄደ ዛሬ ሁለተኛ ቀኑ ነው፡፡ እየተደዋዉልን ስለሆነ ነገ እንደሚመጣ ነግሮኛል፡፡ የዛሬው ቀን ረዝሞብኛል ዛሬ አልፎ ቶሎ ነገ እስኪደርስ በጣም ቸኩያለሁ፡፡ በደስታና በንቃት ስራየን እየሰራሁ ነው፡፡ ከስራ ወደ ቤት ስሄድ ሪም ለነገ አቀባበል ዛሬ ሽርጉድ እያለች ነበር፡፡ ምን እሷ ብቻ አዩ ከሷ ብሷል እንጅ በደስታ እየዘለለ ይቦርቃል ለተመለከተን ሰው ሁለት ቀን የተለየን ሳይሆን ለብዙ አመታት የተለየንን ሰው የምንጠብቅ እንመስላለን፡፡

ነገን በመናፈቅ ደስ በሚል ተስፋ ደስ የሚል መኝታ ደስ የሚል ንጋት! ዛሬ አብደልከሪም ይመጣል! እኔ ወደስራ መሄድ አለብኝ፡፡ አብዲ ቀድሞ እኔ ጋር ስራ ቦታ እንደሚመጣ ነግሮኛል፡፡

እኔም እሱን በማግኘት ተስፋ ስራየን ተያይዣለሁ ደቂቃ በሰአታት እየቀፈራረቁ ሰአታትን አስቆጥረው እኩለ ቀን ደረስን ከ6-7 ባሉት ሰአት በጣም የስራ ውጥረት ይኖራል፡፡ 7 አልፎ 8 ሰአት ደረሰ አሁን ስራ ውጥረት ቀነሰ ከስራ ለመውጣት አብዲን እየተጠባበኩ ባለበት ሰአት------- አንዲት ሴት ሁለት ህፃናት ልጆችን ይዛ ወደ ካፌው ገባች አለባበሷ ቅጡ የጠፋው ከእድሜዋ ጋር የማይሄድ ሙስሊም ትሁን ካፊር ግራ የምታጋባ ግን ደግሞ በየወሬዋ መሀል ወላሂ እያለች መሀላ የምታበዛ ነች :ጫት እየቃመች አፏ የጌሾ ሙቀጫ መስሏል ከ3 ወይም 4 አመት የማያልፈው ወንድ ልጅ እና በወራት እድሜ ያለች ልጅ ይዛለች፡፡ ወንበር ይዘው ተቀመጡ የስራ ሰአቴ ስላለቀ ካሽሪዋ ጎን ቁጭ ብየ አብዲን እየጠበኩ ነው፡፡

ልጇ የተቀመጠበት ወንበር ከእኔ ፊት ለፊት ነበር፡፡ የልጁን መልክ ሳይ ልቤ ቀጥ ብላ የቆመች መሰለኝ ደነገጥኩ ከተቀመጥኩበት ተነሳሁ ሰውነቴ ተንቀጠቀጠ ሁሉ ነገሩ የሞተውን ወንድሜ ፈይሰልን ይመስላል፡፡ "ፈይሲ" አልኩኝ ለራሴ በሚሰማ ድምፅ በእጀ ምልክት ሰጥሁት ና አልኩት ተነስቶ ወደኔ መጣ ምንም ሳልለው ተንበርክኬ አቀፍኩት ደጋግሜ ሳምኩት በደከመ ድምፅ "ስምህ ማነው?" አልኩት
......."ፈይሰል" አለኝ በሚጣፍጥ አንደበት ድንጋጤ ይበልጥ ጨመረ ስሙም የሞተዉ ወንድሜ አይነት ፈይሰል ጋር አንድ ሆነብኝ እሱን እያስታወስኩ እንባየ ያለገደብ መፍሰስ ጀመረ እጄ መንቀጥቀጥ ጀመረ... የመተዉ ወንድሜ ጋር በጣም ይመሳሰላል "አባትህ ማነው ስሙ?" አልኩት "
.....አባቴ እዛ ነው ምሳ በልቸ እናቴጋ እንሄዳለን" አለኝ፡፡
........ "ምሳ እስካሁን አልበላህም!?" አልኩት አንጀቴ በሀዘን እየተላወሰ ቅንጭላቱን በመነቅነቅ አወንታውን ገለፀልኝ፡፡ ጭምቅ አድርጌ አቀፍኩት እና ደግሜ የአባቱን ስም እንዲነግረኝ ጠየኩት "አባቴ ስሙ አባቢ ነው" አለኝ፡፡ " እሽ ህፃኗ ስሟ ማነው አልኩት
....." እህቴኮ ናት " አለኝ፡፡ "
.....እኮ ስሟን ንገረኝ ??አልኩት
..... እናቴ ሩማን ናት ብላለች አባቴ ደግሞ ለይላ ናት ብሏል ስም የላትም" አለኝ እየሳቀ

ነገሮች ሁሉ ተዘበራረቁብኝ በድንጋጤ ደርቄ ቀረሁ እና ከተደረደሩት ኬኮች ውስጥ እያስመረጥኩት
....."ቤታችሁ የት ነው?" አልኩት በእጁ ምልክት እየሰጠኝ "እዛ ነው" አለኝ፡፡ የምፈልገውን መረጃ ከሱ ማግኘት አልቻልኩም እና አቅፌ ወደ እናቱ ወሰድኩትና ከእሷ መረጃ ለማግኘት በዘዴ ቀረብኳት፡፡
....."ሰላም እንዴት ነሽ ማሻአላህ ደስ የሚል ልጅ አለሽ" አልኳት ለመግባባት ያህል ...ግን የእሷ መልሷ አስደነገጠኝ " ......ካማረሽ ወስደሽ አሳድጊው ሰጠሁሽ ልጁን አልፈልገውም" አለችኝና ወደ ልጁ ዞራ "አንተ ደደብ ደንቆሮ አርፈህ ቁጭ በል ብየህ አትሰማም አይደል ምናለ በሞትክና በተገላገልኩህ" ብላ በጥፊ ላሰችው፡፡ በቆምኩበት ደርቄ ቀረሁ እናት ስለመሆኗ ተጠራጠርኩ እማ በቅፅበት በህሊናየ ውል አለችብኝ
....." ለምን ትመችዋለሽ ??ልጅ እኮ ነው ደግሞ ምንም አላጠፋም አንችም እንደ እናት ከአጠገብሽ ሲርቅ አስበሽ የት ሄደ ብለሽ አልፈለግሽውም" አልኳት በንዴት

ልጁ ጉንጩን በእጁ ይዞ እንባው ይረግፋል፡፡ አሳዘነኝ የገዛሁለትን ኬክ አስቀምጨ እንባውን ጠረኩለት "ጎሽ ጎበዝ ልጅ ለዛሬ ራስህን ችለህልኛል ከወጭ አሳረፍከኝ ዳይ ተነስ እንሂድ" ብላ ምሳዉን ሳይበላ የገዛሁለትን ኬክ አንጠልጥላ እየጎተተች ወሰደችው፡፡ "እውነት አሁን ይችም እናት ትባል ይሆን!!?" ብየ እማን አስታውሸ እንባየ ፈሰሰ ዳግም የልጁ ሁኔታ ፊቴ ድቅን አለ


ወደ ውጭ ወጥቼ ወደ ምድር አንገቴን አስግጌ ልጁን ተመለከትኩት ከፊት ለፊቱ ወዳየው ሰው ሩጫ ቀጠለ የልጁን ሩጫውን ተከትየ ሰመለከት አይኔን ማመን አቃተኝ ......

#ክፍል ➊➏
ይቀጥላል.......


https://t.me/IslamisUniverstiy_public_group
1.3K views05:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 14:52:11 ...... "እ አቤት" አልኩት በደከመ ድምፅ
........"ምን እያሰብሽ ነው? ርቀሽ ተጓዝሽ እኮ" አለኝ
...... "አረ ምንም አላሰብኩም እንዲሁ ተመስጨ ነው" አልኩት፡፡
...,, "እእ እኔ ደግሞ ስለኔ እያሰብሽ መስሎኝ" ሲለኝ የውስጤን በማወቁ ደነገጥኩ ..
....እንዴ ስለአንተ ምን አስባለሁ ??ከጎኔ ሆነህ ደግሞ!" ብየ የውሸት ፈገግ አልኩኝ፡፡ አሁንም ዳግም በመሀላችን ዝምታ ሰፈነ፡፡ በራሴ ምላሽ ተናደድኩ!!! ምናለ ስላንተ እያሰብኩ ነው ብለው ኑሮ??? እያልኩኝ በውስጤ " ወደ ቤት እንሂድ!?" አልኩት ስፈራ ስቸር " .......አንቺ ታሪክሽን ነገርሽኝ አንችስ እኔን ማወቅ አትፈልጊም???"አለኝ፡፡ ከራሱ በመምጣቱ ደስ እያለኝ "እፈልጋለሁ ግን እንዳረብሽህ ፈርቸ ነው ዝም ያልኩት" ብየ በደስታ ታሪኩን ለመስማት ጓጓሁ፡፡

አብደልከሪም ገና ንግግር ከመጀመሩ በፊት እንባ ተሽቀዳደመው፡፡ ሚስኪን የወንድ ልጅ እንባ ማየት ምንኛ ከባድ ነው!? እንባውን ሳይ ሆዴ በሀዘን ተላወሰ የምናገረው ጠፋኝ፡፡

" መሪ እኔ ማለት እናቴንም ሆነ አባቴን የማላውቅ እህት ወንድም የሌለኝ ብቸኛ የማደጎ ልጅ ነኝ! ተወልጄ ያደኩት ሳኡዲ ነው እናቴ እና አባቴ በስደት ከሀገር በወጡበት ሰአት ነው እህል ውሀ ያገናኛቸው፡፡ እናቴ እና አባቴ በተጋቡ ሰአት እናቴ ትስራባቸው የነበሩ ሰወች ማለትም የኔ አሳዳጊ ነበር መኖሪያ የሰጣቸው፡፡ ተጋብተው ብዙም ሳይቆዩ እኔ ተፀነስኩ ግን ምን ዋጋ አለው የአላህ ቀድር ሆነና አባቴ በመኪና አደጋ ሞተ፡፡ ይሄ ለእናቴ ከባድ የዱብእዳ ዜና ሆነባት ግን የአላህን ውሳኔ መሻር አይቻልም፡፡ እማ በሀዘን ብትቆራመትም እኔ ከተወለድኩ በኃላ ግን ደስተኛ ነበረች ሀዘኗን በእኔ ረሳች፡፡ እማ በኔ ደስተኛ ብትሆንም እኔ ገና በቅጡ እንኳን ራሴን ሳላውቅ ገና የ5 አመት ህፃን እያለሁ እማን ሞት ነጠቀኝ፡፡

እማ በሰው ሀገር ዘመድ ወዳጅ በሌለበት እኔን ጥላ ሞት ወደሷ መቅረቡን ስታውቅ ለአሰሪወቿ ነበር እኔን አደራ ብላ የሞተችው! ገና በልጅነቴ ክፉና ደጉን ለይቼ በማላውቅበት ሰአት እናቴን በሞት ሳጣ እጅጉን አዝኘ ነበር፡፡ አሳዳጊወቸ ሁለቱንም ወላጆቹን በሞት ያጣ የቲም ነው በማለት ለአላህ ብለው ነይተው ምንም ሳያጓድሉብኝ ከልጆቻቸው እኩል አድርገው አሳደጉኝ፡፡

እድሜየ እየጨመረ ሲመጣ ያኔ በልጅነቴ እናቴ ኢትዩጲያ ስንሄድ ቤተሰቦቼ ጋር ሀይቅ ነው የምንሄደው ትለኝ ነበር፡፡ "ሀይቅ ምንድነው" ብየ ስጠይቃት " የተወለድኩበት ሀገር ነው እዛ ትልቅ ሀይቅ ስላለ ሀገሩም በሀይቁ ስም ተጠራ እዛ ስንሄድ ከባህር እንደወጡ አሳ ትበላለህ በጀልባ ትሄዳለህ" ትለኝ የነበረው በህፃን አእምሮየ ውስጥ ታትሞ ቀርቷል፡፡

እናም እድሜየ እየጨመረ ሲመጣ አሳዳጊዎቼ ምርጫ ሁለት ሰጡኝ አንድ እዛው ሳኡዲ ውስጥ እንድኖር ሁለት ወደ ኢትዩጲያ መጥቸ መኖር እንደምችል እና መቋቋሚያ ገንዘብ እንደሚሰጡኝ ነገሩኝ፡፡ ኢትዩጲያን ከስሟ ውጭ ባላውቃትም የወላጆቼ ሀገር በመሆና እኔም ደግሞ ኢትዩጲያዊ እንጅ የአረብ ደም እንደለለኝ ስላወኩ ከአፈር ይልቅ ደሜን መረጥኩ እናም ወደ ኢትዮጲያ መጣሁ፡፡
..... አዲስ አበባ ላይ ቤት ንብረት አፈራሁ፡፡ ግን ሂወቴ ባዶ ነበር አንድም የኔ የምለው የምኖርለት ሰው የለም እማየ ስትናፍቀኝ የትውልድ ሀገሯ ወደ ሆነችው ሀይቅ በመጓዝ እናቴን በምናቤ እየሳልኩ ከሷ ጋር በሀሳብ ከጎኔ እንዳለች አድርጌ እዝናናለሁ፡፡ ሀይቅን እያካለልኩ ይሄ ልጅ የፋጡማ ልጅ ነው እሷን ይመስላል ብሎ አቅፎ የሚስመኝን ዘመድ በአይኔ እያማተርኩ እውላለሁ፡፡ ግን ይሄ ልጅ ዘመዴን መሰለኝ የሚለኝ ሰው እስካሁን አላገኘሁም! እኔ የቱንም ያህል ሰው ብራብ ግን መጥገብ አልቻልኩም ዘመድ ርቦኛል የቤተሰብ ፍቅር ርሀብተኛ ነኝ! ኢትዩጲያ ከመጣሁ ድፍን 4 አመት ሆነኝ ግን ርሀቤን የሚያስታግስልኝ አንድ እንኳን ዘመድ አላገኘሁም" ብሎ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡

ገና ሲተርክልኝ ጀምሮ የሚፈሰው እንባየ የሱ መንሰቅሰቅ ደግሞ እንደ አዲስ እንባየን አብዝቶ አወረደ፡፡ በእንባ ከመታጠብ ውጭ ቃል ከአፌ ማውጣት አቃተኝ፡፡ ንግግሩን ቀጠለ እናም ልክ እንደ ሁልጊዜው የእማን ናፍቆት ለማስታመም ሀይቅ ውየ ከሰአት ተመልሽ ከሚሴ ከተማ የሚገኝ አንድ በአላህ መንገድ ላይ ያገኘሁት የአኼራ ወንድም አለኝ እሱን ዘይሬ ንጋት ላይ ወደ አዲስ አበባ እመለሳለሁ ብየ አስቤ ነበር፡፡ የአላህ ቀድር ሁኖ ያኔ ሪምን መኪና ገጭቷት ሳይ አሳዘነችኝ እና ወደ ክሊኒክ ወሰድኳት ያኔ ገና ስትመጭ ከመኪና ስትወርጅ እንዴት ከመውደቅ ለትንሽ እንደተረፍሽ አየሁሽ ከአይንሽ የሚፈሰው እምባ ወደር አልነበረውም ለዛ ነበር እህቷ ነሽ ብየ የጠየኩሽ

በአንድ ጊዜ ተቀያይረሽ ስታንቂኝ ከምነግርሽ በላይ አሳዘንሽኝ በኃላ ደግሞ ወደ ቤት ስትሄዱ ባዶ እግርሽን መሆንሽን ሳይ በሪም በጣም ቀናሁ የኔን ሂወት ባዶነት የሚያስብልኝ ሰው አለመኖሩ ትዝ ሲለኝ ጩህ ጩህ ነበር ያለኝ፡፡ እናም እኔ የምናፍቀውን ፍቅር እናንተ ላይ ሳየው ዝም ብየ ልለያችሁ አልፈለኩም ባገኘሁት አጋጣሚ ሁሉ ተጠቅሜ ልቀርባችሁ ፈለኩ፡፡ ሙከራየም ተሳካልኝ የበለጠ ደግሞ ቀርቤ ሳያችሁ የኔ የገንዘብ እና ሀብት ክምችት ትርጉም አልባ ሆነብኝ እኔ ውጭ ላይ ውድ የሚባል ነገር ላይ ከማወጣው ወጭ ይልቅ እናንተ ቤት መጥቸ የማገኘው ትልቅ ፍቅር ይበልጥብኛል፡፡

እማማየ እንደ እናቴ ሪም እንደ እህቴ አዩብ ደግሞ በቃ ልክ እንደ ልጄ" ሲል ሳቄን ለቀኩት "ምነው ምን ያስቅሻል ልጄ ስላልኩ ነው? ልጅኮ በጣም ስለምወድ ነው!!" አለኝ " እሺ ይሁንልህ ባለ ልጅ የአዩብ አባት" ብየ አሁንም ሳኩበት፡፡ እሱም እየሳቀ አንች ደግሞ አቀልጅ እንጂ መቼም መዉለዴ አይቀር አለኝ
....እንደዚህ እየተጨዋወትን በለንበት ሰአት ...እኔ በሱ ሂወት ውስጥ የሚኖረኝን ቦታ ሳይነግረኝ የስልክ ጥሪ አስተጋባ፡፡ ስልኩን አንስቶ ንግግር ጀመረ፡፡ ሳይነግረኝ ስላቋረጠው ስልክ ተናደድኩ ግን ንዴቴን በፈገግታ ደበኩት፡፡ ንግግሩን እንደጨረሰ " ወደ ቤት አንሄድም?" አልኩት "አሁን መሄድ እንችላለን" አለኝ ከተቀመጠበት እየተነሳ ጉዞ ወደ ቤት ጀመርን " መሪ ሶስት ቀን ያህል ለመቆየት አዲስ አበባ መሄዴ አይቀርም እዛ ትንሽ እኔን የሚፈልግ ስራ አለ እሱን አስተካክየ በቻልኩት ፍጥነት እመለሳለሁ!" ሲለኝ በጣም ደነገጥኩ


ክፍል ➊➎
ይቀጥላል ......
join
@Islam_and_Science
1.6K views11:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 14:52:10 #የመራም_ማስታወሻ
           ክፍል ~ ➊➍
ፀሀፊ ☞አሚር ሰይድ




....." አወ ደህና ነኝኮ በሉ በቃ ደህና ዋሉ " ብየ ከቤት ልወጣ ስል "ቆይ ጠብቂኝ አሞሻል በዛ ላይ ፀሀይ ነው ባጃጅ ካጣሽ እንኳን ፀሀዩ የበለጥ ያሳምምሻል እኔ ላድርሰሽ"ሲለኝ ደንግጨ ሪምን ተመለከትኳት እና
..." አረ ምንም አያስፈልግም አመሰግናለሁ በራሴ መሄድ እችላለሁ"አልኩኝ፡፡
.......ሪም ጣልቃ ገብታ " እውነቱን ነው ባጃጅ አታገኝም ፀሀዩ ያሳምምሻል ይሸኝሽ" አለችኝ፡፡ ዝም ብየ ከቤት ወጣሁ እሱም ከኃላየ ተከተሎኝ መጣ ቀድሞ የመኪናውን በር ከፍቶ እንድገባ በእጁ ምልክት ሰጠኝ ምንም ቃል ሳንለዋወጥ መንገዳችንን ቀጠልን፡፡

በውስጤ " ለምንድነው የማያናግረኝ ስለሚፈራ ነው ወይስ ስለሚጠላኝ!? ደግሞ ከጠላኝ ለምን ይሸኘኛል ደግሞ ምን አድርጌዉ ይጠላኛል!?" እያልኩ እያውጠነጠንኩ ደረስን፡፡ ከመኪናው ልወርድ ስል "መራም" አለኝ አንገቴን ወደሱ አዞሬ በቅንድቤ አቤት አልኩት " ግን ለምን ትጠይኛለሽ እንኳን ልታናግሪኝ ልታይኝ እንኳን አስጠላሻለሁ አይደል? እባክሽ በጭፍን አትጥሊኝ ቢያንስ እንኳን አናግሪኝ"አለኝ
.....ደነገጥኩ "እእ የምን ጥላቻ አልጠላህም ስለማታናግረኝ ነው ዝም የምልህ" አልኩት፡፡
......"እና ከዚህ በኃላ ታናግሪኛለሽ!?" አለኝ፡፡
........ ትከሻየን እየሰበኩ" ካናገርከኝ አዎ አናግርሀለሁ!" አልኩት "
.......እሽ አመሰግናለሁ ከነገ ጀምሮ እናወራለን" ብሎኝ ሄደ፡፡ እኔም ወደ ስራየ ገባሁ፡፡

ከዚህ ጊዜ በኃላ ከአብደልከሪም ጋር መነጋገር መግባባት ጀመርን ስለኔ እያንዳንዷን ነገር ጠንቅቆ ያውቃል እናም በራሱ "ተምሳሌት" ብሎ ይጠራኛል፡፡ ስለራሱ ግን አንድም ቀን አያወራም፡፡ ተግባሩ መልካምነቱን ይገልፃል እንጅ ስለራሱም ሆነ ስለቤተሰቦቹ ሲያወራ አልሰማሁም፡፡


አንድ ቀን በተቀመጥንበት በኩል አቅመ ደካማ ሴት እንጨት ተሸክመው አየ ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደሴትየዋ ተጠግቶ ሸክማቸውን አወረደ እና ያወራቸው ጀመር፡፡ እኔ ከሩቅ ሁኔታውን እከታተላለሁ፡፡ ባጃጅ አስቁሞ ወደ ቤታቸው ሸኛቸው ከኪሱም ብር አውጥቶ ለሴትዬዋ እና ለሹፌሩ ሰጣቸው ብዙ መረቁት እነሱን ሸኝቶ ወደኔ ተመለሰ"
....አንተ ግን ምን አይነት ሰው ነህ!?"አልኩት
..... "ምነው!?" አለኝ "
......ማለቴ እንደ ሀብታም አትኮራም ድሆች ትወዳለህ እኔ ገና ያ የመጀመሪያ ቀን እማማየ ግባ ሲሉህ ያንተን የቅንጦሽ ኑሮ አስቤ የኛ ቤት ላንተ ያንስብሀል ብዬ ከውጭ እንድትመለስ ፈልጌ ነበር" ስለው------ ለሰከንዶች ያህል ዝምምም አለ እና በረጅሙ ተነፈሰ "እኔ ከየትኛውም ሰው በታች ደሀ እንደሆንኩ የማውቀው እኔ ብቻ ነኝ" አለ፡፡
,,,,,,,,,,ንግግሩ ግራ አጋባኝ " ምን ማለት ነው!? ቤት መኪና የራስህ የሆነ ስራ አለህ እና ከዚህ በላይ ምን ቀረብህ!?" አልኩ
..... "ይሄ ለእናንተ የሚታየው ነዋ መራም ከእኔኮ አንች ሀብታም ነሽ የሚወዱሽ የምትወጃጀው ሰወች አሉሽ"አለኝ በሀዘን ቅስሙ ተሰብሮ፡፡ ከንግግሩ በውስጡ ብዙ ብሶት እንዳለበት ገባኝና " እስኪ ታሪክህን በጠቅላላ ንገረኝ ልስማህ ግን ፈቃደኛ ከሆንክ ብቻ ነው የምትነግረኝ" አልኩት፡፡

ከንግግሩ ቀድሞ እንባው አይኑን ጥሶ ወጣ፡፡ እንባውን ሳይ ደነገጥኩ መጠየቄ ስህተት መሰለኝ "አብዲ በቃ ይቅርታ ማስታወስ የማትፈልገውን ነገር አስታወስኩህ በአላህ አታልቅስ አስጨነከኝ"አልኩት አይን አይኑን እያየሁ፤
.........እንባውን ጠረገና በረጆሙ ተነፈሰ፡፡ ዝምታ በመሀላችን ሰፈነ ጨነቀኝ መቆየት ይኑርብኝ መሄድ ግራ ገባኝ "አብዲ እንሂድ?" አልኩት ስፈራ ስቸር
--------"አይ ትንሽ እንቆይ ምነው አየሩ አልተመቸሽም ቦታውን አልወደድሽውም እንዴ!?" አለኝ
.... "ወድጀዋለሁ አረ ደስ ይላል" አልኩት፡፡ ቦታውን በርግጥም አረሳውም እማ ያኔ ሚስጥሯን ልትነግረኝ የመጣንበት ቦታ ነበር፡፡ በአይኔ ስቃኝ እኔና እማ ለመጨረሻ ጊዜ የተቀመጥንበት ቦታ ላይ የእማ ምስል ታየኝ፡፡ ከተቀመጥኩበት ተነስቸ ወደዛው አመራሁ፡፡ ስደርስ እማ ጠፋችኝ እማ ባዶ ቦታ ትታልኝ ምስሏን ሸሸገችብኝ እንባየ የአይኔን ግድብ ጥሶ መፍሰስ ጀመረ "መሪ ምን ሆንሽ በእኔ ነው የምታለቅሽው!?" አለኝ መልስ ሳልሰጠው ለቅሶየን ቀጠልኩ
........"መሪ አቁሚ በአላህ አስጨነቅሽኝ ወይም የሆንሽውን ንገሪኝ አብሬሽ ላልቅስ!" እያለ ልመናውን ቀጠለ፡፡
......."ታውቃለህ ለመጨረሻ ጊዜ ከእማ ጋር የመጣነው እዚህ ቦታ ነው ለመጨረሻ ጊዜ አቅፋ የሳመችኝ እዚህ ነው ከዛ በኃላ በቃ ተለያየን ያኔ ችግሯን ሳልረዳት እንድታወራ እድል ሳልሰጣት የራሴን ብቻ አውርቼ ተለየኃት ግን ምን ልትነግረኝ ነበር!?"ብየ ወደሱ ስዞር አይኑ በእንባ ርሷል፡፡ መልስ ሳይሰጥ ዝም አለኝ ንግግሬን ቀጠልኩ "ደግሞኮ አይዞሽ ደርሸልሻለሁ ብያት ነበር እንደዚህ ስላት ግን በጣም አዝና አለቀሰች ሚስኪን የኔ እናት ለካ እሷ ህመሟን በውስጧ አፍና ይዛ ነው፡፡ የዛኑ ለሊት ነው ታማ ሆስፒታል የገባችው እማ መሞቷ ቁርጥ ሲሆን አዩን እና ሪምን በአደራ ሰጠችኝ፡፡

እማየኮ ሚስኪን ናት እንደዛ ያሰቃያትን ሂወታችንን ምስቅልቅሉም ያወጣውን አባየን እንኳን ስትሞት ምን እንዳለችኝ ታውቃለህ አባታችሁ ይወዳችኃል እንዳትጠሉት ነበር ያለችኝ፡፡ እስኪ እሰበው እንደዚህ አይነት አባት.. አባት ይባላል? ጭራሽ የአባትነት ክብር የማይገባውን ሰው እሷ ግን ውደዱት ትላለች ቆይ አሁን ይሄ አባት ይባ...."ንግግሬን ሳልጨርስ አፌን እፍን አድርጎ እንዲህ አለኝ...
....." መሪ አንችኮ እድለኛ ነሽ ቢያንስ የምትናደጅበት አባት እንኳን አለሽ! እስኪ እኔን እይኝ አይደለም የምደሰትበት አንድም የምናደድበት ሰው የሌለኝ ባይተዋር ነኝ መሪ ታውቂያለሽ ከፀብ ጀርባ ፍቅር አለ፡፡ አባትሽን የተቀየምሽው ስለምትወጅው ነው ከሱ የምትጠብቂውን ነገር ማግኘት ባለመቻልሽ ተቀየምሽው ከዛም የጠላሽው መሰለሽ አይደል!? አለኝ፡፡
.." አይ በጭራሽ አልወደውም እንደውም ለሱ እምቅ የሆነ ጥላቻ ነው ያለኝ፡፡ ህልሜን ሰርቆኛል!" አልኩኝ ኮስተር ብየ
...."እሽ አሁን የጠላሽው አባትሽ አደጋ ደረሰበት ወይም ሞተ ቢሉሽ ምንም አይሰማሽ!?" ብሎ ጠየቀኝ፡፡
.. ስለሞት ሲያወራ ልቤ ቀጥ ያለች መሰለኝ ደነገጥኩ "አይ እንደዚህ እንዲሆን አልፈልግም መኖሩን አፈልጋለሁ ግን እሱን በአካል ማግኘት አልፈልግም! በቃ እሱም የራሱን ሂወት ይኑር እኛም እንኖራለን" ብየ ንግግሬን ጨረስኩ፡፡ ከዚህ በላይ ሊከራከረኝ የፈለገ አይመስልም ፈገግ አለና ዳግም በመሀላችን ዝምታ ሰፈነ፡፡ ሁለታችንም በየራሳችን አለም በሀሳብ ተጓዝን፡፡ የሱን ሀሳብ ባላውቅም እኔ ግን በውስጤ " እንኳን የምደሰትበት የምናደድበት ሰው የለኝም" ያለኝን ደጋግሜ እያሰላሰልኩ ስለሱ የማወቅ ፍላጎቴ ቢያሻቅብም እንዳልጠይቀው ፈራሁ ምናልባት ማስታወስ የማይፈልገውን ህመም እንዳልነካበት ፈራሁ እናም በዝምታየ ፀናሁ፡፡ ከረጅም ዝምታ በሆላ "መሪ"ብሎ ሲጠራኝ ከሀሳቤ ባነንኩ
1.3K views11:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 09:58:32 #የመራም_ማስታወሻ
           ክፍል ~ ➊➌
ፀሀፊ ☞አሚር ሰይድ


አንድ ቀን በስራ ሰአቴ እኔ ወደ ማስተናግድበት ካፌ ሁለት ሰወች ሲገቡ ተመለከትኩ ያየሁት ነገር አስደነገጠኝ ለተወሰኑ ሰከንዶች ድርቅ ብየ ቀረሁ፡፡

አዩ እና ልጁ ሲገቡ ተመለከትኩ ልቤ ምቱ ፈጠነ ስሜቴ ሁሉ ተዘበራረቀ ሰውነቴ በፍርሀት ራደ "እንዴ ምን ሁኜ ነዉ ይሄን ያህል??? ማንም ይምጣ ማን ስራየ ማስተናገድ ነው" ብየ ራሴን አደፋፍሬ አረጋጋሁ፡፡ እናም ወደ ተቀመጡበት ወንበር አመራሁ እና አዩን ሳምኩት "መሊ እእ አቢከሊይም እጄን መሪዉ ጋር ይዞ መኪና አስነዳኝ" አለኝ በደስታ እየተፍለቀለቀ "ጎበዝ የኔ ማር" ብየ በድጋሜ ሳምኩት በዚህ አጋጣሚ የልጁ ስም አብደልከሪም መሆኑን አወኩ፡፡
.....ወደሱ ዙሬ "ምን ልታዘዝ?" አልኩት " አሰላሙአለይኪ መራም" አለኝ ደነገጥኩ "ወአለይኩምሰላም ምን ላምጣልህ?" አልኩ ስለደነግጥኩ ቶሎ ከሱ መራቅ ፈለኩ " ጠቆር ያለ ማኪያቶ" አለኝ የአዩን ፍላጎት ሳልጠይቅ ቶሎ ተፈተለኩ፡፡

ግራ ገባኝ "ለምን ራሴን አስደነብራለሁ? እሱ ማነው?" አልኩና ለራሴ ያዘዘኝን ማኪያቶ እና ለአዩ በኔ ምርጫ ማንጎ ጭማቂ ይዠ ተመለስኩ፡፡ ኮስተር ብየ አስቀምጨ ተመለስኩ፡፡ ድጋሜ ወደዚህ ካፌ እንዳይመጣ በልቤ ዱአ አረኩ፡፡

ከስራ ወደ ቤት እንደተመለስኩ ሪም እና እማማየ ቡና አፍልተው ነበር፡፡ አዩ እንቅልፍ ወስዶታል፡፡ እኔም ልብሴን ቀይሬ ወደ ቡናው ተቀላቀልኩ፡፡ የሁለቱም ወሬ ስለ አብደልከሪም ነበር፡፡ ሪም ስለሱ ጥሩነት ስታወራ "ግን ማነህ አብደልከሪም!?" አልኩኝ በውስጤ ስለ መልካምነቱ እያነሱ ደጋግመው ስሙን ሲጠሩ ስለሱ የማወቅ ጉጉት አደረብኝ ግን እኔ ጋር ተነጋግረን ስለማናውቅ እንዴት ብየ እንደምቀርበው አላውቅም፡፡ የማላውቀው አይነት ስሜት ሲሰማኝ "እኔ ደክሞኛል በቃ ልተኛ የነገ ሰው ይበለን ደህና እደሩ" ብያቸው ከአዩ ጎን ተኛሁ፡፡

ጎኔ ቢጋደምም እንቅልፍ ግን ከአይኔ ራቀ ያኔ በቁጣ ተንደርድሬ ያነኩት ቀን የነበረውን እርጋታ አስታወስኩ፡፡ ከዛ ቀን ጀምሮ የነበረውን ሁኔታ በሀሳብ የኃሊት ተጉዤ መረመርኩ፡፡ "አብደልከሪም ግን ለምን ወደ ሂወታችን መጣህ!?" እያልኩ በለለበት ጥያቄ መልስ ከየት ይምጣ፡፡ ሪም ከጎኔ መጥታ ስትተኛ የተኛሁ መስየ አይኔን ጨፈንኩ፡፡ " መሪ አለሽ አልተኛሽም አውቅብሻለሁ እያሰብሽ ነዋ!?" አለችኝ
...... " አይ እንዲሁ እንቅልፍ እንቢ ብሎኝ እንጂ ምን አስባለሁ ብለሽ ነው?" አልኳት፡፡ ሪም ሳልናገር ገና አይታ የማስበውን ታውቃለችና ፈገግ አለች "አብደልከሪም እያሳሰበሽ አይደለም?" አለች፡፡
.....ደነገጥኩ አፌ እየተንተባተበ "ለምን ምን ስለሆነ?" አልኳት ይሄን ጥያቄ ለራሴ ጠይቄ መልስ ያጣሁለት ቢሆንም ዳግም እሷን ጠየኳት፡፡
......."መሪ አብደልከሪም በጣም የሚያሳዝን የታሪክ ባለቤት ነው! አንችን አውቅሻለሁ እህቴ ነሽ ሰው አትጠይም ሰው ወዳድ ነሽ አሁን ግን አብደል ከሪምን ስትሸሽው አይሻለሁ ያማለት ደግሞ የሆነ ስሜት ለሱ አለሽ ማለት ነው ሽንፈትን በመሸሽ ልታመልጭ እየሞከርሽ ነው! መልካምነት ሁሌም አሸናፊ ነው ለመልካምነቱ ብትሸነፊ ክፋት የለውም እማማየ ደግሞ ስለ ሁሉም ነገር ታሪካችንን ነግረውታል" አለችኝ፡፡
....... ሪም የልቤን አውቃ ስትነግረኝ በእጄ እጇን ይዠ" እህቴ አንች ልክ ነሽ አዎ ለሱ የተለየ ስሜት ይሰማኛል ስራ ቦታ የሚመጡ ባለሀብቶት ያላቸውን ኩራትና ንቀት ብዙ አይቻለሁ ግን አብደልከሪም ከዛ ተቃራኒ ሆነ የመጀመሪያ ቀን ቤት እንዳይገባ በጣም ፈልጌ ነበር ግን እሱ ከመኩራራት ይልቅ እንደውም ደስተኛ ነበር ሪም ግን ምን አይነት ሰው ነዉ ብየ ሰለሱ ለማወቅ ሳስብ ስሜቴ ይዘበራረቃል ሳየው ደግሞ ሰውነቴ ይርዳል እና ዳግም ወደኔ እንዳይመጣ ተኮሳትሬ ፊት እነሳዋለሁ እሽ ምን ላርግ!?" አልኳት፡፡ "ተረጋግተሽ ቅረቢው አሁን እንተኛ" ብላ አቅፋኝ ተኛች፡፡

እማማየ በጠዋት የመነሳት ልምድ ቢኖራቸውም ዛሬ ግን ከወትሮው ተለዩብኝ፡፡ በጠዋት ተነሱ ቤቱ ይዘጋጅ ቶሎ ቁርስ ስሩ ማለት ጀመሩ፡፡ እኔ ራሴን ስላመመኝ ሪምን ስሪ ብየ መልሸ ከአዩ ጋር ተኛሁ፡፡ በተኛሁበት ከአዩ ጋር ስጫወት ሪም "ተነሱ ቁርስ ደርሷል" ብትለንም ጨዋታችንን አላቆምንም ቢያመኝም አዩን ደስ እንዲለው ብየ ጨዋታየን ቀጥያለሁ፡፡
......ከውጭ "አሰላሙአለይኩም" የሚል የወንድ ድምፅ ሰማሁ፡፡ ድምፁን ስሰማ ደነገጥኩ ወደ ሪም ዞርኩ ሪም እኔን እያየች ነበር፡፡
..... አዩ "አቢከይም መጣ" ብሎ ሮጦ ተጠመጠመበት እማማየ "ግባ ልጄ ቁጭበል" ይላሉ "እዚህ ተቀመጥ" አለች ሪም፡፡ እኔ ብቻ አይጥ እንደ ጎረሰች ድመት ልሳኔ ተዘጋ፡፡ ከመኝታየ ተነስቼ ፊት ለፊት ከመፋጠጥ እንደተኛሁ መቅረትን መረጥኩ ቁርስ ሲበሉ ሪም በተኛሁበት ከኔ ጋር በላች፡፡

እማማየ የጠዋት ቡና ይወዳሉና ሁሌም ቡና ይፈላል፡፡ አዩብ ከአብደል ከሪም ጋር ይጫወታል እሱም ልክ እንደሱ እየሆነ ያጫውተዋል ከኃላ ሁኔታቸውን አይቼ ሳኩ፡፡ ቡናው ፈላ እኔ ግን አሁንም አልተነሳሁም፡፡ እማማየ ወደኔ ዙረው "አንች ልጅ ካልተሻለሽ ዝም አትበይ ወደ ሀኪም ቤት እንሂድ"አሉ፡፡"አይ ደህና ነኝ አሁን ይተወኛል" ስላቸው መራምን "አሟት ነው እንዴ?" ብሎ ጠየቃት፡፡
....."አወ ራሷን አሟታል ሱቢሂን በግድ ነው የሰገደችው" አሉት፡፡
ወደኔ ዙሮ " መራም ተነሽ ወደ ሆስቲታል እንሂድ መታየት አለብሽ" አለኝ፡፡
......"አረ አሁን ይተወኛል ለዚህ ደግሞ ሀኪም ቤት መሄድ አያስፈልግም ሪም ፓራሲታሞል ስጭኝ" አልኳትና መድሀኒቱን ወስጄ አረፍ አልኩ፡፡
...አብደል ከራም በተደጋጋሚ መሄድ አለብሽ ቢለኝም ባለመሄድ አቋሜ ፀናሁ... ትንሽ ሲቀንስልኝ ተነስቸ የቆሸሹ እቃወችን ማጠብ ጀመርኩ፡፡ እማማየ "እኔ ልጠበው አንች ተኝ" ቢሉኝም አልሰማኃቸውም፡፡

አብደልከሪም ከጎኔ መቶ ቁጭ አለ ምንም ሳይናገር የማጥበውን እቃ እያጠራ ያስቀምጥ ጀመር፡፡ "አረ ተወው ሂድ ተቀመጥ እኔ አጨርሰዋለሁ ትንሽ ናትኮ" ብለውም አልሰማኝም፡፡ ሰአቱ ሲሮጥ ለጉድ ነው፡፡ የዝሁር ሰላት ደረሰ ዝሁርን ሰግደን ምሳ በልተን እንደጨረስን 8 ሰአት ስራ መግባት አለብኝ እና ለመሄድ ስዘጋጅ......
አብደልከሪም "እንደዚህ አሞሽ ስራ ልትሄጅ ነው!?" አለኝ ድምፁ የሀዘን ቅላፄ አለበት፡፡
....." አወ ደህና ነኝኮ በሉ በቃ ደህና ዋሉ " ብየ ከቤት ልወጣ ስል "ቆይ ጠብቂኝ አሞሻል በዛ ላይ ፀሀይ ነው ባጃጅ ካጣሽ እንኳን ፀሀዩ የበለጥ ያሳምምሻል እኔ ላድርሰሽ"ሲለኝ ደንግጨ ሪምን ተመለከትኳት..............
የመራም ታሪክ ምዕራፍ ➊➍ ነገ ይቀጥላል

Join
https://t.me/IslamisUniverstiy_public_group
1.6K views06:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 13:25:18 ቤት አልፎ አልፎ የሚመጣ ቢሆንም ከጊዜ በኃላ ግን ሁል ጊዜ ቤት መምጣት ጀመሮ ለአይኔ በዛብኝ ቃል አውጥተን ባንነጋገርም አልፎ አልፎ አይን ለአይን እንገጣጠማለን፡፡


አንድ ቀን በስራ ሰአቴ እኔ ወደ ማስተናግድበት ካፌ ሁለት ሰወች ሲገቡ ተመለከትኩ ያየሁት ነገር አስደነገጠኝ ለተወሰኑ ሰከንዶች ድርቅ ብየ ቀረሁ፡፡
...ማን ገብቶ ይሆን ???
በክፍል ➊➌
ይቀጥላል........

Join
@Islam_and_Science
1.8K views10:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 13:24:38 #የመራም_ማስታወሻ
           ክፍል ~ ➊➋
ፀሀፊ ☞አሚር ሰይድ



......እጁን ቀስሮ በአየር ላይ "ሪም " ከማለቱ ገና ከአፉ ነጥቄ
...... "ሪም ምን ሆነች!!?" አልኩት ልቤ ምቱ ፈጠነ " ..........መኪና ገጫት.."
በቆምኩበት ድርቅ ብየ ቀረሁ ጨለመኝ ሁሉም ነገር ዞረብኝ በደመነፍስ ሩጫ ቀጠልኩ የምሄድበትን ግን አላውቅም፡፡ አቤል ተከትሎኝ ሮጠ እማማየም ከኃላ "መራም አረ ቆይ ልጀ ተረጋጊ እንጂ" እያሉ ተከተሉኝ፡፡

እኛ ሰፈር አብሮ አደጋችን ሀቢብ ለእናቱ ክሰል አምጥቶ ሲመለስ ነበር የተገጣጠምነው መኪናውን አቁሞ " መሪ ምን ሁነሽ ነው የምትሮጪዉ?? የምትሄጅበት ቦታ ካለሽ ላድርስሽ !? ግቢ" አለኝ፡፡

ወደ ሀቢብ መኪና ገባሁ ያለገደብ ከአይኔ የሚፈሰውን እንባ አይቶ ደንግጧል "ሀቢብ በአላህ አፋጥነው! አፍጥነው ቶሎ በል!" አልኩኝ ወዴት መሄድ እንዳለበት ግራ ገባው፡፡ አቤል እየሮጠ ደረሰብኝና ሀቢብ መኪና ሲገባ "አቤሎ ምንድነው ነገሩ አንተ ንገረኝ እንጅ ሁላችሁም ዝም ብላችሁ አስጨነቃችሁኝኮ በአላህ!"አለ ሀቢብ.....
......፡ "ሪም መኪና ገጭቷት ነው ወደ ሀያት ክሊኒክ ውሰደን" አለው፡፡ "ገጭቷት" የሚለውን ቃል ስሰማ ጭንቀቱ የብስ ባሰብኝ! ሀቢብም በጣም ደነገጠ የሚለው ጠፋበት ከሪም ጋር በእድሜ በተወሰነ አመት ነዉ የሚለያዩት አቅፎ ተንከባክቦ አሳድጓታል ከልጅነቷ ጀምሮ በጣም ይወዳታል፡፡


ሀቢብ በፍጥነት እየነዳ ክሊኒኩ ደረስን፡፡ መኪናው በቅጡ ሳይቆም ለመውረድ ስሞክር በአፌ ከመደፋት አላህ ነው ያዳነኝ .......ሰወች በሁኔታየ ጮሁ እኔ ግን ሪምን ማየት ብቻ ነው ፍላጎቴ! ወደ ውስጥ ስገባ ሪም ግንባሯን እና እጇን ታሽጋ ቁጭ ብላለች ከጎኗ ፈንጠር ብሎ አንድ ወጣት ልጅ ተቀምጧል፡፡ ሳያት በእንባ የታጠበው ፊቴ መልሶ በእንባ ጎርፍ መታጠብ ጀመረ፡፡ "እንዳላቅፍት እንደብርጭቆ የምትሰበርብኝ መሰለኝ ሳሳሁላት፡፡

" ሪም የኔቆንጆ ደህና ነሽ!?" አልካት እግሯ ስር ተንበርክኬ በስስት እያየሆት
......."ደህና ነኝኮ አታልቅሽ" እያለች እንባየን ጠረገችልኝ፡፡ ከአጠገቧ ራቅ ብሎ የተቀመጠው ልጅ "እህቷ ነሽ?" ሲለኝ መልስ ከመስጠት ይልቅ "አንተ ነህ የገጨሀት አይደል!?" ብየ እንደ አራስ ነብር ተከመርኩበት፡፡ እጄን ለማላቀቅ ራሱን ለመከላከል እንካን አልሞከረም ዝም ብሎ በአትኩሮት ተመለከተኝ፡፡

እማማየ "መሪ ተይ ብየሻለሁ ቢገጫትስ ይሄው እጅ ሰቶ መጥቶ እያሳከማት ነዉ .... ገጭቷት ቢጠፋ ነበር ክፉ የሚያስብለው ልጄ እሱምኮ ፈልጎት አይደለም አላህ አገጣጥሞበት እንጅ" አሉ፡፡
.......ሪም ቀጠል አርጋ "መሪ በአላህ ተረጋጊ እሱኮ አይደለም የገጨኝ፤የገጨኝ ትቶኝ ሲሄድ አይቶ እሱ ነው አንስቶ ያመጣኝ" ስትለኝ ሰውነቴ እንደ በረዶ ቀለጠ እጆቼ ተንቀጠቀጡ "ይቅርታ" አልኩት ቃል ከአፉ ሳያወጣ ቅንጭላቱን በማወዛወዝ እሽታውን ገለፀልኝ፡፡

......ሀቢብ ሪምን አይቶ " አንች ሚዳቆ ይሄኔኮ ሩጠሽ ገብተሽበት ነዋ!?" ብሎ ሲቀልድባት
.....ሪምም እንደ አንተ እጁን ያላጠራ ሹፌር ገጥሞኝ ነዉ ብላ ሀቢብን ነካ አረገችዉ፡፡

ሪም ከባድ የሚባል ጉዳት አላጋጠማትም ትንሽ ግንባሯ ተፈርክሷል እጇ ተልጧል እንጅ የሚያሰጋ ነገር የለም፡፡ ሀቢብ ደህንነቷን ካየ በኃላ " በቃ እኔ ልሂድ ቢሮ ይፈልጉኛል አንች አይጥ ደግሞ ሙዝና ብርቱካን ፈልገሽ አይደል የተገጨሽው ከስራ ስወጣ ይዠልሽ እመጣለሁ" ብሎ አስቆን ሄደ፡፡

ሪም ደህንነቷን ደጋግሜ ጠይቂያት በጣም ደህና ነኝ ብላኛለች ..በቃ ወደ ቤታችን እንሂድ ብለን ስንነሳ እማማየ ልጅን እየመረቁ በየ መሀሉ ይመክሩት ነበር፡፡ እማማየ በቃ እንሂድ ወደ ቤት ብያቸው ቅድም ይቅርታ የጠየኩትን ልጅ አሁን ደግሞ ስላደረገልን መልካም ነገር "አላህ ኸይር ጀዛህን ይክፈልህ"አልኩት "አሜን" አለኝ፡፡


ወደ ቤታችን ለመመለስ ባጃጅ ብንጠብቅ በዋዛ ማግኘት አልቻልንም ሁሉም እየሞላ ነው የሚመጣው ጠበቅን ጠበቅን ከዛም " እዚህ ጠብቁኝ ወይ ኮንትራት ይዠ ልምጣ" ብየ መራመድ ስጀምር ለካ ባዶ እግሬን ነኝ፡፡ በባዶ እግሬ መንገድ ጀመርኩ ትንሽ እንደተራመድኩ ሪም "መሪ መሪ ነይ" አለችኝ በእጇ ምልክት እየሰጠችኝ ስመለስ አሁንም ያው ልጅ እኔ ላድርሳችሁ ግቡ ተቡለው መኪናዉ ዉስጥ ገብተዋል፡፡ በውስጤ "ኡፍ ገላገልከኝ" አልኩኝ፡፡

ወደ ሰፈር አድርሶን ሊመለስ ሲል እማማየ "ልጄ ምነው እዚህ አድርሰህን ቤት ሳትገባ መሄድህ?? በል ውረድ አንተም" አሉት
....እኔ ክው ብየ ቀረሁ ከአለባበሱ ጀምሮ መኪናውም ቢሆን ውድ የሚባሉ አይነት ነው፡፡ እሱ የሚኖርበትን የቅንጦሽ ኑሮ ከእኛ ጋር ሲወዳደር እዚህ ግባ የሚባል አይደለምና እኛ ቤት ያለውን ነገር ሳስብ ደንግጨ ቁሜ ቀረሁ በሆዴ መቼም አይገባም ብየ ሳስብ
......"ማዘር ማስቸገር እንዳይሆንብኝ እንጅ ብገባ ደስ ይለኛል" ሲል የበለጠ ደነገጥኩ
........"አረ የምን ችግር ልጄ ና እንግባ" ብለው ከፊት መንገድ እየመሩት ተከተላቸው እኔ ከኃላ በድንጋጤ እራመድ ይዣለሁ ሪምን ሳያት ሳቀችብኝ


ወደ ቤት ስንገባ የሰገድኩበት ሙሰላ እንደተነጠፈ ነበር፡፡ ፈጠን ብየ አነሳሁት " ቁጭ በል የኔ ልጅ" አሉት፡፡ እኔ ጨነቀኝ ምናልባት ስራ ቦታ ላይ የማያቸው ሀብታሞች ሁኔታ ይሆናል ያስጨነቀኝ፡፡

ሪም አልጋው ላይ ጋደም ብላ የሚሆነውን ታያለች፡፡ እማማየ "መሪ መክሰስ አዘጋጅ" አሉኝ፡፡ እኔ እሺ ብየ እኛ የምንበላዉ ከምንጠጣዉ ቤት ካፈራዉ ምግብ አዘጋጅቼ ቡና አፈላሁ፡፡ ከዛም አቀረብኩኝ...የቀረበለትን መክሰስ ከእማማየ ጋር አብሮ ደስ እያለው በላ፡፡
ቡና እያፈላሁ የአዩን ድምፅ ሰማሁ " አዩ ና ወደ ቤት ግባ " አልኩት
..... "መሊ ኔማ አድ ላሳይሽ"አለኝ አየተኮላተፈ
........... "ምን ልታሳየኝ ??ነው" አልኩት
....."በፊም የሚታይ መኪና" አለኝ፡፡ አቅፌ ሳምኩትና ቤት አስገባሁት፡፡

ሪም ታሽጋ ሲያይ ለማልቀስ ዳዳው "ማነው የመታሲ"አላት በቁጣ መንፈስ
..."ወድቄ ነው እሽ ማሬ" አለችው
...."ማን ገፍትሮስ"አላት "
..... አዩ ና መክሰስህን ብላ አራበህም እንዴ??" አልኩት
......."እርቦናል ግን ሊም ማን ያበላታል አመማት" አለ፡፡
..... አንተ ብላና ለሷ እኔ አጎርሳታለሁ አልኩት፡፡ ምግብ እንዳቀረብኩለት ወደ እንግዳው ልጅ ቀርቦ "እንብላ" አለው እሱም እንደገና እጁን ታጥቦ መብላት ጀመረ፡፡ ከአዩ ጋር በፍጥነት ተላመዱ፡፡ በርግጥ አዩ የሚወደድ ልጅ ነው፡፡ ከዛ እኛን አመስግኖ ሪምንም አላህ ያሽርሽ እየመጣሁ እጠይቅሻለሁ አብሽሪ ብሎ እማማየም መርቀዉት ከቤት ወጥቶ ሄደ፡፡

እማማየ ከዛ ጊዜ ጀምሮ ከልጁ ጋር ጥብቅ ወዳጅ ሁነዋል፡፡እማማየ ብቻ ሳይሆኑ አዩንም ይጨምራል ብዙ ጊዜ ቤት እየመጣ ይጠይቃቸዋል አዩን የተለያየ ቦታ እየወሰደ ያጫውተዋል ያዝናናዋል ውዴታቸው ጨምሯል እኔ ግን ስሙን እንኳን አላውቀውም፡፡

እማማየ ሳያነሱት ውለው አያድሩም ግን "ያ መልካም ልጅ"ነው የሚሉት እንጅ ስሙን ሲጠሩ አልሰማም ይገርማል ግን በምን ቋንቋ ተግባቡ??? ልጁኮ ከአፉ ቃል አያወጣም ዝምታ በሱ ላይ ነግሷል! በእርግጥ እኔ ስራ ስለምውል ብዙ አንገናኝም ነገር ግን እግር ጥሎን እንኳን ከተገናኘን ከዝምታ ውጭ ሌላ አላይበትም፡፡
ግን ደግሞ ቤት ሲመጣ ደስተኛ ይሆናል እንደሀብታም ተብየዎች  አያካብድም ልክ እንደኛ ሁኖ ለሰወች ይተናነሳል፡፡
1.7K views10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 13:21:38 ማህበረሰብ ለመባል ብቁ ሁኝ ...በዉበት የምትተማመኝ ከሆነ የአንቺ መጨረሻ የጭንገርድ ሁነሽ መቀመጥ ብቻ እንደሆነ አዘንጊ
ግን ሰው ባመነበት መንገድ ባሻው ቢጋልብ የራሱ ውሳኔ ነውና እኔም ባለችኝ ደመወዝ ከምወዳቸው ሰወች ጋር በደስታ መኖር መርጫለሁ፡፡


በንፋስ ፍጥነት የሚከንፈው የጊዜ ቆጣሪ ወደ አመቱ መገባደጃ ተጠግቶ እነሆ የአመቱ መጨረሻ ማጠቃለያ ፈተና ደረሰ፡፡ ፈተና እንደጨረሰች ሪም እና አዩብን የሆነ ቦታ እንደምወስዳቸው ቃል ገብቸላቸዋለሁ፡፡ እኔም ቃሌን ለመጠበቅ ዛሬ ፈተና የመጨረሻ ቀን ስለሆነ አዩና ሪምን የተሻለ ሆቴል ወስጄ እራት ልጋብዛቸዉ ወስኜ ከትምህርት እሰከምትመጣ እየጠበኩ ነው፡፡ የአሱር ሰላት ሰግጀ በተቀመጥኩበት ከእማማየ ጋር የሞቀ ወሬ ይዘናል፡፡
..... አቤል ከውጭ መሪ መሪ ብሎ በተቆራረጠ ትንፋሽ እየጮሀ ሲጣራ ሩጨ ወጣሁ.....
የአቤልን መደናገጥ እና የልብ ምት መፍጠን ሳይ እኔም በመደንገጥ "አቤሎ ምን ተፈጠረ ምን ሁነህ ነው!?" አልኩት፡፡
......እጁን ቀስሮ በአየር ላይ "ሪም " ከማለቱ ገና ከአፉ ነጥቄ
...... "ሪም ምን ሆነች!!?" አልኩት ድንጋጤ በአንዴ ሰዉነቴን ወረረኝ.... ልቤ ምቱ ፈጠነ.....


የመራም ፈተና እንደ ተተበተበ ክር መፍታት የከበደ ይመስላል እህቷ ሪም ምን ሁና ይሆን???

Part ➊➋
ይቀጥላል......
Join

t.me/IslamisUniverstiy_public_group
  t.me/IslamisUniverstiy_public_group
1.2K views10:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ